• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጴጥሮስ ያቺን” ቃል!

July 30, 2013 02:25 am by Editor 1 Comment

“ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሏቸው እውነት እንዳይመስላችሁ፡፡ ሸፍታ ማለት ያለ አገሩ መጥቶ የሰውን አገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን፡፡” አቡነ ጴጥሮስ፡፡

ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን ጀግናው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በግፍ የተገደሉበት ቀን ነው፡፡ እኒህ ታላቅ አባት ለሰማዕትነት ያበቃቸው ዋናው ምክንያት በወቅቱ ለተጠየቁት ቀላል ለሚመስል ጥያቄ “ቃሌን አልክድም” ብለው በመቆማቸው ነበር፡፡

ፋሺስት ኢጣሊያ አገራችንን ወርሮ ሕዝቡን ባስጨነቀ ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ ከአርበኛው ጋር በመቆም የጣሊያንን ሠራዊት በድፍረት ሲቃወሙና አርበኛውንም ሲደግፉ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም ከጊዜያት በኋላ በፋሺስቶች ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ጣሊያኖች ራሳቸው በሰየሟቸው ዳኞች ፊት አቡኑን ለፍርድ በማቅረብ ከላይ ሲታይ በጣም ቀላል የሚመስል ጥያቄ ያቀርቡላቸዋል፡፡ የጥያቄው ዓላማ አቡኑን የጣሊያን ተገዢ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን በወቅቱ የነበረውን ሕዝባዊ ዓመጽ ለማብረድ ቢቻልም ደግሞ የብዙሃኑን ድጋፍ ለማግኘት የታሰበበት ነበር፡፡

ስለዚህም የግራዚያኒ ዳኞች አቡነ ጴጥሮስን ለፍርድ ባቀረቧቸው ጊዜ የጠየቋቸው “ሊቀጳጳሱ አቡነ ቄርሎስ እንዲሁም ሌሎች የጣሊያንን የበላይነት ተቀብለዋል፤ እርስዎም እንዲሁ ተቀብለው ሌሎችም እንዲቀበሉ ቢያደርጉ ይሻላል፤ ብቻዎን ማመጽ ምንም አይሰራልዎትም፤ ይህንን ቢያደርጉ ምን ይመስልዎታል …” የሚል እንድምታ ነበረው፡፡ … አቡኑም “ከመሞት መሰንበት” በማለት የቀረበላቸውን ምክር አዘል አስተያየት መቀበል አላቃታቸውም፡፡ ሆኖም ለእምነታቸውና ለሕዝባቸው የገቡትን ቃል ከሚክዱ ሞትን እንደሚመርጡ በድፍረት ለዳኞቹ መለሱላቸው፤ እንዲህም አሉ፤

“አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ … ስለ አገሬና ስለ ቤተክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ … እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ” የሚል ነበር፡፡ (ጳውሎስ ኞኞ “የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት” አ.አ. 1980፤ ገጽ 157)

ረቡዕ ሐምሌ 22 ቀን 1928ዓም (July 29, 1936) አቡነ ጴጥሮስ ከፊት ለፊታቸው የተደገነውን የጣሊያንን መትረየስ ሳይፈሩ ከመገደላቸው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሚከተለውን በመናገር የመጨረሻ ቃላቸውን ሰጡ፡፡

“ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሏቸው እውነት እንዳይመስላችሁ፡፡ ሽፍታ ማለት ያለ አገሩ መጥቶ የሰውን አገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን፡፡” (ዝ.ከ.፤ ገጽ 157)

አቡነ ጴጥሮስ ይህንን ከተናገሩ በኋላ የፋሺስት የጦር መኮንኖችና ጄኔራሎች በተሰበሰቡበት አደባባይ የተሰማው የማያቋርጥ የጥይት እሩምታ ነበር፡፡ በእጃቸው ከያዙት መስቀል በቀር “መሣሪያ” በእጃቸው ያልነበራቸው የሃይማኖት አባት የተናገሩት ቃልና ያደረጉት ቆራጥ ውሳኔ የግራዚያኒን ጦር ወኔ ሰለበው፡፡ ለአቡኑ አንድ ጥይት አልበቃ ብሏቸው የመትረየስ እሩምታ ተኩስ በመልቀቅ በግፍ ረሸኗቸው፡፡

abune_petros removed
የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ሲንሳ (ፎቶ Fortune)

ፍርሃት ለአንድ ሰው መትረየስ ያስተኩሳል፤ ለአይጥ ታንክ ያሰልፋል፤ “ለቄጠማ ሰይፍ ያስመዝዛል”፤ የመናገርና የመጻፍ መብቴ ይከበር ለሚል የጸረ አሸባሪ ሕግ ያስወጣል፤ ሰላማዊውን ሰው “አሸባሪ” ያስብላል፡፡ ፍርሃት ያስደነግጣል፤ ያስፈራል፤ ያንቀጠቅጣል፤ ያሸብራል፡፡ ፈሪ የደፋሩ ድፍረት ያስደንቀዋል፤ ድፍረቱን ይመኛል፤ ከዚያ ለመውጣት ግን ራሱ ፍርሃት አንቆ ይይዘዋል፤ ፍርሃት ራሱ ፈሪውን ያስፈራዋል፤ “አልገዛም፤ ቃሌን አልለውጥም” የሚለው የደፋሩ ውሳኔና ቆራጥነት እጅግ ስለሚያሸብረው ራሱ ተሸብሮ ሽብር ይነዛል፤ ያስራል፤ ያሰቃያል፤ ይገድላል፡፡ አልበቃ ሲለው ሃውልት ያስፈርሳል፡፡ ግን አይረካም፤ ምክንያቱም ፍርሃት ሳይሆን ነጻነት ነው ርካታን የሚሰጠው፡፡ ስለዚህ እንደፈራ ኖሮ እንደፈራ ይሞታል፤ ቃሉን የሚጠብቀው ግን በነጻነት ኖሮ በነጻነት ይሞታል፤ ሞቶም ግን በቃሉ ምክንያት ይታወሳል፡፡ የጴጥሮስ ቃል መቼም አይሞትም!!

(ይህ ጽሁፍ ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ርዕስ አቶ መክብብ ማሞ ከጻፉት ጦማር ላይ በሰጡን ፈቃድ ለወቅቱ በሚመች መልኩ የቀረበ ነው፤ ለጸሐፊው ምስጋናችን ይድረሳቸው፤ ፎቶ wikimapia)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Hilina Berhanu says

    July 31, 2013 04:45 pm at 4:45 pm

    የኝህን ታላቅ መንፈሳዊ ሰውና የኢትዮጵያ ጀግና ሙት ዓመት አስታውሳችሁ ልባችንን ስለሞላችሁት ምስጋና ለደራሲዎቹና ለጉልጉል አዘጋጆች ይድረስ!!! ሁሉም፣ በዘር ይሉ በእምነት፣ በሃይማኖት ፤ እንዳው በጠቅላላው ሰላም በማያውቅ በፖለቲካ እብደት፣ ሁሉም በየጎራውና ጉድጓድ ብቻ መጮህ በሚፈልግበት በዛሬው ቀውጢ ሰዓት፣ ኢትዮጵያን ለማዳን ጊዜው እንደ አቡነ ጴትሮስ መንፈሰ ጠንካራነትንና የሃገር፣ የወገን ፍቅር ልባዊ አንድነትን የሚጠይቅ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule