
ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ዞን ሚኤሶ ወረዳ አሰቦት የተነሳውና የታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-50725/04585 ኢት ቦቴ የነዳኝ መኪና በሁለቱም የነዳጅ ታንከር ውስጥ ከ5 ሚሊየን በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ጭኖ ሳለ በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡
ብዛቱ 23,750 ስቴካ ሻምላን (SHAMLAN) ሲጋራ፣ 863 ስቴካ ሺሻ ጭኖ ወደ ሚሌ መስመር በመጓዝ ላይ እያለ ነው ከህዝብ በደረሰ ጥቆማ አፋር ክልል አዋሽ አርባ ላይ በፌዴራል ፖሊስና የጉምሩክ መረጃ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር የዋለው። ንብረቱም በአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት ገቢ መደረጉን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መነሻውን ምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ሚኤሶ ወረዳ አሰቦት ያደረው ነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪ በሁለቱም የነዳጅ ታንከሮቹ ውስጥ ስቴካ ሻምላን ሲጋራ እና ስቴካ ሺሻውን ጭኖ ወደ ሚሌ መስመር በመጓዝ ላይ እያለ አዋሽ አርባ ላይ በፌዴራል ፖሊስና በጉምሩክ መረጃ ሠራተኞች ተይዟል።
ሚኒሰትሩ አቶ ላቀ አያሌው ተሽከርካሪው ከህዝብ በተሰጠ ጥቆማ አፋር ክልል አዋሽ አርባ ላይ መያዙን ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ ለሚሰጠው ጥቆማ ምስጋና በማቅረብ ይሁኑኑ ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። (ኤፍ.ቢ.ሲ)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
Leave a Reply