• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐመር አርብቶ አደሮችና የፖሊስ ግጭት ወቅታዊ መረጃ

January 22, 2015 12:10 am by Editor Leave a Comment

በጥር 7/2007 ሐሙስ ዕለት በሐመር ወረዳ በ”ላላ” ቀበሌ በሐመር ብሔረሰብ አርብቶ አደሮችና ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የደረሰዉ ጉዳት የሚከተለዉን ይመስላል፤
ሀ/ የሞቱ–

1. ሻምበል ለማ አሸናፊ
2/ ወ/ር ሙሴ ማቱሳላ
3/ ወ/ር ደፋሩ ጦና
4/ ወ/ር ካሬ
5/ ወ/ር በኃይሉ
6/ ስሙ ለግዜዉ ያልታወቀ የልዩ ኃይል ባልደረባ
7/ ስሙዋ ለግዜዉ ያልታወቀ ሴት ባለሙያ
8/መምህር መሳይ ነሽ መርነህ

ለ/ የቆሰሉ

1/ አቶ ቹሜሬ የረር /የደቡብ ኦሞ ዞን ፍትህ ጸጥታና ደንብ ማስከበር ምክትል ሀላፊ
2/ ምክትል ሣጅን ጌታሁን ቶላ
3/ ወ/ር ተሰማ መሰረት
4/ ወ/ር ጌታቸዉ ጻንቃ
5/ ወ/ር ቱላ ኪያ
6/ ባሻ ወንድማገኝ ጨነቀ
7/ ወ/ር ሚልኪያስ ግራኝ
8/ ወ/ር ዘለቀ (አባታቸዉ ያልታወቀ)
9/ አቶ ደምሳሽ ሞላ (የዞኑ ሴቶችና ሕጻናት መምርያ ሾፌር)

የሐመር ወረዳ ፍትህ ጸጥታና ደንብ ማስከበር ሃላፊ ኮማንደር ቡራ ካሎ የኦፕሬሽኑ አዛዥ ሲሆኑ ትእዛዝ የሚሰጡት ዲመካ ሁነዉ መሆኑንም ከስፍራዉ ከነበሩ መረዳት ተችሏል፡፡ በአርብቶአደሩ በኩል ስለደረሰው ጉዳት መረጃ ለማግኘት አልተቻለም፡፡
ከዞኑ መስተዳድር የውስጥ ምንጮች በደረሰን መረጃ መሰረት በነገው ዕለት የዞኑ ሲቪል ሠራተኞች ከስከሬን አንሺ የቀን ሠራተኞች ይዘው ወደ ቦታው በመሄድ አሰከሬኖችን ለማምጣት እንደሚንቀሳቀሱና በዚህ ጉዞም ወታደራዊ ኃይል እንዳይኖር/እንዳያጅባቸው መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በአሁኑ ሰዓት በሃመር ወረዳ ዋና ከተማ ዲመካ ምንም የፖሊስ ኃይል ለመኖሩና አንዳንድ የወረዳውና ከዞኑ የተንቀሳቀሱ ፖሊሶች የፖሊስ ልብሳቸውን በመቀየር/ከአካባቢው ሲቪል ሠራተኞች በመውሰድ/ በእግር ጫካ ለጫካ በመጓዝ ከዞኑ ከተማ ጂንካ መድረሳቸውንና የከተማው ነዋሪም ‹‹እንኳን ለቤታችሁ አበቃችሁ›› እያለ እየጠየቃቸው እንደሆነና እነርሱም ‹‹ በማናውቀው አስገብተውን ሊያስቸርሱን ነበር፣ የተፈጠረው ሁኔታና በወንድሞቻችን ላይ የደረሰው በእጅጉ አሳዛኝ ነው›› በሚል ቁጭታቸውን ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡ የከተማው ነዋሪዎችና ከቦታው ተመላሾች ኢሣት መረጃውን ለኢትዮጵያዊያን በማድረሱ ባለውለታችን ነው በማለት ሲያመሰግኑ ተደምጠዋል፡፡

የግጭቱ ምክንያቶች ብዙ ቢሆኑም የሚከተሉት በስፋት በአርብቶ-አደሩ የሚነሱ ናቸዉ፤

ወቅታዊው/ኢሚዲየት/ መነሻው የወረዳው ፖሊስ በለመደው መንገድ የአካባቢውን ባህላዊ አባቶች በ‹‹ንቀት›› አልፎ የሀመር ወጣቶች ላይ ኃይሉን ለማሳየት ያደረገው ሙከራ ቢሆንም–

1/ በአካባቢዉ ስም ከመነገዱ ውጪ ያየነዉ ለዉጥ ባለመኖሩ ሐመር ከ23 አመት በፊት በነበርንበት መገኘታችን፤
2/ እኛን ባላማከሩበት የግጦሽና ውኃ ማጠጫ ቦታችንን ከፓርኩ ክልል አስገብተው ባለበት አርብቶ አደርነታችን እየታወቀ ለከብቶቻችን ዘመናዊ የግጦሽ ስፍራ ሳይዘጋጅልን በበጋ ወደ ፓርክ ለግጦሽና ለዉሃ እንዳናስገባ መደረጉ ሀብቶቻችንን እንድናጣ መገደዳችን፤
3/ የወረዳዉ ፖሊስ አዛዥ መቶ አለቃ ጋዲ በርቂ በመኪና ገጭተዉ በገደሉት ሀመር በህግ አለመጠየቃቸዉ፤በተመሳሳይ ወ/ር ዋዶ የተባሉ ሀመሩን ደረቱ ላይ ረግጠዉ ሲገሉ በህግ አለመጠየቃቸዉ፣በተቃራኒው ደግሞ በቂ ዕውቀትና መረጃ የሌለዉ የሀመር እረኛ ጎሽ ገደለ ተብሎ ወህኒ መወርወሩ፤ የኛ ሰውነት ከእንሰሳ/ጎሽ ያነሰ ተደርጎ በራሳችን ልጆች ጭምር መታየቱ፤…. የሚሉት በህዝቡ ውስጥ ይብላሉ የነበሩና በተደጋጋሚ ተነስተው ምላሽ የተነፈጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡

በተፈጠረው ሁኔታ በወረዳው ብቻም ሳይሆን በዞኑ ውጥረትና ያለመረጋጋት ነግሷል፣የተፈጠረው ችግር መቼና እንዴት መፍትሄ እንደሚያገኝ አይታወቅም፣የማኅበራዊ አገልግሎት ተቋማት አገልግሎት አቋርጠዋል፡፡ አስቸኳይ አሳታፊ መፍትሄ ካለገኘም የመስፋትና መዛመት ዕድሉ ሰፊ እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ሥጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ድርጅታችን የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/ ባለፉት 23 ዓመታት በዞኑ ያለውን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንና ምስቅልቅል በአጠቃላይ፣ በተለይም በየጊዜው በዞኑ ነዋሪዎች የሚነሱ ጥያቄዎችንና እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን የመሳሰሉ የአርብቶአደሩን ጥያቄዎችና በዞኑ ያለጥናት የሚደረጉ ሰፈራዎችን እንዲሁም ከስኳር ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የሚደረጉ የህዝብ ማፈናቀሎችንና ይህንኑ ተከትሎ የሚነሱ ጥያቄዎችን መንግሥት በአግባቡና የአካባቢውን ባህላዊና አካባቢያዊ ግጭት አፈታት ዘዴዎችን ባገናዘበ መንገድ መልስና መፍትሄ እንዲሰጠቸው፣በመሣሪያ ኃይል ጥያቄዎችን ለማፈን የሚደረገው ሙከራ ዘላቂ መፍትሄ ካለማስገኘቱም ግጭት ሊያስከትል እንደሚችል በተደጋጋሚ ለዞኑ መንግሥት ባለሥልጣናት ስንገልጽ ለችግሮቹ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ ጥያቄዎቹን በማንሳታችን ሊያስፈራሩና ሊወነጅሉ ሲሞክሩ ተመልክተናል፡፡ የዚህ አካሄድና አስተሳሰብ የመጨረሻ ውጤቱ ይህ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ድርጅታችን መንግሥት–

1. በግጭቱ ስለደረሰው ጉዳት መጠንና ዓይነት/ የሰው ህይወት፣አካል ጉዳት…/፣የንብረት ውድመት፣…. ላይ በቂ መረጃ እንዲሠጥና የድርጊቱ አዛዞች፣ፈጻሚዎች….ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፤
2. በግጭቱ ለተጎዱ ወገኖችና ለደረሰው የንብረት ውድመት ካሳ እንዲከፍል፤
3. ግጭቱ ከመጪው ምርጫ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ስለሆነ አፋጣኝ አሳታፊ መፍትሄው እንዲፈልግለት፤የፖሊስ ተግባራትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ወደቦታቸው/ተግባራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርግ፣
4. ለችግሩ ሥረ-መንስኤዎች ሕብረተሰቡን ያሳተፈና በማኅበረሰቡ ተቀባይነት ያለው አካባቢያዊ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያበጅና ችግሩ እንዳይባባስና እንዳይስፋፋ አስቸኳይ የማረጋጋት እርምጃ እንዲወስድ፤
የማንአለብኝነት ኃይል እርምጃ መቼውንም መፍትሄ አይሆንምና ለቀጣይም መንግሥት ከዚህ ዓይነቱ አካሄድ እንዲታቀብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule