• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሀገር የማያድስ አዲስ ዓመት ለእኔ ምኔ ነው?!

August 27, 2015 12:26 am by Editor 2 Comments

ዛሬ ላይ የጊዜ ዑደት ተፈጥሮአዊ ልማድ አጃቢና አድማቂ ከመሆን በቀር ዘመን ተሸኝቶ ዘመን ሲተካ አላፊውን ዘመን በመልካምና በበጎ የምንዘክርበት መጪውንም ተስፋ የምናደርግበት አንዳች ተጨባጭና በቂ አመክንዮ (ምክንያት) ያለን መስሎ አይሰማኝም!! ይህን ስል ግን ከእያንዳንዱ ግለሰብ አሊያም ቡድን አንፃር ሳይሆን አንደሀገር ማለቴ ነው፡፡

እነሆ ዳር ላይ ቆመን እንቀበለው ዘንድ የምናሰፈስፍለት የ2008 ዓ.ም በተዳፈነ ዲሞክራሲ የአማራጭ እሳቤ አልባ ወደሆነ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤቶች አስተዳደር ስር የሚዘፍቀን ከዛም ባለፈ ምንአልባትም ሳንሰማና ሳናይ፤ መስማማትና አለመስማማታችንም ሳይታወቅልን በሚደነገጉ የሕግ፣ የደንብ እና የፖሊሲ ድንጋጌዎች የምንዋጥበት ወቅት ጅማሬ ነው ማለት ይቻላል! ለመጠናቀቅና የዘመኑን መቁጠሪያ ወደ 2008 ለመቀየር ጥቂት ቀናት የቀሩት ይህ የ2007ዓ.ም በመሪዎቻችን አጅግ አሳዛኝ፣ አሣፋሪና አስቂኝ ድርጊቶች አንዲሁም ወደር በማይገኝለት ሐሰት የተጨማለቀ ነበር ብዬ ብል ከግነት ይቆጠርብኛል የሚል ግምት የለኝም! ምክንያቱም ሁሉንም እያየንና እየታዘብን ያለፍነው ሐቅ ነውና!

ሕሊናቸውን ሽጠው ሆዳቸውን እየሞሉ ካሉ፤ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጥምቀት የልማታዊ ዲሞክራሲ ማህተብ ካነገቱ ካድሬዎች በቀርስ ማን አጋነንክ ወይም ሐሰት ተናገርክ ብሎ ይከሰኛል??!!

1. አሳዛኞቹ ተግባራት፡- ነገ ላይ በአዲሱ ዘመን አሮጌው ሊሰኝ የሚጣደፈውና ጉደኞች ጉደኛ ያሰኙት 2007ዓ.ም የሰላሳ ወገኖቻችን ደም በሊቢያ በረሐ በአረመኔዎች እጅ በከንቱ መፍሰስን የተመለከትንበትና የሰማንበት መንግሰታችንም ዜጎቹ መሆናቸውን አስኪያጣራ ዓለም ኢትዮያዊያን አንደሆኑ አኛም ወንድሞቻችን መሆናቸውን ቀድመን ያወቅንበትን ሂደት አሳልፈናል፣ የሳሙኤል አወቀ ሰለእውነት የመጮህ ትግል ፍሬ በሐሰተኞች በግፍ የመገደል እጣ ፈንታ መሆኑን ተረድተንበታል፣ በሐይማኖት ነፃነት መብት ለጥያቄዎቻቸው መልስን ለችግሮቻቸው መፈትሔዎቸን ይፈልግ ዘንድ የተቋቋመ ኮሚቴ አባላት የነበሩ የሙስሊም ወገኖቻችን ላይ በተመሰረተ የሽብር ክስ ከ7 እስከ 22 ዓመት የሚደርስ የእስር ፍርድን ተመልክተናል፣ በዩ.ኤስ.ኤ ካሊፎርኒያና በአውስትራሊያ የተከሰተው ዓይነት ድርቅ (ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ለተናገሩት አኔ አፍራለሁ!!) በተወሰነው የሀገራችን አካባቢዎች መከሰቱን አይተናል፤ በእነዚህ ሁሉ 2007 ዓ.ም ሁላችንን አሳዝኖ ወደማለፉ ነው፡፡

2. ወደር አልባው ሐሰትና አስቂኙ ክንውን፡- ከ1987ዓ.ም ጀምሮ አምስት ዓመታትን እየጠበቀ በ2 እና በ7 በሚጨርሱ የዘመን አድሜ ቁጥሮች የሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ 2007ዓ.ም ላይ ሲደረስ ለየለትና በማሩ ፈንታ እሬቱን እና ምሬቱን የጋገረች ንብ መቶ በመቶ ተመርጣለች የሚል ለጆሮ የሚከበድ ትልቅ ሐሰት ተሰማበት፤ ይህን ውሸት የነገረን ምርጫ ቦርዱ ደግሞ የዚህ አስቂኝ የሀሰት ክንውን የስራ ሂደት ባለቤት መሆኑን በቁርጠኝነት አስመሰከረ!

3. የዓመቱ ዘመን ተሻጋሪ አስቂኝ ትውስታዎች፡- መቼም 2007ዓ.ም እድለኛ ዓመት ነበር ከተባለ ለመጀመሪያ ጊዜ በስልጣን ላይ የሚገኝ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሀገራችንን ለመጎብኘት የመጣበት ዘመን ተብሎ ሊጠራ መቻሉ ብቻ ይሆናል፡፡ እናም ይህን ተከትሎ መሪዎቻችን የቀለዷት ቀልድ ዘመን ዓለሜን ስስቅባት የምኖር አቻ የለሽ ቀልድ ናት፡፡ ይህቺውም ምንድንናት ብትሉኝ ባራክ ኦባማ ወደ ናይሮቢ ከዛም ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት እየተሰናዳ ባለበት ወቅት ያለምንም ኮሽታ ሌላው ቀርቶ ክሳቸውን የያዘው ፍርድ ቤት እንዃን ስለሁኔታው ሳይሰማና ሣያውቅ በክስ መቋረጥ ሰበብ የተወሰኑ የዞን9 ጦማሪያንና ጋዜጠኞችን ከእስር የለቀቁባት ኩምክና ናት እላችኋለሁ!!

እንደው ይቺ ቀልድ መቶ ዓመት የመኖር እድል ቢገኝ መቶውንም ዓመት ጥርስ ታስከድናለች ትላላችሁ? በዚህም ብቻ ያልበቃው ቀልድ ፕሬዝዳንቱ ከተሸኑና ሰንበትበት ካልንም በኋላ በቅርቡ የተወሰኑ ፖለቲከኞችን በነፃ በመልቀቅ ቀጥሏል!! ሲፈልግ ያለበደልህ ያስርሀል፤ ሲያሻው በነፃ ይለቅሀል!! ታድያ ይህን የመሰለ ቀልደኛ ከወዴት ይገኛል?!

የቀልዱ ጨዋታ የገባቸው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማም ጨዋታውን ተቀላቅለው የኛውን ቀላጅ በኢዮቤልዩ ቤተመንግሰት ከፍ ከፍ አደረጉና በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በዝረራ አፈርጠውልኝ ሔዱ’አ!!

ዘመን ሲቀየር አስተሳሰብ አብሮ ላይቀየር፣ ስርአትም ከዘመን ኋሊት ለፈፀመው በደልና ስህተት ከዘመን ፊት ቀርቦ ላይታረምበትና እና ላይጠየቅበት የአዲስ ዓመት ለውጥ የቁጥር መቀየር እና የወቅት ሽግግር አንጂ የዘመን መታደስ ሊሰኝ አንዴት ይቻለዋል?! አሳዛኙ ድርጊት፣ ሐሰቱና አስቂኙ ክንውን አንዲሁም ቀልዱ ለከርሞ አብሮን ሲሻገር እያየን! እውነት እላችኋለሁ አዲስ ዓመት የሚባል የለም አሁንም ነገም አሮጌው ላይ ነን!!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tigestu Firew says

    August 27, 2015 07:28 pm at 7:28 pm

    የዚህ ፅሑፍ ፀሐፊ እይታዎች ሁሌም ይገርሙኛል!! የተለያዩ ፅሑፎቹን በፌስቡክ ገፁ ላይ አንብበያለሁ በጣም ይመቹኛል! ጎለጉል ጋዜጣም ይህ ፅሑፍ ለብዙኀን ተደራሽ ይሆን ዘንድ በጋዜጣው ላይ ማውጣቱ አስደስቶኛል!!

    Reply
  2. አክሊለ says

    September 1, 2015 05:26 pm at 5:26 pm

    ውድ ጎልጉል፣ ይህን ግጥም በዚህ ሊንክ ላይ አንብቤ ስለወደድኩት ልኬላችኋለሁ። የነገ ሰው ይበለን። http://ethiopianchurch.org/en/poems_shorts/242-%E1%88%98%E1%88%B5%E1%8A%A8%E1%88%A8%E1%88%9D%E1%8A%95-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB.html

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule