• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሚዩኒክ ጀርመን የወያኔ የአባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ ተስተጓጎለ

November 3, 2013 09:22 am by Editor Leave a Comment

እ.ኤ.አ. ቅዳሜ ኖቬምበር 02, 2013 ዓ.ም. በጀርመን ሚዩኒክ ከተማ ወያኔ ሊያደርግ ያሰበው የአባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች በተሰበሰቡ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ሊከሽፍ ችሏል።

ከዚህ በፊት በጀርመን ፍራንክፈርት ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ከተሞች እክል የገጠመው የወያኔ የቦንድ ሽያጭ ኮሚቴ አካሄዱን በመቀየር የቦንድ ሽያጩ ይጀመራል ተብሎ ከታሰበበት ጊዜ ሶስት ሰዓት ያህል በማዘግየት ለተቃውሞ የመጡትን ሰዎች ተስፋ ለማስቆረጥ ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ ከመቅረቱም በላይ በወቅቱ በነበረው ቅዝቃዜና ብርድ ሳይበገሩ የፕሮግራሙን መጀመር በትዕግስት በቅርብ ርቀት የተከታተሉት እነዚህ ተቃዋሚዎች የመግቢያ ትኬት ሽያጭ ሲጀመር germany2በአንድ ጊዜ ቁጥራቸው ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ የኦነግ አባላት፣የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አባላት፣የኢህአፓ አባላት፣የ‘‘ድምፃችን ይሰማ‘‘ ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አስተባባሪነት በር ላይ የነበሩ የወያኔ የደህንነት ሰዎችን በመጣስ ወደ አዳራሹ የገቡ ሲሆን በወቅቱ የመግቢያው በር ላይ በተፈፀመ ግርግር የሚዩኒክ ፖሊሶች በስፍራው በመገኘት የወያኔ ደህንነቶችን ከመደብደብ ታድገዋል።

በአዳራሹ ውስጥ ለገቢ ማሰባሰቢያ በሚል ተዘጋጅቶ የነበረ ምግብ እንዲሁም ከለስላሳ መጠጦች እስከተለያዩ ዊስኪዎችና ቮድካዎች የነበሩ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ ‘‘የሀገራችን ንብረት ነው‘‘ በማለት ከምግቡም ከመጠጡም በመቋደስ ወያኔ በተከራየው አዳራሽ ውስጥ ለሁለት ሰዓታት ያህል በወቅታዊ የሀገራችን ሁኔታ በተለይም በዜጎች ላይ እየደረሰ ባለው አፈናና እንግልት፣የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣የእምነት ነፃነት አለመከበርና በመሳሰሉት ላይ ውይይት በማካሄድ እንዲሁም ወያኔ በኢትዮጵያ ውስጥ እየፈፀመ የሚገኘውን አፈናና የግፍ አገዛዝ በአባይ ግድብ እና በልማት ስም ለመሸፈን የሚያደርገውን መሠሪ ተግባር በማውገዝ ተጠናቋል።

(በየነ መስፍን ከጀርመን)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule