• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የከያኔ ቴዎድሮስ ካሳሁን በሰባ (ሳባ) ደረጃና ቅኔው

September 12, 2014 01:35 am by Editor 6 Comments

“በሰባ (ሳባ) ፈረጃ” ሰሞኑን ከያኔ ቴዎድሮስ ካሳሁን የለቀቀው ነጠላ ዜማ ነው፡፡ የዘፈኑ (የሙዚቃው) በነገራችን ላይ ሙዚቃ የአማርኛ ቃል አይደለም ሚውዚክ የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል በሀገርኛ አማርኛ ሲጠራ ነው ልክ school አስኳላ እንደተባለው ማለቴ ነው፡፡ እናም ቴዲ ይሄንን ነጠላ ዘፈን እንደለቀቀ ያው እንደሚታወቀው ቴዲ ዝም ብሎ ዘፋኝ አይደለምና ማለትም የሥነ-ኪንን ዓላማና የዜግነት ግዴታን ጠንቅቆ የሚያውቅ የተረዳ በሥራዎቹም ላይ በተደጋጋሚ ይሄንን ያሳየ ከያኔ ነውና በዚህ ነጠላ ዜማው “ምን ብሎ ይሆን?” በሚል ጉጉት አድማጩ ያተኮረው በስንኞቹና መልእክታቸው  ላይ ነበር፡፡

ለሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ ይህ ነጠላ ዜማ ቴዲን የማይመጥን ብላሽ ዓይነት ዘፈን ነው የሆነበት፡፡ አንዳንዶችማ ጭራሽ “ቴዲ እንዴት ቢንቀን ነው እንዲህ ዓይነት ፍሬ ፈርስኪ የሆነ ዘፈን በነጠላ ዜማ የቆየውን ያህል ቆይቶ ያውም በአዲስ ዓመት ዋዜማ ወርውሮ የጣለብን? እኛ እሱ የቀበጣጠረውን ሁሉ የግድ መቀበል አለብን እንዴ?” ያሉ አሉ፡፡ ሌሎቹም የቴዲን ችሎታ እስከመጠራጠር በመሄድና ቴዲን በዚህ “ብላሽ” ባሉት ሥራ በመለካት የባልደራሱና የኡኡታየ ደራሲ እሱ አለመሆኑን ለራሳቸው እርግጠኛ የሆኑ አሉ፡፡ ምክንያቱም ይሉና “ያንን የመሰለ የድርሰት ችሎታ ያለው ጭንቅላት እንዲህ ዓይነት ብላሽ ዘፈን አይጽፍም ይላሉ”

ነገሩ ግን ወዲህ ነው ወገኖቸ ቴዲ ከነበረበት ችሎታና አቅም የበለጠ መጠቀ ረቀቀ እንጅ አልወረደም አልተንሸራተተምም፡፡ የእውነቴን ነው የምላቹህ ቴዲ በዚህ ዘፈኑ ቀላል አልተቀኘም፡፡ በእርግጥ የዚህ ዜማ ቅኔ ከዚህ በፊት እንደተቀኘባቸው ዘፈኖቹ እንደ ባለደራሱና ኡኡታየ ዳህላክንና ያሥተሰርያልን ያልጨመርኳቸው ቴዲ በእነዚህኞቹ ማለት የፈለገውን በቅኔ ሳይኖን በግልጽ ያለ በመሆኑ ነው፡፡ እናም እንደ ሁለቱ ማለትን እንደ ባልደራሱና ኡኡታየ ለብዙው ሰው የሚገባ ቅኔ ባለመሆኑ ይህ “በሰባ ደረጃ” የተሰኘው ነጠላ ዜማው ለሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ ግልጽ አልሆነለትም፡፡ እንኳን ለሁሉም አድማጭ ለከያኔያን (ገጣሚያን፣ ባለቅኔዎችና ጸሐፍት) እንኳን ግልጽ ስላልሆነላቸው ስላልገባቸው “እልም ያለ የፍቅር ዘፈን” እንደሆነ አድርገው ነበር ለመሔስ የሞከሩት፡፡

ሌላው ዜጋ ባይረዳው እንኳን ከያኔያኑ ግን ሊረዱት በተገባ ነበር፡፡ ይሄ እንግዲህ ስንኞቹ ምን ያህል የጠጠሩ የረቀቁ እንደሆኑ ነው የሚያሳየው፡፡ እውነቴን ነው የምላቹህ ቴዲ ሊሠራው የፈለገው ዘፈን የፍቅር ዘፈን ቢሆን ኖሮ ለየት ባለ መልኩ ከዚህ በላቀ መልኩ አሳምሮ ጽፎ ባቀነቀነልን ነበር፡፡ ዘፈኑ ሁሉም ሰው ነው እንደሚለው “የፍቅር” ሳይሆን “የሀገር” ስለሆነ ግን ሊያስተላልፈው የፈለገው መልእክትና ሐሳብ ቀይዶ ስለያዘው ዘፈኑ የፍቅር ዘፈንን ያህል አሰኛኘት፣ ቀለም፣ ቃና፣ ድምቀትና ጣእም እንዳይኖረው ሊያደርገው ችሏል፡፡

መቶ በመቶ እግጠኛ ባልሆንም ቴዲ የዚህን ዘፈን ቅኔ ትርጉም ይሄ ይሄ ነው ብሎ እንኳን ለሌላ ሰው ለባለቤቱም እንኳን ነግሯታል ወይም ይነግራታል ለማለት እቸገራለሁ፡፡ ከእሷ ለመደበቅ ፈልጎ ማለቴ ሳይሆን አለ አይደል ተመራምራ ትድረስበት ብሎ እሷን ለማመራመር፡፡

የዚህን ዘፈን ቅኔ ትርጉም ከመተርጎሜ በፊት ቴዲን ይቅርታ ልጠይቅ እወዳለሁ፡፡ እንደሚመስለኝ ቴዲ የዚህን ዘፈን ቅኔ ትርጉም ሊነግረን የሚሻው የሚችለውም ፍትሕ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊ (በይነ-ሕዝባዊ) የመንግሥት አሥተዳደር ባገኘን ጊዜ ይሄ ማለት ይሄ ነው እያለ ለመተርጎም ከራሱ ጋር እንደተቃጠረ እገምታለሁ፡፡ በመሆኑም አሁን በዚህ ጊዜ በማንም ቢሆን መተርጎሙን ይወደዋል ብየ አልገምትም፡፡

ከዚህ አንጻር መተርጎሜ ቅር ሊያሰኘው እንደሚችል ስገምት አስቀድሜ ይቅርታ ልጠይቀው እንደሚገባኝ አመንኩ እናም ቴዲሾ ይቅርታ! መቸም አንድ የሥነ-ኪን ሥራ ለአደባባይ ከበቃ በኋላ አትሒሱብኝ አትተርጉሙብኝ ማለት አይቻልምና ብየ ነው፡፡ ቆይ! ቆይ! ወይም እንዲህ ብናደርግስ? ዝርዝሩን ልተወውና ምሳሌያዊ አገላለጹን (It’s Metaphorical expression) ብቻ ብጠቃቅስስ? አዎ ይሄ ሐሳብ የሚያስማማን ይመስለኛል፡፡

ጥሩ እንግዲህ በዚህም መሠረት በዘፈኑ ውስጥ ያለችው ሴት ገጸ-ባሕርይ (character) ኢትዮጵያ ናት፣ ለገጸ ባሕርይዋ ያለው ፍቅር የሀገር ፍቅር ነው፣ ገጸ-ባሕርይዋ ግድ የለሽ (ኬሬዳሽ) መሆኗ ሀገሪቱ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ አልሰማት ማለቱን በቃ ማለት አለመቻሏን ለማጠየቅ ነው፣ ሰባ (ሳባ) ደረጃ ከሳባ ከቀዳማዊ ምኒልክ እናት እስከ ራስ መኮነን ልጅ ተፈሪ (ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ) ድረስ ያለውን ረጅሙን የሀገራችንን የመንግሥት አሥተዳደር እና አድካሚውን የሥልጣኔን ዳገታማ ጉዞ ይወክላል፣ ክራሩ እንደሚታወቀው ክራር ንዋዬ-ሐቅል ነው (የሽፍታ ንብረት) የእነፋኖ የአርበኞቹ መሸነጫ መቀስቀሻ ማንጎራጎሪያ መሣሪያ ነው እናም ክራሩ የወከለው አርበኝነትን ነው፡፡ ቴዲ ይሄንንም ለማስገንዘብ ሲል “ሄዶ ከኮሪያ ዘማች ሲመለስ፤ ያወሳል ናፍቆቱን በክራሩ ድምጽ” በማለት እነ ካሳ ተሰማን የሚያህል በክራር አንጎራጓሪ የአርበኛ ዘፈን አንጎራጓሪን እፊታችን እንዳለ ያህል እንዲሰማን በማድረግ ሥዕላዊ ትውስታን እንድናይ ያደርገናል፡፡

በሉ “ለአዋቂ አንዲት ቃል ትበቃለች” እንዲሉ በተስማማነው መሠረት በዚሁ ይብቃቹህ፡፡ ስንኞቹ ይሄ ማለት ይሄ ነው እንዲህ ማለት እንዲህ ነው እያሉ ለመተርጎም እንዴት ይመቹ ነበር መሰላቹህ፡፡ ነገር ግን ይሄንን ለማድረግ ሁኔታዎች አይፈቅዱምና እያዘንኩ በዚሁ እቋጨዋለሁ፡፡ አንድ የምነግራቹህ ነገር ቢኖር ግን ቴዲ ያለትርጉም ያስገባት አንዲትም ቃል አለመኖሯን ነው፡፡ ለማንኛውም ነግቶልን በነጻነት እንዲህ ያለው እንዲህ ለማለት ነበር እያልን ለመጨዋወት ያብቃን አሜን!

በመጨረሻም ቴዲቲ ተሳክቶልሀል እጅ ይባርክ ብያለሁ ተባረክ ከያኔ (Artist) ማለት እንዲህ ነው፡፡ በእርግጥ የዚህን ያህል አክብደህ ቅኔውን በማራቅህ ቢከፋኝም ከነዚሁ ቅሬታየ በጣም አደንቅሀለሁ፡፡ በእርግጥ አንድ ከያኔ ነገርን በቅኔ የሚገልጽበት አራት ምክንያቶች ቢኖሩም እኔ ግን በግሌ ሸፋፍኖ መናገር አልወድም በእርግጥ በእኔም ግጥሞችና ጽሑፎች ላይ ቅኔ የለባቸውም ማለቴ አይደለም፡፡ ከአራቱ ምክንያቶች በአንደኛው ምክንያት ማለቴ ነው፡፡ የሆነ ሆኖ ግን እኔ አንጀቴ የሚርሰው በግልጽ ልክ ልኩን በነገርኩት ጊዜ ነው፡፡ ምክንያቱም የነገሩን ቅኔ በጣም በሰወርነው ጊዜ እንዲደርስ የተፈለገው መልእክት እንዲደርሰውና እንዲገነዘበው ለፈለግነው አካል ሳይደርስና ሳይረዳው ይቀራል ብየ ስለማስብ ነው፡፡ እንዲህ ሲሆን ያ የኪነት ሥራ ግቡን ሳይመታ ይቀራል፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. shimon says

    September 13, 2014 11:31 am at 11:31 am

    ቀስተ ደመና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ልጁ የተወለደበት ነበር .. እናልሀ ባለፈው ዓመት አራሱን ሰፋ ሲያደርግ ውስጥ የነበሩ ነዋሪዎችን አስወጥቶዋል .. የቴዲ ዘመዶች ቤቱን ሲለቁ ድሮ ካሳሁን ግርማሞ የፃፋት ግጥም ተገኘች ተዘፈነች .. አንተ የሌለ ቅኔ ለመዝረፍ ዳዴ ትላለህ .. ግጥሙ የድምፃዊና ጋዜጠኛ አባቱ ካሳሁን ግርማሞ ነው አትቀባጥር .. ዳንትል!!

    Reply
  2. Abe says

    September 13, 2014 12:05 pm at 12:05 pm

    TedyAfro fesun bifesam QINE new yemitilut…..bishqoch

    Reply
    • asefa korench says

      September 15, 2014 09:10 am at 9:10 am

      @abe you are bull and u are an ordinary person ,empty mind don’t post as such down graded ideas keshim

      Reply
  3. Woy Zendro says

    September 14, 2014 04:44 am at 4:44 am

    Qoy golguloch gin min nekachihu? Ahun yihen yemesele dingay ras endezih aynet worQ guday lay enditsf tadergalachihu? Be-Teddy “70 dereja” wust Qine ale bilo yelem bilew yetekerakerutin BewQetun yemesaselu TalalaQ bale Qinewochin keneQore bihuala….Qinewun yinegrenal bilen sintebiQ ziba-zinke tantararam yileQibinal ende! Zim billo si’ilun ayisilim! Azimam chibba 😉

    Reply
  4. Amsalu Gebrekidan says

    September 16, 2014 05:17 pm at 5:17 pm

    ለአስተያየታቹህ አመሰግናለሁ አብዛኞቻቹህ አልገባቹህም እንጅ እኮ ያስቀረሁት ነገር የለም፡፡ ቁልፉ ከተሰጣቹህ በኋላ ከፍቶ መግባት ያቅታቹሀል እንዴ? እስኪ እንዲህ አድርጉ የነገርኳቹህን ቁልፍ ቁልፍ ነገሮች ያዙና ዘፈኑን አድምጡት ተስፋ አደርጋለሁ ሁላቹህንም ባይሆን ይገባቹሃል፡፡ ሁላቹህንም ለማለት ያልደፈርኩት አንዳንድ ታሪካዊ ኩነቶችን የማያውቁ ሰዎች ዘፈኑን ሽ ጊዜ ቢያደምጡትም ለመረዳት ስለማይቻላቸው ነው፡፡ አስቀድሜ እንደተናገርኩት ከዚህ በላይ እያንዳንዷን ቃል እንዲህ እንዲህ ነው እያልኩ አብራርቸ መተንተኑ አደጋ ስላለውና ቴዲን ለጅቦች አሳልፎ መስጠት ስለሆነ ነው፡፡ አመሰግናለሁ

    Reply
  5. ተስፋየ says

    September 20, 2014 06:39 am at 6:39 am

    Le ato amsalu ge/kidan
    It looks like that you want to praise Teddy. as far as I am concerned, you are not praise him insteade you want to send him to jail and being languished in Woyanies prison for the second time. What ever he said, we love his him for his lyrics and also for his messages. The way how you said it for those who are naive enough to fallow what you say, it seemed you love his works. But from what you have said you want woyane cadres to check him out about the massage of his new clip. Please, please let us get out from such rut. Stop it. Don’t tel me you love him. We all understand Amharic well. I don’t think we need some self appointed “Turjumans.” We have been paid dare price already. If you love him just tell him “we love you Teddy, keep up the good job”, this will be fine for one who live under AGAZI’s Administration.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule