• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” ቡድን አፍራሽ ተግባሩ ቀጥሎበታል

October 30, 2015 12:13 am by Editor Leave a Comment

በጅዳ ቆንስላ ጸ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” የተሰኘው ቡድን ጽ/ቤቱ ለሕዝብ መሥራት ከሚገባው ጉዳይ በመውጣት በግለሰቦች ማንነት እና ሃይማኖት ላይ ጽንፈኛ አቋም እየያዘ መምጣቱ ታወቀ፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት “በመልካም አስተዳደር ሽፋን” ዙሪያ ይካሄዳል ተብሎ የተጠራው አሁን ካለው የከረረ ሁኔታ አኳያ ግጭት ያስነሳል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡

በተለያዩ ሁኔታዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት “በመልካም አስተዳደር” ዙሪያ ሰሞኑን በተደረገው ግምገማ ጥቂት የደቡብ ተወካይ ነን የሚሉ ግለሰቦች አማራውን በብሄር እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በሃይማኖት በመከፋፈል የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ ጅዳ እና አካባቢዋን ስጋት ውስጥ ከቷል። በተለይ እራሱን “ወገን ለወገን” እያለ የሚጠራው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው የቆንስላ ቡድን የተካሄደውን ግምገማ ተከትሎ በቆንስላው ተገልጋይ ላይ ሲፈፀም ለነበረው በደል እና መጉላላት በቀጥታ የአማራውን ብሄር ተወላጆች ተጠያቂ በማድረግ የጀመሩትን የስም ማጥፋት ዘመቻ በማጠናከር በአካባቢያችን የሚገኙ ታዋቂ የብሄሩ አባላትና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያላቸውን ጥላቻ በመግለጽ ግምገማውን ለሌላ አጀንዳ ማስፈፀሚያ መጠቀማቸውን የቆንስላው ምንጮች ይገልጻሉ።

ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን በተገልጋዩ ችግሮች ዙሪያ ከመስራት ይልቅ ማህበረሰቡን መቋጫ ወደሌለው የእርስ በእስር ቅራኔና ግጭት ለመዝፈቅ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይናገራሉ። ቆንስላ ውስጥ የአንድ ብሄር አባል እና እምነት ተከታዮች ነጥሎ ለመምታት እየተደረገ ያለው ጥረት በአሁኑ ሰዓት ከቁጥጥር ውጭ በመሆኑ የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የጠራውን ህዝባዊ ስብሰባ ላልተወሰን ጊዜ መራዘም እንደሚገባው የሚናገሩ እነዚህ ውስጥ አዋቂዎች በመልካም አስተዳደር ሽፋን በተጠራው ስብሰባ ላይ ሊደርስ ለሚችለው ግጭት የቆንስላው ሹማምንቶች ሃላፊነቱን መውሰድ እንደሚገባቸው ያሳስባሉ። ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያቀነባበረውን ሴራ ከጀመረ አመታትን ቢያስቆጥርም፤ ሰሞኑንን ቆንስላ ውስጥ ቁልፍ ሃላፊነት ቦታ ላይ በተቀመጡ አንዳንድ ሹማምንቶች አይዟችሁ ባይነት በአዲስ መልክ ቡድኑ የጀመረው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እየደረሰ መምጣቱ ለማወቅ ተችሏል።

jedaቡድኑ እስከ ሪያድ በዘለቀው ፀረ ብሄርና ሃይማኖት ቅስቀሳው የ2008 አዲስ አመት ተከትሎ የአማራ ብሄር ተወላጆች ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ሊያከብር የነበረውን አውደ ዓመት አሳግዷል። የአማራን ብሄር ተወላጆችን ከመጠጥ እና ከሴስኝነት ጋር በማያያዝ የስም ማጥፋት ዘመቻውን ያጠናከረው ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን እየፈፀመ ባለው አስነዋሪ ተግባር በአካባቢው ማህበረሰብ የሁለቱም እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።

በቪዛ ነጋዴዎችና ደላሎች የሚደገፈው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው ይህ ቡድን ቆንስላ ውስጥ በህዝባችን ላይ ለተፈፀመው በደል የቆንስላው ሹማንቶችን በሙሉ ተጠያቂ ማድረግ ሲገባው “በመልካም አስተዳደር” ሽፋን በጅዳ የአማራ ብሄር ተወላጅ እና የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነው የኢሚግሬሽን ኃላፊ ሹም በመወንጀል ቡድኑ ድብቅ አጀንዳውን ለማስፈፀም በመራወጥ ላይ ይገኛል።

ይህ በዚህ እንዳለ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌለውን በጅዳ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ እና በኮንትራት ሰራተኞች ላይ የሚፈፀመውን ግፍ እና በደል በመዘገብ የሚታወቀውን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ጨምሮ በጅዳ እና አካባቢው የሚኖሩ የብሄሩ ተወላጅ የሃገር ሽማግሌዎችና ተዋቂ ሰዎች በዘር ሃረጋቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ የዘመቻው ስለባ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ለጥቅምት 5፣ 2015 ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ አግባብ አይደለም የሚሉ ነዋሪዎች ጥሪው በጅዳ እና አካባቢ የተፈጠረውን ውጥረት የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ ጥቂቶች የብዙሃኑን ፍቅር ለማግኘት “የቀይ ሽብር ወንጀለኞች የማጋለጥ ድራማ” የሚለይ ባለመሆኑ ከስብሰባው በፊት በኃይማኖት እና በብሄር ጥላቻ የተዘፈቀው ቡድን ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እና ከቆንስላው መታገድ እንዳለበት ይስማሙበታል። (ዘገባውን ከምስል ጋር ለጎልጉል የላኩት Ethiopian Hagere Jed Bewadi ናቸው፡፡)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule