• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁሉም ለሀገሩ ዘብ ይቁም !!

April 18, 2013 12:52 am by Editor Leave a Comment

በዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በሀገራችን ዉስጥ የተጣለብን ከፋፍለህ ግዛ ዘመቻ ከቀድሞው በተለየ እጅግ ዘግናኝና አስከፊ በሆነ ሁኔታ ላይ መገኘት የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ወኔና ሞራል ሳይነካ አይቀርም ብዬ እገምታለሁ።  ከዚህም ውስጥ ዋነኛውና የመጀመሪያው ሰሞኑን በአማራዉ ብሔረሰብ ላይ በመድረስ ላይ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ህዝቡን ከአድማስ አድማስ እያነጋገረው መምጣቱ ሲሆን፤ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገሬ ምን ሠራሁ በማለት እራሱን እየጠየቀ ? ይህን ዘረኛ የሆነ የወያኔ መንግስት ከስር መሰረቱ ነቅሎ ለመጣል በቁርጠኝነት በመነሳት ሀገራዊ የዜግነት ግዴታውን መወጣት አለበት ፡፡ ለዚህም በዋንኛነት ትኩረት ተሰጥቶት ለነገ ይደር የማይባልበት ጉዳይ ፣ ማናቸውም የተቃዋሚ ፓርቲዎችና ፥ የድጋፍ ድርጅቶች ፣ አንድ በመሆንና እጅ ለእጅ በመያያዝ ቅድሚያ ለሀገር ሰጥቶ የመጣብንን የወያኔ ሰደድ እሳት ማጥፋት ግድ ይለናል ፡፡

ለዚሁም ለ- April 8 ቀን  በኦስሎ ኖርዌይ የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያና  ኢህአፖ የጠሩት ሀገርህን አድን ዘመቻ ጥሪ እንደ አንድ አብነት ሆኖ የሚጠቀስ  ነው ፡፡  ዘረኛው የወያኔ መንግስት ከጥነሰሱ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ስልጣን ላይ ፊጥ ብሎ እስከቀጠለበት ድረስ ሰንቆ ያመጣውን የሀይማኖትና የዘር ማጥፋት ትልም በተግባር ላይ ማዋል ከጀመረ እነሆ ብዙ አመታትን አስቆጥሯል ፡፡ ይኸውም የመጀመሪያው በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የተጀመረው የሀይማኖት ብጥብጥ በአይበገሬው የሙስሊም ወንድሞቻችን ትግል ዕለት በዕለት እየተፋፋመ ወያኔን እንቅልፍ ቢነሳውም ፣ ህወሃት-ኢሃዴግ ተስፋ ባለመቁረጥ እንደገና ፊቱን ወደ ኦርቶዶክስ ኃይማኖት በማዞር የተለመደውን የስልጣን ማራዘም ዘመቻና ህዝብን ከህዝብ የማፋጀት አባዜን በማፋፋም እነሆ አሁን ደግሞ የአማራውን ህዝብ ከእናት ምድሩና ሀገሩ የማባረርና ዘር የማጽዳት ዘመቻውን በሰፊው ተያይዞታል።

ይህም ከማናለብኝነትና ለህዝቡ ካለው ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት የመነጨ በመሆኑና በአንድ ዘር የበላይነት ብቻ የማመን ጠባብነት ጭምር የተጸናወተው በመሆኑ ነው ። ወያኔ ከመጀመሪያው ጀምሮ በኢትዮጵያ አንድነት የማያምንና ጭራሽ ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንደሌለችና ኢትዮጵያ የሚለውንም ስም ያገኘችው በሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት መሆኑን ለማሳመን የሚያደርጉትን ባዶ ጥረት በመረጃ  አንድ ግለሰብ በኢሳት ቲቪ ላይ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አገኔ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ከነ መረጃቸው አስደምጦናል ። ይህም ማለት አማራው ለትግራይ ህዝብ ጠላቱ መሆኑን አስምረው አረጋግጠውልናል ማለት ነው ። እንደውም ለአማራ ያላቸውን ጥላቻና ዘረኝነት ለመግለጽ ሲሉ ! ሆስፒታል ውስጥ አንድ በሽተኛ ከፈረንጅ ሀኪምና ከአማራ ሀኪም ማን እንዲያክምህ ትፈልጋለህ ተብሎ ምርጫ ሲቀርብለት የመለሰው መልስ አማራ ከሚያክመኝ ፈረንጁ የፈለገውን ቢያደርገኝ ይሻለኛል ብሎ በሽተኛው እስከመመለስ መድረሱን አድምጠናል።

ጎበዝ ! ወያኔዎች እኮ ዛሬ አማራውን ነገ ደግሞ ጉራጌውን ከዛም ኦሮሞውን ከሀገር በማፈናቀል እንደተባለውም ኢትዮጵያ የተባለችውንና ለዘመናት ተከብራና ታፍራ የኖረችውን፤ ጀግኖች አባቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍስሰው ያስረከቡንን ሀገር ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ሆን ብለው የተነሱ አረሞች ናቸው።  እምነበረድ ይክበዳቸውና ! አሁን በአካለ ህይወት የሌሉት ፣ የቀድሞው ጠ.ሚኒስተር የነበሩት በራዕያቸው ግን አገሪቱን የሚያስተዳድሩት ሰው ባለቤት የሆንችው ወ\ሮ አዜብ መስፍን(ጎላ) ሰሞኑን በኢቲቪ ማቅ (ጥቁር ለብሳ)  እኛን ግን ሳቅ  አላብሳናለች ፣ ስለ ባለቤትዋ የወር ደሞዝ ማለት ነው ለኢህአዲግ መዋጮ ከፍሎ የሚደርሰው 4,000ብር ብቻ ነው ብላናለች ፡፡  አንድም ቀን ልጆቼን ፣ ቤቴን ሳይል ለሀገሩ 24 ሰአት ያገለገለ መሪ ነው ፥ ወደዚህ ሀገር ሲመጣም ጭንቅላቱን ብቻ ነው ይዞ የመጣው ብላናለች ። ሌላው ሰው ወደዚህ ዓለም ሲመጣ ምን ጨብጦ እነደመጣ ፣ ኧህ ! ካሏት አዜብ መስፈን ብዙ ቀልዶችን ሳትነግረን አትቀርም ፡፡

ወይዘሮዋን አንድ ያልገባት ነገር ቢኖር ፣  መለስ  ጭንቅላቱን አሟጦ የተጠቀመበት ፣ የባንዳ ልጅ እየተባለ ያደገበትን በቀል ፣ህዝቡ ላይ በመበቀል ሙሉ ኃይሉን የተጠቀመ  አረመኔ ፥ ጨካኝና ዘረኛ  መሪ መሆኑን ያለመረዳቷ ጉዳይ ነው ። ከዚህ በፊት የመለስ ራእይ ሳይደለዝና ሳይበረዝ ትግሉ ወደ ፊት ይቀጥላል ያልሽው እንደተጠበቀ ሆኖ ፣ ዛሬ ደሞ በትንሽ ደሞዝ እየተከፈለው ሌት ተቀን እየሰራ ሀገራችንን ትልቅ ደረጃ ላይ እንድትደርስ ያደረገ የመጀመሪያው መሪ መሆኑ ተሰምሮበት (Guinness book of records) ላይ ተመዝግቦ መቀመጥ አለበት አይነት ትእዛዛዊ የማስጠንቀቂያ መልክት በማስተላለፍ “የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያድርቅ” አይነት ጨዋታሽን በጥሩ ተውኔታዊ ገቢር ! የሃዘን ልብስሽን እንደ ጉሬዛ ግንባርሽ ድረስ ተከናንበሽ ትውነሽልናል፡፡

ምናልባት መለስ ዜናዊ ትግራይን አልምቶ ይሆናል አላውቅም በእርግጠኝነት ግን መናገር የምችለው ቀሪዋን ኢትዮጵያን አድምቷል ። ህዝቡንም እርስ በእርሱ ደም እንዲቀባባና ፥ በዘርና በሀይማኖት በመከፋፈል የሀገሪቷንም መሬት ለባእዳን በመሸጥ ህዝቡን ለከፍተኛ ችግርና መከራ አጋፍጦ ፣ ዜጋ ሁሉ የሚወዳትን ሀገሩን እየጣለ በየአረብ ሀገሩና አውሮፓ ውስጥ እንዲሰደድ ያደረገ ትልቅ የማይረሳ ነቀርሳና ጠባሳ ህዝቡ ላይ  ትቶ የሄደ መሪ ነው ። የእርሱን ራእይ በመከተል እነሆ አሁንም ያሉት መሪ ተብዬ ጃሌዎቹ ከሱ በባሰና አስከፊ በሆነ ሁኔታ ህዝቡን ከተወለደበትና እትብቱን ከቀበረበት ቀዬ በግፍና በጭቆና እያባረሩት ይገኛሉ ። ስለዚህ ጎበዝ ይህን ጉዳይ ዝም ብለን ማየት የማንችለውና ሁላችንም በአንድ ላይ ሆነን እጅ ለእጅ ተያይዘን ወያኔንና አንጃዎቹን “በቃ” ማለት የሚጠበቅብን ወቅቱ  ከምንግዜውም በላይ አሁን ነው ።

በመጨረሻም ማለት የምፈልገው ነገር ቢኖር የኢህአፓ ወክንድ የሚያደርገው እንቅስቃሴ እጅግ የሚያኮራ በመሆኑ ሳይደነቅ መታለፍ የሌለበት ጉዳይ ነው። ለዚሁም ከዚህ በፊት በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ወያኔ ያደረሰውን በደል አብሮ ከጎኑ በመሰለፍ ፣በኦርቶዶክስ ሀይማኖት ላይም እንዲሁ ችግሩን አብሮ በመጋፈጥና አሁን ደሞ በአማራው ህዝብ ላይ ወያኔ የሚያደርሰውን አሰቃቂ በደል በመቃወም በከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ሌላው ደግሞ ማናቸውም ለሀገራችን ተቆርቋሪዎች ነን የሚሉ ኢትዮጵያዊያኖች ወገኖቻችንን በሙሉ የሚያሳትፍ (keep of fighting ethiopian youth forum KOFEYF) የሚል የፓልቶክ (paltalk room) ከፍቶ ዘውትር በየሳምንቱ እሁድ ከ15፡00 – 3፡00pm ሰአት ጀምሮ አንጋፋ የሆኑ የፖለቲካ ባለሞያዎችንና የሀገር ተቆርቋሪዎችን በመጋበዝ ትልቅ አስተዋጾ በማድረግ ላይ ይገኛል ። እርሶም ይህን እድል በመጠቀም ያለዎትን እውቀት ለማህበረሰቡ በማስተማርና በመማር ለሀገርዎ ትልቅ አስተዋጽኦ በማድረግ ዉድ ሀገራችንን  ኢትዮጵያን ከገባችበት የድጥ ማጥ ውስጥ እናውጣት የሚል ተማጽኖዬን በማክበር እጠይቃለሁ።

ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኑር!!!

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያ ሀገራችንን በምህረቱ ይጎብኛት!!!

Dawit Abebe, April 2013. Oslo

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule