• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔ እንዳዳመጥኩት

October 28, 2015 12:10 am by Editor Leave a Comment

መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።

ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር አመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።

እና አዳመጥኩ፣ “የዛሬ አሥር አመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን፣ ምክንያቱም አሁን እየቀጠርናቸው ያለነው ቻይናውያን፣ ህንዳውያን፣ ብራዚላውያን፣ ወዘተርፈዋውያን . . . የዛሬ አሥር አመት ኢትዮጵያውያን ይሆናሉ፣ በቁጥርም ከ 80 ሚሊዮን በላይ ይሆናሉ” ብዬ አዳመጥኩ።

ያገሬ ህዝብ ደግሞ የቀን ሥራ እንኳን ሳይቀር እየተቀማ ለቻይና ሲሰጥበት፣ ተግቶ ይጸልያል። “የባሰ አታምጣ” እያለ። እኔ ደግሞ አዳምጣለሁ፣

“የባሰ አታምጣ”ን መሥማት ደከመኝ

“የተሻለ አምጣ” የሚል ናፈቀኝ” ብዬ።

ሌላ ጊዜ ደግሞ ሌላው ቁጥር 00 ተናገሩ። እኔም አዳመጥኩ። በጫወታዬ ላይ ቁጥር ከ 00 በላይ መቁጠርም ሞክራለሁ። ግን የሚናገሩት ተመሳሳይ ስለሆነ መለየት ቸግሮኝ ነው አንድ አይነት ቁጥር የሰጠኋቸው። እና ሌላው ቁጥር 00 ተናገሩ። “እኛ ስለእድገታችን ስንተነብይ ቁጥሩን ለጥጠን ተናግረናል። አሁንም ቢሆን ለጥጠን እንናገራለን።” ሲሉ ተሰማ።chinese cc

እኔም ደግሞ “አዎን ለጥጠን እንናገራለን። ቃም፣ ቃም አርገን መርቀን ሥንል በጎ፣ ከፍ፣ ከፍ ያለ ቁጥር ብንመኝ ምናለበት? ቢሳካ ባይሳካ ምን ችግር አለው? ማን ይጠይቀናል?” ብዬ አዳመጥኩ።

ሌላ ጊዜ ደግሞ ሌላው ቁጥር 00 ተናገሩ፣ “ቻይናዎች አውሮፕላኑ የነሱ እንደሆነ እንዲሰማቸው እንፈልጋለን። የነሱን ዜጋም የቀጠርነው ለዚህ ነው።”

እኔም “ከቻይናው ባንክ በወለድ የተበደርነውን መክፈል ባለመቻላችን በሰሊጥ፣ በኑግና በሌሎችም ጥሬ ምርቶች ከፍለን፣ ከፍለን፣ ከፍለን፣ እዳው አላለቀም። እንግዲህ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እየሸራረፈን፣ ለምሳሌ የነሱን ዜጋ በመቅጠር አይነት ለመክፈል አስበን ነው” ብዬ ለማዳመጥ እየከጀልኩ ነው።

ጌቱ ኃይሉ የጸሃዮቹ (http://tsehayochu.com/)መጽሃፍ ደራሲ ነው።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule