• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሚዩኒክ ጀርመን የወያኔ የአባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ ተስተጓጎለ

November 3, 2013 09:22 am by Editor Leave a Comment

እ.ኤ.አ. ቅዳሜ ኖቬምበር 02, 2013 ዓ.ም. በጀርመን ሚዩኒክ ከተማ ወያኔ ሊያደርግ ያሰበው የአባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች በተሰበሰቡ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ሊከሽፍ ችሏል።

ከዚህ በፊት በጀርመን ፍራንክፈርት ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ከተሞች እክል የገጠመው የወያኔ የቦንድ ሽያጭ ኮሚቴ አካሄዱን በመቀየር የቦንድ ሽያጩ ይጀመራል ተብሎ ከታሰበበት ጊዜ ሶስት ሰዓት ያህል በማዘግየት ለተቃውሞ የመጡትን ሰዎች ተስፋ ለማስቆረጥ ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ ከመቅረቱም በላይ በወቅቱ በነበረው ቅዝቃዜና ብርድ ሳይበገሩ የፕሮግራሙን መጀመር በትዕግስት በቅርብ ርቀት የተከታተሉት እነዚህ ተቃዋሚዎች የመግቢያ ትኬት ሽያጭ ሲጀመር germany2በአንድ ጊዜ ቁጥራቸው ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ የኦነግ አባላት፣የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አባላት፣የኢህአፓ አባላት፣የ‘‘ድምፃችን ይሰማ‘‘ ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አስተባባሪነት በር ላይ የነበሩ የወያኔ የደህንነት ሰዎችን በመጣስ ወደ አዳራሹ የገቡ ሲሆን በወቅቱ የመግቢያው በር ላይ በተፈፀመ ግርግር የሚዩኒክ ፖሊሶች በስፍራው በመገኘት የወያኔ ደህንነቶችን ከመደብደብ ታድገዋል።

በአዳራሹ ውስጥ ለገቢ ማሰባሰቢያ በሚል ተዘጋጅቶ የነበረ ምግብ እንዲሁም ከለስላሳ መጠጦች እስከተለያዩ ዊስኪዎችና ቮድካዎች የነበሩ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ ‘‘የሀገራችን ንብረት ነው‘‘ በማለት ከምግቡም ከመጠጡም በመቋደስ ወያኔ በተከራየው አዳራሽ ውስጥ ለሁለት ሰዓታት ያህል በወቅታዊ የሀገራችን ሁኔታ በተለይም በዜጎች ላይ እየደረሰ ባለው አፈናና እንግልት፣የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣የእምነት ነፃነት አለመከበርና በመሳሰሉት ላይ ውይይት በማካሄድ እንዲሁም ወያኔ በኢትዮጵያ ውስጥ እየፈፀመ የሚገኘውን አፈናና የግፍ አገዛዝ በአባይ ግድብ እና በልማት ስም ለመሸፈን የሚያደርገውን መሠሪ ተግባር በማውገዝ ተጠናቋል።

(በየነ መስፍን ከጀርመን)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule