• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሀገር የማያድስ አዲስ ዓመት ለእኔ ምኔ ነው?!

August 27, 2015 12:26 am by Editor 2 Comments

ዛሬ ላይ የጊዜ ዑደት ተፈጥሮአዊ ልማድ አጃቢና አድማቂ ከመሆን በቀር ዘመን ተሸኝቶ ዘመን ሲተካ አላፊውን ዘመን በመልካምና በበጎ የምንዘክርበት መጪውንም ተስፋ የምናደርግበት አንዳች ተጨባጭና በቂ አመክንዮ (ምክንያት) ያለን መስሎ አይሰማኝም!! ይህን ስል ግን ከእያንዳንዱ ግለሰብ አሊያም ቡድን አንፃር ሳይሆን አንደሀገር ማለቴ ነው፡፡

እነሆ ዳር ላይ ቆመን እንቀበለው ዘንድ የምናሰፈስፍለት የ2008 ዓ.ም በተዳፈነ ዲሞክራሲ የአማራጭ እሳቤ አልባ ወደሆነ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤቶች አስተዳደር ስር የሚዘፍቀን ከዛም ባለፈ ምንአልባትም ሳንሰማና ሳናይ፤ መስማማትና አለመስማማታችንም ሳይታወቅልን በሚደነገጉ የሕግ፣ የደንብ እና የፖሊሲ ድንጋጌዎች የምንዋጥበት ወቅት ጅማሬ ነው ማለት ይቻላል! ለመጠናቀቅና የዘመኑን መቁጠሪያ ወደ 2008 ለመቀየር ጥቂት ቀናት የቀሩት ይህ የ2007ዓ.ም በመሪዎቻችን አጅግ አሳዛኝ፣ አሣፋሪና አስቂኝ ድርጊቶች አንዲሁም ወደር በማይገኝለት ሐሰት የተጨማለቀ ነበር ብዬ ብል ከግነት ይቆጠርብኛል የሚል ግምት የለኝም! ምክንያቱም ሁሉንም እያየንና እየታዘብን ያለፍነው ሐቅ ነውና!

ሕሊናቸውን ሽጠው ሆዳቸውን እየሞሉ ካሉ፤ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጥምቀት የልማታዊ ዲሞክራሲ ማህተብ ካነገቱ ካድሬዎች በቀርስ ማን አጋነንክ ወይም ሐሰት ተናገርክ ብሎ ይከሰኛል??!!

1. አሳዛኞቹ ተግባራት፡- ነገ ላይ በአዲሱ ዘመን አሮጌው ሊሰኝ የሚጣደፈውና ጉደኞች ጉደኛ ያሰኙት 2007ዓ.ም የሰላሳ ወገኖቻችን ደም በሊቢያ በረሐ በአረመኔዎች እጅ በከንቱ መፍሰስን የተመለከትንበትና የሰማንበት መንግሰታችንም ዜጎቹ መሆናቸውን አስኪያጣራ ዓለም ኢትዮያዊያን አንደሆኑ አኛም ወንድሞቻችን መሆናቸውን ቀድመን ያወቅንበትን ሂደት አሳልፈናል፣ የሳሙኤል አወቀ ሰለእውነት የመጮህ ትግል ፍሬ በሐሰተኞች በግፍ የመገደል እጣ ፈንታ መሆኑን ተረድተንበታል፣ በሐይማኖት ነፃነት መብት ለጥያቄዎቻቸው መልስን ለችግሮቻቸው መፈትሔዎቸን ይፈልግ ዘንድ የተቋቋመ ኮሚቴ አባላት የነበሩ የሙስሊም ወገኖቻችን ላይ በተመሰረተ የሽብር ክስ ከ7 እስከ 22 ዓመት የሚደርስ የእስር ፍርድን ተመልክተናል፣ በዩ.ኤስ.ኤ ካሊፎርኒያና በአውስትራሊያ የተከሰተው ዓይነት ድርቅ (ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ለተናገሩት አኔ አፍራለሁ!!) በተወሰነው የሀገራችን አካባቢዎች መከሰቱን አይተናል፤ በእነዚህ ሁሉ 2007 ዓ.ም ሁላችንን አሳዝኖ ወደማለፉ ነው፡፡

2. ወደር አልባው ሐሰትና አስቂኙ ክንውን፡- ከ1987ዓ.ም ጀምሮ አምስት ዓመታትን እየጠበቀ በ2 እና በ7 በሚጨርሱ የዘመን አድሜ ቁጥሮች የሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ 2007ዓ.ም ላይ ሲደረስ ለየለትና በማሩ ፈንታ እሬቱን እና ምሬቱን የጋገረች ንብ መቶ በመቶ ተመርጣለች የሚል ለጆሮ የሚከበድ ትልቅ ሐሰት ተሰማበት፤ ይህን ውሸት የነገረን ምርጫ ቦርዱ ደግሞ የዚህ አስቂኝ የሀሰት ክንውን የስራ ሂደት ባለቤት መሆኑን በቁርጠኝነት አስመሰከረ!

3. የዓመቱ ዘመን ተሻጋሪ አስቂኝ ትውስታዎች፡- መቼም 2007ዓ.ም እድለኛ ዓመት ነበር ከተባለ ለመጀመሪያ ጊዜ በስልጣን ላይ የሚገኝ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሀገራችንን ለመጎብኘት የመጣበት ዘመን ተብሎ ሊጠራ መቻሉ ብቻ ይሆናል፡፡ እናም ይህን ተከትሎ መሪዎቻችን የቀለዷት ቀልድ ዘመን ዓለሜን ስስቅባት የምኖር አቻ የለሽ ቀልድ ናት፡፡ ይህቺውም ምንድንናት ብትሉኝ ባራክ ኦባማ ወደ ናይሮቢ ከዛም ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት እየተሰናዳ ባለበት ወቅት ያለምንም ኮሽታ ሌላው ቀርቶ ክሳቸውን የያዘው ፍርድ ቤት እንዃን ስለሁኔታው ሳይሰማና ሣያውቅ በክስ መቋረጥ ሰበብ የተወሰኑ የዞን9 ጦማሪያንና ጋዜጠኞችን ከእስር የለቀቁባት ኩምክና ናት እላችኋለሁ!!

እንደው ይቺ ቀልድ መቶ ዓመት የመኖር እድል ቢገኝ መቶውንም ዓመት ጥርስ ታስከድናለች ትላላችሁ? በዚህም ብቻ ያልበቃው ቀልድ ፕሬዝዳንቱ ከተሸኑና ሰንበትበት ካልንም በኋላ በቅርቡ የተወሰኑ ፖለቲከኞችን በነፃ በመልቀቅ ቀጥሏል!! ሲፈልግ ያለበደልህ ያስርሀል፤ ሲያሻው በነፃ ይለቅሀል!! ታድያ ይህን የመሰለ ቀልደኛ ከወዴት ይገኛል?!

የቀልዱ ጨዋታ የገባቸው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማም ጨዋታውን ተቀላቅለው የኛውን ቀላጅ በኢዮቤልዩ ቤተመንግሰት ከፍ ከፍ አደረጉና በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በዝረራ አፈርጠውልኝ ሔዱ’አ!!

ዘመን ሲቀየር አስተሳሰብ አብሮ ላይቀየር፣ ስርአትም ከዘመን ኋሊት ለፈፀመው በደልና ስህተት ከዘመን ፊት ቀርቦ ላይታረምበትና እና ላይጠየቅበት የአዲስ ዓመት ለውጥ የቁጥር መቀየር እና የወቅት ሽግግር አንጂ የዘመን መታደስ ሊሰኝ አንዴት ይቻለዋል?! አሳዛኙ ድርጊት፣ ሐሰቱና አስቂኙ ክንውን አንዲሁም ቀልዱ ለከርሞ አብሮን ሲሻገር እያየን! እውነት እላችኋለሁ አዲስ ዓመት የሚባል የለም አሁንም ነገም አሮጌው ላይ ነን!!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tigestu Firew says

    August 27, 2015 07:28 pm at 7:28 pm

    የዚህ ፅሑፍ ፀሐፊ እይታዎች ሁሌም ይገርሙኛል!! የተለያዩ ፅሑፎቹን በፌስቡክ ገፁ ላይ አንብበያለሁ በጣም ይመቹኛል! ጎለጉል ጋዜጣም ይህ ፅሑፍ ለብዙኀን ተደራሽ ይሆን ዘንድ በጋዜጣው ላይ ማውጣቱ አስደስቶኛል!!

    Reply
  2. አክሊለ says

    September 1, 2015 05:26 pm at 5:26 pm

    ውድ ጎልጉል፣ ይህን ግጥም በዚህ ሊንክ ላይ አንብቤ ስለወደድኩት ልኬላችኋለሁ። የነገ ሰው ይበለን። http://ethiopianchurch.org/en/poems_shorts/242-%E1%88%98%E1%88%B5%E1%8A%A8%E1%88%A8%E1%88%9D%E1%8A%95-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB.html

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule