• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ

January 25, 2024 09:08 am by Editor 1 Comment

አልሸባብ ጋልሙዱግ በሚባል ክልል ከሶማሌ ጦር ጋር ባደረገው ውጊያ ሶስት የሶማሊያ ጦር ካምፖችን በቁጥጥሩ ስር አድርጓል።

አል ሸባብ ከሶማሊያ ጦር ጋር አምስት ሰዓታት ያህል የቆየ ከባድ ጦርነት ካካሄደ በኋላ ከጥቃቱ የተረፉ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር የ”ጎርጎር ኮማንዶ” መኮንኖችና ወታደሮች እንደተናገሩት በውጊያው ከ230 በላይ  የሶማሊያ ወታደሮች መሞታቸውን እንዳረጋገጡና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መቁሰላቸውን ገልፀዋል።

የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በቦታው ያሰፈራቸው ወታደሮቹ 4 ሻለቃ የ”ጎርጎር ኮማንዶዎችን” ሲሆን 15 የአል ሸባብ አሸባሪዎች ጋር ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ሞትና የአካል ጉዳት አስተናግዷል።

የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በአል ሸባብ ከበባ ውስጥ ሆኖ ምንም ዓይነት የሽፋን ኃይል ማሰማራት አልተቻለውም ተብሏል።

ፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአል ሸባብ የሽብር ቡድን ላይ ዘመቻ ጀምሬያለሁ ካሉበት የቅርብ ጊዜ መግለጫቸው ወዲህ ብቻ የተገደሉ ወታደሮች ቁጥር ከ 4,000 በላይ ሲደርስ ከ300 በላይ የሶማሊያ ጦር አዛዦችም በሽብር ቡድኑ መገደላቸውን ዘገባዎች አስታውሰዋል። (Esleman Abay)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: al shabab, Port of Ethiopia, somalia, Somaliland

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 30, 2024 06:32 pm at 6:32 pm

    የራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች የሚባለው እንዲህ ያለው ነገር ሲከሰት ነው። የመቋዲሾው መሪ ኢትዮጵያ ጋር ለመግጠም ተዘጋጅተናል ይላል። ጥቁሩ ዓለም ጨለማ ሃሳቢ ነው። የአረብና የነጭ መንጋ ወደባቸውን ሲወር ትንፋሽ ያላሰሙት አሁን እንሆ ገና ላም አለኝ በሰማይ ወሬ ከወደ አዲስ አበባና ከሃርጌሳ ተሰማ ተብሎ ይህን ያህል መፎከር ምን የሚሉት እብደት ነው። ሱማሊያ ሃገር መሆኗ የቀረው በ 1991 ነው። ያው የአፍሪቃ መከራ ሁሌ የሚታከከው የቅኝ ግዛት ወሰንን ተከትሎ ሌላውን ገመና እየደረበ በመሆኑ በእንግሊዞች ስር የቆየችው ሶማሊላንድ ከቀረው የሱማሊያ ክፍል ተለይቼ ሃገር ሆኛለሁ ካለች ዘመናት አለፉ። በእነዚህ አስርተ አመታት መልካም ነው በሚባል ደረጃ ቁራሿን ሃገር አስተዳድረዋል። እያስተዳደሩም ይገኛሉ። እርግጥ ነው ሃገርነታቸውን ሌሎች ሃገሮች አልተቀበሉትም። እንደ እውነቱ ከሆነ የዓለም ፓለቲካ ገጣባ ነው እንጂ የሱማሊላንድ ጥያቄ ከኤርትራው ጥያቄ የሚለይ አይደለም።
    ታላቋን ሶማሊያ እመሰርታለሁ በማለት የያንየው እብድ ሲያድ ባሬ ኢትዮጵያን ወሮ ብዙ እልቂት እንደ ደረሰ ሁሉ አሁንም እንደ ግብጽና ሌሎች የነጭ እቃ ተሸካሚና ተላላኪ ሃገሮች የሱማሊያና የኢትዮጵያን ግጭት ይፈልጉታል። ለዚህ ነው ቱርክ ኢትዮጵያንም ሱማሊያንም የምታስታጥቀው። እሳቱን በጋራ ይሙቁት በለው ነው። ጥቁር እንደ ቅጠል ሲረግፍ ደስ ይላቸዋል። ግን ይህ ብቻ አይደለም የግብጽ መንግስት ድንፋታ የኤርትራው መሪና የመቋድሾው መሪ የካይሮ ቆይታ ሁሉ ለጥቁር ህዝቦች ያሰበ ሳይሆን ለራስ ጥቅም ነው። የአረቡ ራቢጣ ኢትዮጵያን እንደ እሳት ነው የሚፈራው። በመሆኑም መቋዲሾን ደግፎ መግለጫ መስጠቱ የሚጠበቅ ነው። ልብ ላለው ግን ሱማሊያ እንድትበታተን፤ ዛሬ እነ አል ሸባብና ሌሎች በውጭና በሱማሊያ ውስጥ አክራሪ የእስልምና እይታ እንዲይዙ ያደረጉት ከአረብ ሃገር የሚመነጨው የእስልምና ትምህርት ነው። በሃይማኖት አክራሪዎች የተነሳ የስንቱ ቤት ፈረሰ? የስንቱ ሃገር ተፍረከረከ? ቤቱ ይቁጠረው። የእምነት አክራሪዎች የእስልምና እምነት ተከታዪች ብቻ አይደሉም። ስመ ክርስቲያኖችንም ይጨምራል።
    በቅርቡ የሚኒሴቷዋ የሶማሊያ ተወላጅ የኮንግረስ ተወካይ ከአሜሪካ ይልቅ ሶማሊያን አስቀድማ መናገሯ ምን ያህል የትሮጃን ፈረሶች አሜሪካን እንደ ወረራት ያሳያል። እንደ እኔ ቢሆን ያላትን ሁሉ ሰብስቦ፤ ከነ ነጭ ባሏ መቋድሾ ማድረስ ነበር። ምን አልባትም ሸረኛውና ዘረኛው ዶላንድ ትራምፕ ከተመረጠ ልትሸኝ ትችል ይሆናል። ይህ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ ተወሽቆ ሳይመርጡ መለፍለፍ መከራን ያመጣል።
    ባጭሩ የመቋድሾው መንግስት በቋፍ ላይ ያለ፤ በተመድ ወታደሮች የኢትዮጵያን ጨምሮ በድጋፍ የቆመ በመሆኑ ኢትዮጵያን የመውጋት አንድም አቅም አይኖረውም። ይህ ሲባል ግን በዚህም በዚያም ተወንጫፊ ከአረብና ከነጩ አለም እየሰበሰበ ሃገር አያተራምስም ማለት ግን አይደለም። ግብጽ ለሶማሊያ አንድነት አብራ እንደምትዋጋ አስታውቃለች። ጥሩ ነው ይምጡ። ድሮስ እነ አሉላ አባነጋ ቂጥ ቂጣቸውን ብለው አይደል ከኤርትራ መሬት ያባረሯቸው? ግን ዛሬ ያን ታሪክ ማን ወደ ኋላ ተመልሶ ያየዋል። በዘሩና በቋንቋው ሰክሮ ይወላገዳል እንጂ! እውነተኛ የፓለቲካ ሰው፤ አፍሪቃዊ፤ ኢትዮጵያዊ መጠየቅ ያለበት ግን UAE ወደቡን ተረክባ ስታስተዳደር፤ ጅቡቲ ለፈረንሳይ ለቻይና ለአሜሪካ ወዘተ ወደብ ሲፈቅድ ለምን ያኔ የተቃዋሚ ድምጽ አልበረከተም? መልሱ የአረቡና የነጩ ዓለም ጥላቻ በኢትዮጵያ ላይ በመሆኑ ነው። ይህ አልገባኝም የሚል ወያኔ 3 ጊዜ ወረራ ሲያደርግ ከላይና ከሥር ጦርነቱን በይፋ ይመሩት የነበሩት አሜሪካኖች ናቸው። እናስብ ስንት ብልሃት ተጠቀሙ ሰውንና አመራሩን ለማስበርገግ? ስንት ጊዜ ተመድ በትግራይ ጉዳይ ተሰበሰበ ትዝ ይበለን። ጠላቶቻችን እልፍ ናቸው። የኢትዮጵያን ል ዕልና ያኔም ዛሬም አይፈልጉትም። እነርሱ የሚፈልጉት እቃ ተሸካሚና ተላላኪ መንግስት ነው። ወያኔ በዚህ በኩል የተሳካለት ባለ ሁለት የፊት ገጽታ ባለቤት ነበር። ለሃገርና ለውጭ ዓለም የሚያሳየው መልኩ ለየቅል ነበር። ግን ሁሉ ነበር ሆነ። ኢትዪጵያ መተንፈሻ ወደብ በግድም በውድም መፈለጓ ምርጫ ሳይሆን የግድ ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule