• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የስደተኛው “ሲኦል ምድር” የመን እና የእኛ ስጋት …

July 5, 2014 11:36 pm by Editor 1 Comment

ሰሞነኛው የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታገትና ወደ ኢትዮጵያ የመተላለፍ ዜና ብዙዎችን እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ሆኗል። በአረብ ሃገር የሚገኙን ጨምሮ ኢትዮጵያውያንን በመላ አለም ከአድማስ አድማስ በተቃውሞና በድጋፍ እያነቃነቀም ይገኛል።

ምሽቱን በፊስ ቡክ በ Facebook ማህበራዊ ገጽ ከተንሸራሸሩት አስተያየቶችና ወቅታዊ መወያያ ርዕሶች መካከል የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታገት ሲሰማ የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፋ እንደምትሰጥ ምንጩን ሳይነግረን መረጃ ያቀበለን የአውራምባ ታይምስ አዘጋጅ ዳዊት ከበደ ያስተላለፈው የማወያያ መጠይቅ አስገርሞ አሳዝኖኛል። ዳዊት በዚህ መጠይቁ “…አቶ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያ ፖስፖር ይዞ መቆየት የለበትም ትላላችሁ ?” በማለት ዳዊት ራሱ ለመረጃ ቅርብ እንደሆነ ባለሙያ በአለማችን ነባራዊ ሁኔታ የነጻነት ታጋዮችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እያወቀ እንዳላወቀ ሆኖ በለቀቀው በሚመስለኝ መጠይቁ ሊያወያየን ከጅሏል …

ወዳጀ የአውራንባው ታይምስ ጋዜጠኛ  ዳዊት Dawit Kebede ይህን ጉዳይ ሲያነሳ በዘመነ ደርግ  “ሽፍታ ፣ ወንበዴ እና ገንጣይ! ” በሚል ስም ይወገዙ የነበሩት የወያኔ መሪዎች በሃገር ቤት ፣ እውቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ፣ የኩርዱ ነጻነት ታጋይ ኦጀላንን ጨምሮ በርካታ በአለማችን የምናውቃቸው የነጻነት ታጋዮች አንባገነን የሚሉትን መንግስት ለመጣል የሃገራቸው ፖስፖርት ይዘው እንዳልነበር ጠፍቶት አይመስለኝም። ሌላው ይቅርና በኢትዮጵያ ውስጥ የኤትራውን ጨቋኝ የኢሳያስን መንግስትን ለመጣል በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሰው ቡድን መሪዎች በኤርትራ ፖስፖርት ይሆን የሚንቀሳቀሱት?  ብየ ዳዊትን እንድጠይቀውም አድርጎኛል። ይህ በዳዊት አፍንጫ ስር ያለ መረጃ ነውና ወዳጀ ዳዊት እንዲፈትሸው በማሳሰብ ዳዊት የአቶ አንዳርጋቸውን እንቅስቃሴ የማይደግፍ ከሆነ እንደ ዜጋ በግልጽ የራሱን ሃሳብ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ እንደሆነ የወንድም ምክሬን መክሬዋለሁ። በእኔ በኩል ግን ከላይ በሰጠው የወረደ ማወያያ ሃሳብ መነሻ ሚዛናዊነት መጉደል አካሄዱ ስላላማረኝም። ይህም በመሆኑ ወዳጀ ጋዜጠኛ ዳዊት ያነሳው ማወያያ ሃሳብ አላስደሰተኝም!  … ዳዊት የጀመረው ተራ ብሽሽቅ እንጅ መረጃ ቅበላ አልመሰለኝምና አዝኛለሁ! እግዚአብሔር ዳዊትንም እኛንም ይታረቀን ብየ ብዘለው ይሻለኛል:

(ከመነሻ እግረ መንገዴ ይህን ካልኩ ወደ የመን ሰሞነኛ እርምጃ እና እርምጃው ወዳስከተለው ስጋት በጨረፍታ ላምራ …

የየመን መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት “ቀንደኛ” ተፈላጊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በማገትና በማስተላለፉ ረገድ ያሳየው ፍጥነት ብዙዎችን አስገርሟል። ላለፉት አስርት አመታት በየመን ምድር ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ ግፍ በኢትዮጵያውያን ላይ ሲፈጸም ተመልካች የሆነው የየመን መንግስት የዛሬ አርምጃ ፍጥነት ብዙዎችን አስገርሟል።

ያልታደሉ ስደተኞች ኢትዮጵያውያን ግፍ ከተበራከተባቸው አረብ ሃገራት መካከል የመንን የሚተካከላት የለም። ግፍ ተፈጽሞባቸው እዚህ ሳውዲ አረቢያ ያገኘኋቸው ግፉአን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በየመንን ምድር እንደ እንስሳ ተቆጥረው ያዩትን የስደትና እንግልትና እገታ ሲገልጹት “የሲኦል ምድር!” ማለት ይቀናቸዋል።  ስደተኛ ወገኖቻችን ዛሬ ድረስ በየመን ከተማ ፣ጉራንጉሮችና በየበርሃው የከፋ በደል እየተፈጸመባቸው ለመሆኑ የአደባበይ ሚስጥር በመሆኑ ዋቢ የሚያሻው አይደለም። የኢህአዴግ መንግስት  በኢኮኖሚ ሰደተኞች በሆኑ ዜጎቹ ላይ በየመን ምድር የሚፈጸመውን ግፍ ተቃውሞ አርባና ያለው እርምጃ መውሰድ ባለመቻሉ እስካሁን ያለው የስደተኞች ይዞታ አሳሳቢ እንደሆነ ቀጥሏል ።  በግዛት መሬቱ ላይ በዜጎቹ ግፍ ሲፈጸምብን መገደብ የተሳነው የየመን ስንኩል መንግስትም ቢሆን አለም አቀፍ ህግጋትን አክብሮ የወሰደው ቅንጣት እርምጃ ካለማሳየቱ በተዛማጅ የዛሬ አቶ አንዳርጋቸውን የማስረከብ እርምጃ ለኢትዮጵያ ሰላም በማሰብ ሳይሆን የፖለቲካ ጥቅምን ለማጋበስ የወሰደው እርምጃ ነው በሚል ብዙዎችን ቂም አስቋጥሯል።

በየመን በሽዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በግፍ በየባህሩና በርሃው ወድቀው ሲቀሩ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች የዜጎቻቸውን መብት ሲያስከብሩ አይተን ለማናውቅ ዜጎች የመንና ኢትዮጵያ  “አሸባሪ! ” ያሏቸውን ግለሰብ በታገቱበት ጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ሃገር ቤት ማስተላለፋቸው ዜና መሰማቱ ብዙዎቻችን አስደምሟል። ይህ ያልተጠበቀ ክስተትና በየመን የተወሰደ የማስተላለፍ እርምጃን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በየአቅጣጫው የተለያየ አስተያየት በመስጠት ላይ ናቸው። በርካታ ነዋሪዎች  ” አቶ  አንዳርጋቸውንና የሚመሩትን ድርጅት ስም ማንሳት በወንጀለኝነት ያስቀጣል ” የሚለውን ማስጠንቀቂያ እየጣሱ መንግስት “በአሸባሪነት ” ስለፈረጃቸው የቀድሞ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ የመጣው ይምጣ በሚል አንድምታ ድፍረት በተቀላቀለበት መንገድ ዋንኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

በኢትዮጵያ መንግስት  “ነውጠኛ አሸባሪ” የተፈረጁት እና በኢህአዴግ ላይ ጦር የሰበቀው የግንቦት 7 ድርጅት “አራጊ ፈጣሪ ናቸው” የሚባሉት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን “ለዲሞክራሲና ነጻነታቸው የተጉ፣ ብርቱ አርበኛና ታጋይ !” እያለ ከንፈሩን የሚጥላቸው እና የሚያደንቋቸው ብዙ ነዋሪዎች አጋጥመውኛል። የመንግስት ደጋፊዎች በበኩላቸው “ትልቁ አሳ ወጥመድ ውስጥ ገብቷል!” ብለው ያምናሉና ጮቤ ከመርገጥ ባለፈ በትምክህት “እኛ እንዲህ ነን!” በሚል በኩራት ሲናገሩ አድምጫለሁ! በማህበራዊ ድረ ገጾችና በሰሚ ሰሚ ወሬው ደርሶት አስተያየት ላለመስጠት የሚሸሸው ነዋሪ ብዙ ቢሆንም በሆነው ሁሉ ያደረበትን ስጋት ከመግለጽ የተቆጠበ ግን የለም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታገትና ለኢትዮጵያ መንግስት መተላለፍ ከተደሰቱት ውጭ ያለው ብዙ ነዋሪ የበቀል እርምጃ እንደሚፈጽሚ ሲዝቱ ተስተውሏል።

“ዲሞክራሲና ሰብአዊ መብትን አላስከበራችሁም !” በሚሉ ተቃዋሚ ቡድኖችና “በሁለት አስርት አመታት ዲሞክራሲን አስፍኛለሁ፣ ሰብአዊ መብት አስከብሬያለሁ!” በሚለው ኢህአዴግ መካከል አመታት የዘለቀው መጓተት ባመጣው ጣጣ በርካቶች “ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ !” በሚል ዘብጥያ ወርደዋል። አቶ አንዳረጋቸውም ቢሆን በኢህአዲግ ላይ ጠንስሰዋል በተባለው መፈንቅለ መንግስት በሌሉበት የሞት ፍርድ የተበየነባቸው መሆኑ ሲታወስ “ተይዘው ወደ ኢህአዲግ እጅ  ተላልፈዋል !” የመባሉ ዜና በቀል አስቋጥሮ ፣ በዛቻና ፉከራው ታጅቦ ዳግም በፖለቲካ ትርምስ ፍጥጫ እንዳይከታትና ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የመጠፋፋት አዙሪት እና ብጥብጥ እንዳይዶላት በነዋሪው ላይ ታይቶ የማይታወቅ ስጋት አጭሯል።

አዎ !  አረብ ሃገራት እንዲህ ናቸው ፣ በአረብ ሃገር  ያለን ስደተኞች መከራ ብዙ ነው 🙁 እኔም የሃገሬ ህዝብ በነቂስ ስለሚነጋገርበት ሰሞነኛ አጀንዳ ቢያገባኝ ይህችን ታክል መረጃ አቀብል ዘንድ ነፍሴ ፈቅዳለች ። ከዚህ ባለፈ መጻፍና መናገር ግን አቅሙ የለኝም ልበል ይሆን?

እስኪ ቸር ያሰማን !

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Eyosias Mesfin Tesfaye says

    July 8, 2014 09:01 am at 9:01 am

    Bro there are lots of children who had askaris grandpas
    In Ethiopia that betrayal goes through there veins it’s
    a bad heredity Dawit can’t help it bro I am glad
    Time for askaris children is over soon
    Thanks a million Nebeyu

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule