• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከህወሃት የአናሳዎች ቁማር ጨዋታ ይጠንቀቁ!!

September 27, 2016 08:46 pm by Editor 2 Comments

በቅርቡ ብዙዎቻችሁ እንደተመለከታችሁት፣ ህወሃት ሶማሊዎች ኦነግን ወይም ግንቦት ሰባትን በመቃወም ወጡ የሚል ፕሮፓጋንዳ እየነዛ ነው። መታወቅ ያለበት እውነት እንዲህ ዓይነቱን የህወሃት ድራማ እየተጫወቱ ያሉት ክልሉን አስተዳድራለው የሚለው አሻንጉሊት ፓርቲ አባላት ብቻም ሳይሆኑ፣ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ፣ ከሶማሊ ላንድ እንዲሁም ከኬኒያ የመጡ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች መሆናቸውን ነው።

እብደት፣ ንዝላልነትና ስርዓት አልበኝነት የተጠናወተው የክልሉ የህወሃት ቅጥረኛ ፕሬዚዳንት አብሲ ኢሌ፣ ዛሬ የቡና ቤት ሰራተኞች ሳይቀር በማስገደድ ሰልፍ አስወጥቷል። የህወሃት አገዛዝ ይህንን ለምን አደረገ?

በመጀመሪያ ይህ የሚያሳየው ህወሃት በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ባበጃቸው ታዛዥና አሻንጉሊት የነበሩ ፓርቲዎችም ጭምር ሳይቀር መተፋቱንና ተስፋ መቁረጡን ነው። በነዚህ ሁለት ትልልቅ ክልሎች (ኦሮሚያና አማራ) ስርዓቱ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ ቢጠራም አንድም ወደ ተቃውሞ ይቀየራሉ በሚል ስጋት ሰርዟቸዋል ወይም ደግሞ ማንም ሰው ባለመገኘቱ የድጋፍ ሰልፎቹ ከሽፈዋል።

ጉዳዩ ግን ከዚህም በላይ ክፉ (sinister) እሳቤ ያለበት ነው። ጉዳዩ ህወሃቶች የሞት ሽረት ትግል (existential fight) የሚያደርጉበት የአናሳዎች (minority) ፖለቲካዊ ቁማር ጨዋታ አካል ነው። የዚህ ዓይነቱን ቆሻሻ ቁማር ካርድ ከሁለት ሳምንታት በፊት ስዩም መስፍንና አባይ ጸሃዬ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ መዝዘውት ነበር። ይሄን ለማድረግ ሁለት ተልዕኮ ነበራቸው፥

የመጀመሪያው፣ ከዓለምዓቀፉ ዳተኛ ማህበረሰብ (liberal international community) “ትግሬዎች ላይ በሁለቱ ትልልቅ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች (ኦሮሞና አማራ) አጋርነት የዘር ማጥፋት ዘመቻ እየተካሄደ ነው” በሚል የድረሱልን ጥሪ ለማስተላለፍ ተፈልጎ ነው። ወያኔዎች ለዓለምዓቀፍ ዲፕሎማቶች “ትግሬ ብቻ ሳይሆን ሌሎች የሃገሪቱ አናሳ ቡድኖችም ጭምር ለጥቃት እየጠጋለጡ ነው” በሚል ከፍተኛ አቤቱታና ውትወታ እያቀረቡ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።

ሁለተኛው ምክንያት ግን ህወሃት ከበረሃ አንስቶ ሲሰራበት የነበረውና የኦሮሞንና የአማራን የተባበረ ጫና (concerted impact) ለመቋቋም ሌሎች የሃገሪቱን አናሳ ቡድኖች አደራጅቶና በነሱ ላይ የበላይ ሆኖ (ዶሚኔት አድርጎ) ማንቀሳቀስ የሚለው ሸፍጠኛ ፖሊሲው ነው። ይሄ ከትግሉ ዘመን ጀምሮ ሲያራምዱት የነበረ ስትራቴጂ ነው። ትግራይን ከቤኒሻንጉልና በምዕራብ ታች ጋምቤላ ድረስ ወርዶ እንዲሁም በምስራቅ በኩል በአፋርና ሶማሌ ላይ የሚያገናኘው ካርታ የተሰራው በተራ ስህተት ሳይሆን ከ1970ቹ ጀምሮ ታቅዶ የተሰራበት ፕሮጀክት ነው። በትግራይ ልሒቃን የኢኮኖሚ ስግብግብነት የተነሳ ባይሳካላቸውም፣ በከተሞች ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ አናሳ ቡድኖችንም ከጎናቸው ለማሰለፍ ህወሃቶች ጥረው ነበር።

በእርግጥ ግን ህወሃት በኢትዮጵያ የአናሳ ቡድኖች አጋር ነውን? ስራው የሚያሳየው ግን እንዳልሆነ ነው። ምሳሌዎችን እንጥቀስ፥

+ የህወሃት ሰራዊት በሶማሊ ክልል ዘር ማጥፋትን ጨምሮ ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽሟል። ይሄንን አሰቃቂ ወንጀል ደግሞ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በሰፊው የዘገቡት ሲሆን ያሁኑ የክልሉ ፕሬዚደንት አብዲ ኢሌ በቅጥረኛ ነፍሰገዳይነት እንደተባበረ እልፍ አእላፍ መረጃዎች አሉ።

+ በ2003 በጋምቤላ ክልል በአኙዋኮች ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ያካሄደ ሲሆን፣ ይሄንኑ ዓይነት ጭፍጨፋ እስካሁንም ቀጥሎበታል።

+ በ2002 ሎቄ ላይ ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ሲዳማዎች ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አካሂዷል።

+ አሁን በዚህ ወቅት እንኳን የኮንሶ ህዝብ ራስን በራስ ለማስተዳደር ስለጠየቀ ብቻ የህወሃት ሠራዊት መንደሮቹን በእሳት እያጋየ ነው።

+ ሙርሲዎችን በገፍ ገድሏል፣ የተቀሩትን ደግሞ እንደ ጥንት ዘመን ባሮች አጠላልፎ በማሰር የሰው ልጅ በዚህ ዘመን ሊያየው በማይገባ ሁናቴ አስሮ እያሰቃያቸው ነው።

+ የስልጤና ጉራጌ ነጋዴዎችን ከንግድ ስርዓቱ በማስወጣት በትግሬዎች ተክቷል።

+ የአፋርን መሬት ትግሬዎች መቀራመት ብቻም ሳይሆን ሲፈልጉም የሱማሌ ኢሳዎችና ሌሎች እንዲቀራመቱት አድርገዋል።

+ ወዘተርፈ……

በሚቀጥሉት ሳምንታትና ወራት የኦሮሞና የአማራ አክቲቪስቶችና የነጻነት ቀንዲሎች የተባበረ ክንዶቻቸውን ማሳረፍ ሲቀጥሉ፣ ህወሃት የአናሳዎችን ቁማር ካርድ ይበልጥ እንደምትመዝ ይጠበቃል። የዚህ ዓይነቱ አስነዋሪ ቁማር ደግሞ በኢትዮጵያ ባሉት ሌሎች አናሳ በሔረሰቦች እንዲሁም በኦሮሞና በአማራ መካከል ቅራኔና ቁርሾ ለመፍጠር ያለም ነው የሚሆነው።

በዚሁ መሰረት ወያኔ ከዚህ ቀጥሎ የተጠቀሱትን እኩይ ተግባራት ለመፈጸም ይችላልና እንንጠቀቅ፥

+ በዳያስፖራም ሆነ በተወሰኑ ያገር ውስጥ አካባቢዎች ተመሳሳይ የሆኑ ኦሮሞንና አማራን ለማናደድ (offend) ያለሙ ሰልፎችን ሊያዘጋጅ ይችላል፤

+ ተንኳሽና ቆስቋሽ ቃላትን በመጠቀም ፕሮፓጋንዳ የመንዛት ዘመቻው ሊጧጧፍ ይችላል፤

+ በሶማሊዎችና በኣማራ እንዲሁም በኦሮሞ መካከል ግጭት ለመፍጠር፣ ግለሰባዊ ትንኮሳዎች እንዲሁም በተቋማት ላይ ሊደረግ የሚችል ጥቃት ሊኖር ይችላል፤

+ በክልሎች የድንበር አካባቢዎች መፍጠር የጀመሩትን ግጭት ይቀጥላሉበታል።

በአማራና በቤኒሻንጉል እንዲሁም በኦሮሚያና በሶማሊ ክልሎች መካከል ህወሃት በቅርቡ የፈጠረችውን ግጭት ይበልጥ እንዲባባስ ልታደገው ትችላለች፤

እነዚህ የህወሃት ሸፍጦች እንዲከሽፉ ተባብረን ካልሰራን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ብሄሮች መካከል የማይሽር ጠባሳ ሊያሳርፉ ይችላሉ። ስለሆነም ይህንን ለመመከት የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይኖርብናል፥

+ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች በዚህ ዓይነቱ የህወሃት ወጥመድ ውስጥ ላለመውደቅ፣ ከሶማሊ ክልል ካድሬዎችና የአብዲ ኢሌ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች ጋር ውይይትም ሆነ ክርክር ወይም ማናቸውንም ዓይነት መሳፈጥ ማድረግ እንደማያስፈልግ መረዳት ያስፈልጋል፤

+ ይህንን ዓይነቱን ጉዳይ ለአክቲቪስቶችና ለፖለቲካ መሪዎች ተውላቸው። እነርሱ እንዳስፈላጊነቱ ያሳጧቸዋል (debunk)፤

+ የስርዓቱ ቅጥረኞች እንደ ኦሮሞ፣ አማራ ወይም ሶማሊ በመምሰል ግጭት ለመጫር እንደሚተጉም ማስተዋል ያስፈልጋል።

+ ወያኔ ነፍሰ ገዳይ ቅጥረኞችን ልታሰማራ ስለምትችል የታወቁ አክቲቪስቶች እንዲሁም የፖለቲካ መሪዎች በያሉበት መጠንቀቅ አለባቸው።

በኦሮሞም ሆነ በአማራ ኮሚኒቲዎች ውስጥ ያሉ የስርዓቱ ቅጥረኞች ሶማሊዎችን እንዲያጠቁና ግጭት እንዲፈጥሩ ሙከራዎች ሊደረጉ ይችላሉ። የኦሮምና የአማራ ሰዎች ላይም ጥቃት ሊቃጣ ይቻላል። ምንም ሆነ ምን ግን ምላሹ የጋርዮሽ (communal) ሆኖ በሶማሊ ወይም በሌላው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ላይ ያነጣጠረ መሆን አይገባውም። አካሄዳችን የዚህ ዓይነቱን የወንጀል ጥቃት የሚፈጽሙትን ግለሰቦች ነጥሎ በማውጣት ለህግና ፍትህ ማቅረብ መሆን ይኖርበታል። የዚህ ዓይነቱ ያረጀና ያፈጀ የወያኔ ክፉ የከፋፍለህ ግዛ አባዜ የስርዓቱን እድሜ ሊያራዝመው አይችልም። (Jawar Mohammed)

(ፎቶ: ህወሃት ያሰማራቸው የሶማሊ ተወላጆች የህወሃትን ባንዲራ ዘቅዝቀው የተነሱት)

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mohammed says

    September 29, 2016 07:38 pm at 7:38 pm

    Mirga Oromoos ta’e , mirgi Amaaraa ha kabajamu gaafiin mirgaa deebiin rasaasa hin ta’u!

    Reply
  2. Lusif says

    October 1, 2016 01:25 am at 1:25 am

    One thing, we all should understand is to read and hug realty. Anybody who clearly understands reality, can not be distracted by anything else. It is not only human beings, there are also a lot of bizarre things in nature, that distract us to catch up with reality. It is the correct understanding of reality, genuine self-confidence and persistent that matters.
    As a matter of principle, those guys has the same right like everybody else to support or oppose whom they like. It is up to us to show them that they are wrong. Or just ignore them. Sooner or later they will understand that all their futile efforts was only to collect dimension returns. There could be a lot more like this one. Do not sensationalize out of proportion. Please try to be realistic.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule