• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መንግሥት ከደላሎች ጋር አይደራደርም” ኃይለማርያም

December 26, 2014 01:02 am by Editor Leave a Comment

ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት መንግስት በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በኢትዮጵያውያን ላይ የተከሰተውን ስቃይ እና በደል ተከትሎ ለስራ ወደ አረብ ሀገራት በሚደረግ ጉዞ ላይ እገዳ መጣሉ ይታወሳል። በተለይ ያለአንዳች የህይወት ዋስትና ወደ ተጠቀሱት ሃገራት በኮንትራት የሚሄድ ሰራተኞችን ከገጠር እስከ ከተማ በዘለቀ ድለላ ህጋዊ ፈቃድ አግኝተው ዜጎችን እያጋዙ የነበሩ የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ባለቤት ቢሮዎች መዘጋታቸው አይዘነጋም። ዘግይቶም ቢሆን መንግስት በወቅቱ ወሰደ በተባለው እርምጃ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ህይወት ከአስከፊው የአረብ ዓለም ስቃይ  መታደግ ቢችልም ከግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎቻችንን ህይወት ስላለበት ሁኔታ የተጠቀሱትን የኤጀንሲ ባለቤቶች በህግ ለመሞገት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ቴድሮስ አድሃኖም የገቡትን ቃል መተግበር አለመቻላቸው ብዙዎችን አሳዝኖል።

ይህ በዚህ እንዳለ ሰሞኑን በዚህ ዙሪያ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የቀረበው ረቂቅ  ተስፋ ተጥሎበት የነበረውን የዜጎች ደህነነት የማስጠበቅ እርምጃ መቅኔ አስጥቶት መንግስት ከኤጀንሲ ባለቤቶች ጋር በሌላ አቅጣጫ እየደረገ ያለው ድርድር በስረዓቱ በባለስልጣናት ዘንድ በዚህ ዙሪያ አንድ አቋም  አለመኖሩ  ይነገራል። ከዚህ ቀደም በሁለት ሃገራት መካከል ስምምነትና በቂ ዝግጅት ሳይደረግ በሳውዲ ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ዜጋ ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው ኤጀንሲዎች በየገጠር ከተሞች ተግዘው “ያሉበትን ይዞታ እንዲህ ነው” ብሎ መረጃ መስጠት ቀርቶ፣ የትና በምን ሁኔታ እንደሚገኙ የሚያውቅ ኤጀንሲም ሆነ የመንግስት ተወካይ በሌለበት መንግስት  ከተጠቀሱት ወንጀለኞች ጋር በዜጎች ህይወት መደራደሩ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር መሆኑን ታዛቢዎች ይገልጻሉ፡፡

ሰሞኑንን ለሃገር ውስጥ ጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ጠ/ሚ/ር ሐይለማርያም ደሳለኝ መንግስታቸው ከደላሎች ጋር እንደማይዋዋል ቢያረጋግጡም እነዚህ ወገኖች በተለያዩ የመንግስት መዋቅሮች ውስጥ ሰርገው በመግባት የአንዳንድ ደካማ ባለስልጣናት  እጅ በመጠምዘዝ መንግስት ከደላሎች ጋር እንዲደራደር ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸው ታውቋል። አብዛኛዎቹ የኤጀንሲ ባለቤቶች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጭምር  በጥቅም የተቆራኙ ከመሆናቸውም በላይ ከልማት ማህበራት አንስቶ የኢህአዴግ አባል መሆን የሚያስችላቸውን መታወቂያ ካርድ በመውሰድ በህዝብ ሰም እየማሉ የአዞ እንባ በማንባት ከልካይ በሌለበት እንሱ ፈላጭ ቆራጭ በሆኑበት ስረአት ውስጥ በዜጎቻችን ህይወት መክበራቸው ይታወቃል።

በዋንኛነት መቀመጫቸውን ሳውዲ አረቢያ ጅድ እና ሪያድ ከተማ ያደረጉ እነዚህ ወገኖች ከዲፕሎማቱ ጋር ባላቸው የእከክለኝ ልከክለህ ወዳጅነት ሲሻቸው በቆንስላው ቢሮ በመፈንጨት መብቴ ይከበርልኝ ያለውን ዜጋ ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በመፈረጅ ምንም አይነት ስለነሱ ምንም እንዳይተነፍስ በማስፈራራት ሲሻቸው በህገወጥ የሃዋላ ንግድ በፍረጠመው ጡንቻቸው በጠራራ ጸሃይ የሃይል ጥቃት ለመፈጸም ይቃጣቸዋል።  የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ባለቤቶችን ያስከፋው ሰሞነኛው የጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም መግለጫ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውሩ በተለይ ወጣቶች የተሳሳተ መረጃ ተስፋ ሰንቀው እዚያ ላይ ተሰማርቼ ማጨድ አለብኝ በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ መሆኑን አውስተው አንዳንድ ሰዎች ይህ ፍልሰት የበዛው ወደ አንዳንድ የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሚደረገው ጉዞ በመከልከሉ ምክንያት ነው የሚለውን ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በመሞገት ዜጎች በህጋዊ መንገድ መጓዝ በአውሮፕላን ሆነ እንጂ ከዚያኛው የሕገወጥ ጉዞ አንደማይሻልና  አስረድተዋል። ጠ/ሚ/ሩ በማያያዝ ሃሳብቸውን ሲያጠናክሩ የዜጎች ህይወት በአስተማማኝ መልኩ ሊጠበቅ የሚችለው ከደላሎች ጋር በመደራደር ሳይሆን ከመንግሥታት ጋር ስምምነት ሲኖር ብቻ መሆኑን ደግመው አረጋግጠዋል፡፡

እስካሁን እልባት ባላገኘው የአረብ ሃገር ኮንትራት ሰራተኞች ጉዞ የህይወት ዋስትና ጉዳይ በተለያዩ ጊዜያቶች በኢህአዴግ ባለስልጣናት ዘንድ የሚሰጠው መግለጫ እርስ በእርሱ የተጣረዘ መሆኑን የሚናገሩ ታዛቢዎች የሰራተኛ እና አሰሪ አገናኝ ኤጀንሲ ባለቤቶች እንደወትሮው ቢሮቻቸውን ከፈተው በዜጎች ንግድ ላይ ለመሰማራት በማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካኝነት በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ይህ ይጨመር አሊያም ይቀነስ በማለት እየተዋዋሉ ባሉበት ሁኔታ መንግስቴ ከደላሎች ጋር አይደራደረም  የሚለው የጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ መግለጫ ግልጽነት የሌለው እና አብዛኛውን ወገን ግራ ያጋባ መሆኑ ይነገራል።

Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule