• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” ቡድን አፍራሽ ተግባሩ ቀጥሎበታል

October 30, 2015 12:13 am by Editor Leave a Comment

በጅዳ ቆንስላ ጸ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” የተሰኘው ቡድን ጽ/ቤቱ ለሕዝብ መሥራት ከሚገባው ጉዳይ በመውጣት በግለሰቦች ማንነት እና ሃይማኖት ላይ ጽንፈኛ አቋም እየያዘ መምጣቱ ታወቀ፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት “በመልካም አስተዳደር ሽፋን” ዙሪያ ይካሄዳል ተብሎ የተጠራው አሁን ካለው የከረረ ሁኔታ አኳያ ግጭት ያስነሳል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡

በተለያዩ ሁኔታዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት “በመልካም አስተዳደር” ዙሪያ ሰሞኑን በተደረገው ግምገማ ጥቂት የደቡብ ተወካይ ነን የሚሉ ግለሰቦች አማራውን በብሄር እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በሃይማኖት በመከፋፈል የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ ጅዳ እና አካባቢዋን ስጋት ውስጥ ከቷል። በተለይ እራሱን “ወገን ለወገን” እያለ የሚጠራው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው የቆንስላ ቡድን የተካሄደውን ግምገማ ተከትሎ በቆንስላው ተገልጋይ ላይ ሲፈፀም ለነበረው በደል እና መጉላላት በቀጥታ የአማራውን ብሄር ተወላጆች ተጠያቂ በማድረግ የጀመሩትን የስም ማጥፋት ዘመቻ በማጠናከር በአካባቢያችን የሚገኙ ታዋቂ የብሄሩ አባላትና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያላቸውን ጥላቻ በመግለጽ ግምገማውን ለሌላ አጀንዳ ማስፈፀሚያ መጠቀማቸውን የቆንስላው ምንጮች ይገልጻሉ።

ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን በተገልጋዩ ችግሮች ዙሪያ ከመስራት ይልቅ ማህበረሰቡን መቋጫ ወደሌለው የእርስ በእስር ቅራኔና ግጭት ለመዝፈቅ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይናገራሉ። ቆንስላ ውስጥ የአንድ ብሄር አባል እና እምነት ተከታዮች ነጥሎ ለመምታት እየተደረገ ያለው ጥረት በአሁኑ ሰዓት ከቁጥጥር ውጭ በመሆኑ የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የጠራውን ህዝባዊ ስብሰባ ላልተወሰን ጊዜ መራዘም እንደሚገባው የሚናገሩ እነዚህ ውስጥ አዋቂዎች በመልካም አስተዳደር ሽፋን በተጠራው ስብሰባ ላይ ሊደርስ ለሚችለው ግጭት የቆንስላው ሹማምንቶች ሃላፊነቱን መውሰድ እንደሚገባቸው ያሳስባሉ። ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያቀነባበረውን ሴራ ከጀመረ አመታትን ቢያስቆጥርም፤ ሰሞኑንን ቆንስላ ውስጥ ቁልፍ ሃላፊነት ቦታ ላይ በተቀመጡ አንዳንድ ሹማምንቶች አይዟችሁ ባይነት በአዲስ መልክ ቡድኑ የጀመረው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እየደረሰ መምጣቱ ለማወቅ ተችሏል።

jedaቡድኑ እስከ ሪያድ በዘለቀው ፀረ ብሄርና ሃይማኖት ቅስቀሳው የ2008 አዲስ አመት ተከትሎ የአማራ ብሄር ተወላጆች ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ሊያከብር የነበረውን አውደ ዓመት አሳግዷል። የአማራን ብሄር ተወላጆችን ከመጠጥ እና ከሴስኝነት ጋር በማያያዝ የስም ማጥፋት ዘመቻውን ያጠናከረው ይህ ቆንስላ የመሸገው ቡድን እየፈፀመ ባለው አስነዋሪ ተግባር በአካባቢው ማህበረሰብ የሁለቱም እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።

በቪዛ ነጋዴዎችና ደላሎች የሚደገፈው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው ይህ ቡድን ቆንስላ ውስጥ በህዝባችን ላይ ለተፈፀመው በደል የቆንስላው ሹማንቶችን በሙሉ ተጠያቂ ማድረግ ሲገባው “በመልካም አስተዳደር” ሽፋን በጅዳ የአማራ ብሄር ተወላጅ እና የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነው የኢሚግሬሽን ኃላፊ ሹም በመወንጀል ቡድኑ ድብቅ አጀንዳውን ለማስፈፀም በመራወጥ ላይ ይገኛል።

ይህ በዚህ እንዳለ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌለውን በጅዳ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ እና በኮንትራት ሰራተኞች ላይ የሚፈፀመውን ግፍ እና በደል በመዘገብ የሚታወቀውን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ጨምሮ በጅዳ እና አካባቢው የሚኖሩ የብሄሩ ተወላጅ የሃገር ሽማግሌዎችና ተዋቂ ሰዎች በዘር ሃረጋቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ የዘመቻው ስለባ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ለጥቅምት 5፣ 2015 ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ አግባብ አይደለም የሚሉ ነዋሪዎች ጥሪው በጅዳ እና አካባቢ የተፈጠረውን ውጥረት የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ ጥቂቶች የብዙሃኑን ፍቅር ለማግኘት “የቀይ ሽብር ወንጀለኞች የማጋለጥ ድራማ” የሚለይ ባለመሆኑ ከስብሰባው በፊት በኃይማኖት እና በብሄር ጥላቻ የተዘፈቀው ቡድን ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እና ከቆንስላው መታገድ እንዳለበት ይስማሙበታል። (ዘገባውን ከምስል ጋር ለጎልጉል የላኩት Ethiopian Hagere Jed Bewadi ናቸው፡፡)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule