• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐመር አርብቶ አደሮችና የፖሊስ ግጭት ወቅታዊ መረጃ

January 22, 2015 12:10 am by Editor Leave a Comment

በጥር 7/2007 ሐሙስ ዕለት በሐመር ወረዳ በ”ላላ” ቀበሌ በሐመር ብሔረሰብ አርብቶ አደሮችና ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የደረሰዉ ጉዳት የሚከተለዉን ይመስላል፤
ሀ/ የሞቱ–

1. ሻምበል ለማ አሸናፊ
2/ ወ/ር ሙሴ ማቱሳላ
3/ ወ/ር ደፋሩ ጦና
4/ ወ/ር ካሬ
5/ ወ/ር በኃይሉ
6/ ስሙ ለግዜዉ ያልታወቀ የልዩ ኃይል ባልደረባ
7/ ስሙዋ ለግዜዉ ያልታወቀ ሴት ባለሙያ
8/መምህር መሳይ ነሽ መርነህ

ለ/ የቆሰሉ

1/ አቶ ቹሜሬ የረር /የደቡብ ኦሞ ዞን ፍትህ ጸጥታና ደንብ ማስከበር ምክትል ሀላፊ
2/ ምክትል ሣጅን ጌታሁን ቶላ
3/ ወ/ር ተሰማ መሰረት
4/ ወ/ር ጌታቸዉ ጻንቃ
5/ ወ/ር ቱላ ኪያ
6/ ባሻ ወንድማገኝ ጨነቀ
7/ ወ/ር ሚልኪያስ ግራኝ
8/ ወ/ር ዘለቀ (አባታቸዉ ያልታወቀ)
9/ አቶ ደምሳሽ ሞላ (የዞኑ ሴቶችና ሕጻናት መምርያ ሾፌር)

የሐመር ወረዳ ፍትህ ጸጥታና ደንብ ማስከበር ሃላፊ ኮማንደር ቡራ ካሎ የኦፕሬሽኑ አዛዥ ሲሆኑ ትእዛዝ የሚሰጡት ዲመካ ሁነዉ መሆኑንም ከስፍራዉ ከነበሩ መረዳት ተችሏል፡፡ በአርብቶአደሩ በኩል ስለደረሰው ጉዳት መረጃ ለማግኘት አልተቻለም፡፡
ከዞኑ መስተዳድር የውስጥ ምንጮች በደረሰን መረጃ መሰረት በነገው ዕለት የዞኑ ሲቪል ሠራተኞች ከስከሬን አንሺ የቀን ሠራተኞች ይዘው ወደ ቦታው በመሄድ አሰከሬኖችን ለማምጣት እንደሚንቀሳቀሱና በዚህ ጉዞም ወታደራዊ ኃይል እንዳይኖር/እንዳያጅባቸው መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በአሁኑ ሰዓት በሃመር ወረዳ ዋና ከተማ ዲመካ ምንም የፖሊስ ኃይል ለመኖሩና አንዳንድ የወረዳውና ከዞኑ የተንቀሳቀሱ ፖሊሶች የፖሊስ ልብሳቸውን በመቀየር/ከአካባቢው ሲቪል ሠራተኞች በመውሰድ/ በእግር ጫካ ለጫካ በመጓዝ ከዞኑ ከተማ ጂንካ መድረሳቸውንና የከተማው ነዋሪም ‹‹እንኳን ለቤታችሁ አበቃችሁ›› እያለ እየጠየቃቸው እንደሆነና እነርሱም ‹‹ በማናውቀው አስገብተውን ሊያስቸርሱን ነበር፣ የተፈጠረው ሁኔታና በወንድሞቻችን ላይ የደረሰው በእጅጉ አሳዛኝ ነው›› በሚል ቁጭታቸውን ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡ የከተማው ነዋሪዎችና ከቦታው ተመላሾች ኢሣት መረጃውን ለኢትዮጵያዊያን በማድረሱ ባለውለታችን ነው በማለት ሲያመሰግኑ ተደምጠዋል፡፡

የግጭቱ ምክንያቶች ብዙ ቢሆኑም የሚከተሉት በስፋት በአርብቶ-አደሩ የሚነሱ ናቸዉ፤

ወቅታዊው/ኢሚዲየት/ መነሻው የወረዳው ፖሊስ በለመደው መንገድ የአካባቢውን ባህላዊ አባቶች በ‹‹ንቀት›› አልፎ የሀመር ወጣቶች ላይ ኃይሉን ለማሳየት ያደረገው ሙከራ ቢሆንም–

1/ በአካባቢዉ ስም ከመነገዱ ውጪ ያየነዉ ለዉጥ ባለመኖሩ ሐመር ከ23 አመት በፊት በነበርንበት መገኘታችን፤
2/ እኛን ባላማከሩበት የግጦሽና ውኃ ማጠጫ ቦታችንን ከፓርኩ ክልል አስገብተው ባለበት አርብቶ አደርነታችን እየታወቀ ለከብቶቻችን ዘመናዊ የግጦሽ ስፍራ ሳይዘጋጅልን በበጋ ወደ ፓርክ ለግጦሽና ለዉሃ እንዳናስገባ መደረጉ ሀብቶቻችንን እንድናጣ መገደዳችን፤
3/ የወረዳዉ ፖሊስ አዛዥ መቶ አለቃ ጋዲ በርቂ በመኪና ገጭተዉ በገደሉት ሀመር በህግ አለመጠየቃቸዉ፤በተመሳሳይ ወ/ር ዋዶ የተባሉ ሀመሩን ደረቱ ላይ ረግጠዉ ሲገሉ በህግ አለመጠየቃቸዉ፣በተቃራኒው ደግሞ በቂ ዕውቀትና መረጃ የሌለዉ የሀመር እረኛ ጎሽ ገደለ ተብሎ ወህኒ መወርወሩ፤ የኛ ሰውነት ከእንሰሳ/ጎሽ ያነሰ ተደርጎ በራሳችን ልጆች ጭምር መታየቱ፤…. የሚሉት በህዝቡ ውስጥ ይብላሉ የነበሩና በተደጋጋሚ ተነስተው ምላሽ የተነፈጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡

በተፈጠረው ሁኔታ በወረዳው ብቻም ሳይሆን በዞኑ ውጥረትና ያለመረጋጋት ነግሷል፣የተፈጠረው ችግር መቼና እንዴት መፍትሄ እንደሚያገኝ አይታወቅም፣የማኅበራዊ አገልግሎት ተቋማት አገልግሎት አቋርጠዋል፡፡ አስቸኳይ አሳታፊ መፍትሄ ካለገኘም የመስፋትና መዛመት ዕድሉ ሰፊ እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ሥጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ድርጅታችን የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/ ባለፉት 23 ዓመታት በዞኑ ያለውን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንና ምስቅልቅል በአጠቃላይ፣ በተለይም በየጊዜው በዞኑ ነዋሪዎች የሚነሱ ጥያቄዎችንና እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን የመሳሰሉ የአርብቶአደሩን ጥያቄዎችና በዞኑ ያለጥናት የሚደረጉ ሰፈራዎችን እንዲሁም ከስኳር ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የሚደረጉ የህዝብ ማፈናቀሎችንና ይህንኑ ተከትሎ የሚነሱ ጥያቄዎችን መንግሥት በአግባቡና የአካባቢውን ባህላዊና አካባቢያዊ ግጭት አፈታት ዘዴዎችን ባገናዘበ መንገድ መልስና መፍትሄ እንዲሰጠቸው፣በመሣሪያ ኃይል ጥያቄዎችን ለማፈን የሚደረገው ሙከራ ዘላቂ መፍትሄ ካለማስገኘቱም ግጭት ሊያስከትል እንደሚችል በተደጋጋሚ ለዞኑ መንግሥት ባለሥልጣናት ስንገልጽ ለችግሮቹ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ ጥያቄዎቹን በማንሳታችን ሊያስፈራሩና ሊወነጅሉ ሲሞክሩ ተመልክተናል፡፡ የዚህ አካሄድና አስተሳሰብ የመጨረሻ ውጤቱ ይህ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ድርጅታችን መንግሥት–

1. በግጭቱ ስለደረሰው ጉዳት መጠንና ዓይነት/ የሰው ህይወት፣አካል ጉዳት…/፣የንብረት ውድመት፣…. ላይ በቂ መረጃ እንዲሠጥና የድርጊቱ አዛዞች፣ፈጻሚዎች….ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፤
2. በግጭቱ ለተጎዱ ወገኖችና ለደረሰው የንብረት ውድመት ካሳ እንዲከፍል፤
3. ግጭቱ ከመጪው ምርጫ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ስለሆነ አፋጣኝ አሳታፊ መፍትሄው እንዲፈልግለት፤የፖሊስ ተግባራትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ወደቦታቸው/ተግባራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርግ፣
4. ለችግሩ ሥረ-መንስኤዎች ሕብረተሰቡን ያሳተፈና በማኅበረሰቡ ተቀባይነት ያለው አካባቢያዊ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያበጅና ችግሩ እንዳይባባስና እንዳይስፋፋ አስቸኳይ የማረጋጋት እርምጃ እንዲወስድ፤
የማንአለብኝነት ኃይል እርምጃ መቼውንም መፍትሄ አይሆንምና ለቀጣይም መንግሥት ከዚህ ዓይነቱ አካሄድ እንዲታቀብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule