• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” ቡድን አፍራሽ ተግባሩ ቀጥሎበታል

October 30, 2015 12:13 am by Editor Leave a Comment

በጅዳ ቆንስላ ጸ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” የተሰኘው ቡድን ጽ/ቤቱ ለሕዝብ መሥራት ከሚገባው ጉዳይ በመውጣት በግለሰቦች ማንነት እና ሃይማኖት ላይ ጽንፈኛ አቋም እየያዘ መምጣቱ ታወቀ፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት “በመልካም አስተዳደር ሽፋን” ዙሪያ ይካሄዳል ተብሎ የተጠራው አሁን ካለው የከረረ ሁኔታ አኳያ ግጭት ያስነሳል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡

በተለያዩ ሁኔታዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት “በመልካም አስተዳደር” ዙሪያ ሰሞኑን በተደረገው ግምገማ ጥቂት የደቡብ ተወካይ ነን የሚሉ ግለሰቦች አማራውን በብሄር እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በሃይማኖት በመከፋፈል የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ ጅዳ እና አካባቢዋን ስጋት ውስጥ ከቷል። በተለይ እራሱን “ወገን ለወገን” እያለ የሚጠራው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው የቆንስላ ቡድን የተካሄደውን ግምገማ ተከትሎ በቆንስላው ተገልጋይ ላይ ሲፈፀም ለነበረው በደል እና መጉላላት በቀጥታ የአማራውን ብሄር ተወላጆች ተጠያቂ በማድረግ የጀመሩትን የስም ማጥፋት ዘመቻ በማጠናከር በአካባቢያችን የሚገኙ ታዋቂ የብሄሩ አባላትና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያላቸውን ጥላቻ በመግለጽ ግምገማውን ለሌላ አጀንዳ ማስፈፀሚያ መጠቀማቸውን የቆንስላው ምንጮች ይገልጻሉ።

ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን በተገልጋዩ ችግሮች ዙሪያ ከመስራት ይልቅ ማህበረሰቡን መቋጫ ወደሌለው የእርስ በእስር ቅራኔና ግጭት ለመዝፈቅ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይናገራሉ። ቆንስላ ውስጥ የአንድ ብሄር አባል እና እምነት ተከታዮች ነጥሎ ለመምታት እየተደረገ ያለው ጥረት በአሁኑ ሰዓት ከቁጥጥር ውጭ በመሆኑ የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የጠራውን ህዝባዊ ስብሰባ ላልተወሰን ጊዜ መራዘም እንደሚገባው የሚናገሩ እነዚህ ውስጥ አዋቂዎች በመልካም አስተዳደር ሽፋን በተጠራው ስብሰባ ላይ ሊደርስ ለሚችለው ግጭት የቆንስላው ሹማምንቶች ሃላፊነቱን መውሰድ እንደሚገባቸው ያሳስባሉ። ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያቀነባበረውን ሴራ ከጀመረ አመታትን ቢያስቆጥርም፤ ሰሞኑንን ቆንስላ ውስጥ ቁልፍ ሃላፊነት ቦታ ላይ በተቀመጡ አንዳንድ ሹማምንቶች አይዟችሁ ባይነት በአዲስ መልክ ቡድኑ የጀመረው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እየደረሰ መምጣቱ ለማወቅ ተችሏል።

jedaቡድኑ እስከ ሪያድ በዘለቀው ፀረ ብሄርና ሃይማኖት ቅስቀሳው የ2008 አዲስ አመት ተከትሎ የአማራ ብሄር ተወላጆች ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ሊያከብር የነበረውን አውደ ዓመት አሳግዷል። የአማራን ብሄር ተወላጆችን ከመጠጥ እና ከሴስኝነት ጋር በማያያዝ የስም ማጥፋት ዘመቻውን ያጠናከረው ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን እየፈፀመ ባለው አስነዋሪ ተግባር በአካባቢው ማህበረሰብ የሁለቱም እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።

በቪዛ ነጋዴዎችና ደላሎች የሚደገፈው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው ይህ ቡድን ቆንስላ ውስጥ በህዝባችን ላይ ለተፈፀመው በደል የቆንስላው ሹማንቶችን በሙሉ ተጠያቂ ማድረግ ሲገባው “በመልካም አስተዳደር” ሽፋን በጅዳ የአማራ ብሄር ተወላጅ እና የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነው የኢሚግሬሽን ኃላፊ ሹም በመወንጀል ቡድኑ ድብቅ አጀንዳውን ለማስፈፀም በመራወጥ ላይ ይገኛል።

ይህ በዚህ እንዳለ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌለውን በጅዳ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ እና በኮንትራት ሰራተኞች ላይ የሚፈፀመውን ግፍ እና በደል በመዘገብ የሚታወቀውን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ጨምሮ በጅዳ እና አካባቢው የሚኖሩ የብሄሩ ተወላጅ የሃገር ሽማግሌዎችና ተዋቂ ሰዎች በዘር ሃረጋቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ የዘመቻው ስለባ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ለጥቅምት 5፣ 2015 ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ አግባብ አይደለም የሚሉ ነዋሪዎች ጥሪው በጅዳ እና አካባቢ የተፈጠረውን ውጥረት የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ ጥቂቶች የብዙሃኑን ፍቅር ለማግኘት “የቀይ ሽብር ወንጀለኞች የማጋለጥ ድራማ” የሚለይ ባለመሆኑ ከስብሰባው በፊት በኃይማኖት እና በብሄር ጥላቻ የተዘፈቀው ቡድን ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እና ከቆንስላው መታገድ እንዳለበት ይስማሙበታል። (ዘገባውን ከምስል ጋር ለጎልጉል የላኩት Ethiopian Hagere Jed Bewadi ናቸው፡፡)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule