• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዓይኖች ሁሉ ወደ ኦስሎ ተተክለው ስለ ኢትዮጵያ ተመለከቱ”

December 11, 2019 07:53 pm by Editor 1 Comment

ኦስሎ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ እስክትመስል ድረስ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና በኢትዮጵያ ባነሮች ተውባ ሰነበተች። ሚዲያዎች ሁሉ ስለ ኢትዮጵያ በኩራት መሰከሩ። ኢትዮጵያን በድህነትና በጦርነት፣ በረሐብና በእልቂት የሚያውቋት ሁሉ አዲስ ታሪክ ሆነባቸው። በሩጫ ስናሸንፍ ነበር የሚያውቁን፤ ዛሬ ደግሞ በሰላም ሥራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ስናሸንፍ አዩን። ከግሪን ላንድ እስከ ኒውዚላንድ፣ ከቺሊ እስከ ጃፓን ዓይኖች ሁሉ ወደ ኦስሎ ተተክለው ስለ ኢትዮጵያ ተመለከቱ።

በመላው ዓለም ተበትነው የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን የዜግነት ክብራቸውን ከፍ የሚያደርግ ሥራ በታሪክ ውስጥ ሲመዘገብ አዩ። ልጆቻቸው በባዕድ ሀገር በታሪካቸው ኮሩ። ሀገራቸው በምሳሌነትና በአርአያነት ስትነሣ በዓይናቸው ብሌን ተመለከቱ፤ ሰሙ። በዓረብ ሀገር የሚኖሩ ዜጎቻችን አሠሪዎቻቸው ወደታች ሳይሆን ወደላይ እንዲዩዋቸው የሚያደርግ ታሪክ በዓለም አደባባይ ሲከወን ዕንባ በተሞሉ ዓይኖቻቸው አደነቁ።

ሁለት ዓይነት ታሪክ ሲሠራ የዓለም ዓይኖች ታዘቡ። በጦርነት የምትታወቅ ሀገር የሰላም ሽልማት ተሸለመች። የሰላምን ዋጋ የሚያውቀው ዓለም፤ የሰላም ሽልማት በቀላሉ እንደማይገኝ የሚያውቁ የዓለም ዜጎች በደስታና በክብር አብረውን ከረሙ። ለሕዝቦች መቀራረብ፣ ለሕዝቦች መገናኘት፣ ለሕዝቦች ዕርቅና ሰላም መሥራት የሚያሸልም ተግባር መሆኑን የሚያውቁ ሁሉ፤ የቻሉ በኦስሎ ጎዳናዎች ተገኝተው፤ ያልቻሉ በየቴሌቭዥን መስኮቶች አፍጥጠው ክብር ሰጡን።

በኦስሎ ያገኘነው ክብር የሀገራችን ጉዞ ከትናንት የዛሬው፣ ከዛሬውም የነገው እጅግ የተሻለ መሆኑን አመላክቶናል። ይህ ለኢትዮጵያውያን የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይሆንም። በሰላም፣ በሳይንስ፣ በሥነ ጽሑፍ ገና ብዙ ኢትዮጵያውያን ወደ ኖቤል ሀገር ወደ ኖርዌይ ይመጣሉ።

ዛሬ ያገኘነውን አክብረን አያሌ ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች ሀገራቸውን እንዲያስጠሩ እንሠራለን። ለዚህ ደግሞ ሁላችንም ሀገር የሚያስጠራ ጥረት እንድናደርግ ጥሪ አቀርባለሁ።

Abiy Ahmed Ali

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column, Nobel Peace Prize Laureate Abiy Ahmed Ali

Reader Interactions

Comments

  1. መታሰቢያ says

    December 12, 2019 10:52 am at 10:52 am

    በመላው አለም በታሪክ ውስጥ ያለውን ጦርነቱንም ሰላሙንም ሽልማቱንም የሚፈጥሩት በአብዛኛው እራሳቸው ግሎባሊስት ኦሊጋርኬዎቹ ናቸው።የአንድን ሀገር መሪ ሲያወድሱም ሲሸልሙም ያ ግለሰብ ለሀገሩ ህዝብ ብሄራዊ ጥቅም ምን መልካም ነገር ሰራ ወይንም ለወደፊት ምን መልካም ነገር ይሰራል ብለው ሳይሆን ዋና መመዘኛቸው ለግሎባሊስት ኦሊጋርኬው አለም አቀፍ ጥቅም ምን ሰርቷል ወይንም ወደፊት ምን ሊሰራ ይችላል ተብሎ ታቅዶና ተሰልቶ ነው። በተቃራኒው የአንድን ሀገር መሪ ሲያወግዙና ጫና ሲያደርጉም ከራሳቸው ዘላቂ ጥቅም አንፃር አስልተው ነው።ሌላው በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ለተፈጠረው ሰላም መሸለም የነበረባቸው የሁለቱም ሀገር መሪዎች መሆን ነበረባቸው።ለምን ዶክተር አቢይ ብቻ ተለይተው ተሸለሙ?
    እርግጥ ነው ለሰላም የሚገባውን ዋጋ ያህል መከፈል አለበት።ከዚህ አንፃር ኤርትራና ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሰላም መስፈን በየፊናቸው ምን ያህል ዋጋ እየከፈሉ ነው?ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያስ ዘላቂ ብሄራዊ ጥቅሟን ምን ያህል እያስጠበቀች ነው?ነው ወይንስ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟ የሚጠበቀው በኖቤል ሽልማቱ ብቻ ነው ማለት ነው?ኢሳያስ ቀርተው አብይ ተለይተው ሲሸለሙ ኢትዮጵያ እስከዛሬ ለሰላም አብልጣ የከፈለችው እና ወደፊትም በቀጣይ የምትከፍለው የበለጠ ብዙ ዋጋ አለ ማለት ነው?
    የሀገራችን መሪ በአለም አደባባይ መሸለሙ የኢትዮጵያ ስም በመልካም መጠራቱ ጥሩ ስሜት ይፈጥራል ደስ ይላል።
    ነገር ግን በእውነት እና በምክንያትነት ላይ ያልተመሰረተ ሆያ ሆዬ እና ጊዚያዊ የደስታ ስሜት አላፊ ነው።የኖቤል ሽልማቱ ጊዚያዊ ስኬት መሬት ላይ ያለውን ያፈጠጠ ያገጠጠ ነባራዊ ሁኔታ ያን ያህል አይቀይረውም።
    አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ እንዳይሆን አርቆ ማሰቡ ይጠቅማል።
    የአንድን ሀገር እና ህዝብ አጠቃላይ መፃኢ
    እና ነባራዊ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ከአንድ ግለሰብ ጋር አቆራኝቶ ማስተሳሰርም ወደ ሌላ ተጨማሪ ፈተና እንዳይወስደን መጠንቀቅና አርቆ ማሰብ ይጠቅማል።የአንድ ሀገር ዋናው የኖቤል ሽልማቱ በቅድሚያ የራሱን ሀገር ብሄራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ነው።ፈረንጆቹ ብልጦች ስለሆኑ በየተቋሞቻቸው ለሚያቀርቡልን ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ጊዚያዊ ውዳሴ ከንቱ ሁሉ እንደ ህፃን ልጅ በቀላሉ የምንሸነፍ ወይንም የምንሸወድ ከሆነ ብዙ ጥፋቶችን ልንሰራ እንችላለን።ጥሩ የሰራን እየሸለሙ ማበረታታት ያለና ወደፊትም የሚኖር መልካም ነገር ነው።ነገር ግን አንድ ሽልማት ሲሰጥ ለሽልማቱ ከበስተጀርባው ያለው ገፊ ምክንያት ምንድን ነው ብሎ መጠየቅና መመርመር ይገባል።የውጪ ሃይሎች ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲሉ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ውዳሴ ከንቱ እያቀረቡ ወደፊትም እንደ ህፃን ልጅ በጊዚያዊ ብልጭልጭ ነገር እንዳይሸውዱን እና ብሄራዊ ጥቅማችንን ለጊዚያዊ ጥቅም እያሳለፍን እንዳንሰጥ ቆም ተብሎ ቢታሰብበት ጥሩ ነው።ይሄ አካሄድ በኢትዮጵያ እንደ ልምድ እየተስፋፋ ነው።ለመልካም ስራ ሽልማት እየሰጡ እውቅና መስጠቱ ጥሩ ነው።ነገር ግን ምንጊዜም ቢሆን የተሰራው ስራ መልካም ከሆነ እራሱ ተግባሩ ሌላ መስካሪ ሳይፈልግ አፍ አውጦቶ ይመሰክራል።ከኖቤል የሰላም ሽልማቱም ይልቅ መሬት ያለው ነባራዊ እውነታ አፍ አውጥቶ ይመሰክራል።በሌላው ፅንፍ ያለውን ስናይ አብይ ለምን ተሸለሙ ብሎ ለተቃውሞ ሰልፍ መውጣት መብት ቢሆንም እንኳን ተገቢ አይደለም።ይሄን ማድረግ ዶ/ር አብይ ለሀገራቸው ዜጋ መጦፎ ስሜትን እንዲያሳድሩ በር ይከፍታል።ከሀገራቸው ብሄራዊ ጥቅም ይልቅ ጭራሽ የአለም አቀፍ ኦሊጋርኬውን አለም አቀፍ ጥቅም እንዲያስጠብቁ እድል ይፈጥራል።የውጪ ሃይሎች እንደ እኛ አይነት የታዳጊ ሀገራት መሪዎችን ከሚመሩት ህዝባቸው ነጥለው ወደራሳቸው አለም አቀፍ ኦሊጋርኬ ጎራ የሚስቡበት የተለያዩ የስነልቦናና የስሜት መቀየሪያ ታክቲኮች አሏቸው።አንዱ ዘዴ ያ መሪ ከህዝቡ የተለየ ማንነት እንዳለው አድርጎ እንዲያስብ አድርገው እየካቡ ሰማይ ያወጡታል።የራሱን እና የቤተሰቡን የህይወት ዘይቤውን እና አመለካከቱን ሁሉ ከሀገሩ ብሄራዊ ማንነት ይነጥሉና የራሳቸው አለም አቀፍ ጎራ ውስጥ ይከቱታል።ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ያ መሪ በሀገሩና በህዝቡ ላይ እንደ ባእድ የውጪ ሰው ጨካኝ ዲክታተር ይሆናል።ዶክተር አቢይ ለምን ተሸለሙ ብሎ መቃወም እሳቸውን ወደዚያ አቅጣጫ መግፋት ይሆናል።ሆኖም ግን ሽልማቱ ዶክተር አብይን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ከቶውንም እንደማያዘናጋቸው ተስፋ አደርጋለሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule