በአሁኑ ሰዓት አማርኛ ተናጋሪው ወገናችን ላይ መለኪያ የሌለው ግፍ እየተፈፀመበት ነው። ይህ ግፍ፤ የአማራውን ወገናችን ለማጥፋት ከሚደረግ ወንጀል ሌላ፤ መገንዘቢያ ቀመር የለውም። የዛሬው እስከመቼ ይኼን ጉዳይ ይመለከታል። (የመግለጫው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል) ባሁኑ ሰዓት በአማራው ወገናችን ላይ እየደረሰ ያለው አማራን የማጥፋት ሴራ፤ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የሚካሄደው ተግባር ዋናው አካል ነው። (ክፍል ፪ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ከ “እስከመቼ” የተሰጠ መግለጫ
Archives for March 2013
የትግራይ ህዝብ ስማ!!
ሰሞኑን በውዴታም ይሁን በግዴታ በመቀሌ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ሲጨፍሩ፣ ሲዘሉ፣ ከበሮ እየመቱ የባህላቸውን ዘፈንና ውዝዋዜ ሲያወርዱ አይተናል። ምክንያቱ በግልጽ ባይነገርም ሲደበቅ የነበረው የህወሃት ሃብትና ንብረት ውጤት የሆኑ፣ በልዩ የመንግስት ድጋፍ የተከናወኑ ግዙፍ ተቋሞች በጎዳና ለህዝብ ሲቀርቡም ተስተውሏል። ልማቱ መልካም ነው። ደስ ይለናል። ምንም ተቃውሞ የለንም። ግን መልዕክት አለን። ለማን? ምሬትን፣ ጭቆናና መንገፍገፍ ሲበዛ በፍቃደኛነት በቦንብ ላይ እንደሚያስሮጥ ለሚያውቀው የትግራይ ህዝብ!! የትግራይ ህዝብ ስማ!! ሰሞኑን ይፋ የሆነው የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ሪፖርት የትግራይ ክልል በትምህርት፣ በኤሌክትሪክ፣ በመንገድ፣ በእርሻ፣ በደን፣ በኢንዱስትሪ፣ በጤና፣ ወዘተ ከሌሎች ክልሎች ሁሉ ርቃ መሄዷን ይፋ አድርጓል። … [Read more...] about የትግራይ ህዝብ ስማ!!
የኦህዴድ ምርጫ ውጤት ተራዘመ
ድሮ “ላዩ ካኪ ውስጡ ውስኪ” እየተባለ በኢሰፓ አባላት ዩኒፎርም ይቀለድ ነበር። ዛሬ ደግሞ ኢህአዴግ ተመሳሳይ ልብስ አልብሶ በየክልሉ የሰየማቸውን ፓርቲዎችና አመራሮቻቸውን የተመለከቱ “ስቱኮ” እያሉ እንደሚቀልዱባቸው ተሰምቷል። “ስቱኮ” ግልብጥና ግጭት የበዛበት መኪና ተቀጥቅጦ አልስተካከል ሲል፣ የተገጣጠበና አልመሳሰል ያለ ግድግዳ “በግድ” ለማመሳሰል የሚያገለግል ቶሎ የሚፈረካከስ ጭቃ መሰል የቀለም አይነት ማጣበቂያ ነው። “ኮሚኒስቶች በችግርና በቅራኔ ውስጥ ሆነው በግድ ለመመሳሰል አንድ ዓይነት መለያ መልበስ ይወዳሉ። ኢህአዴግም በተመሳሳይ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ሳለ፣ ለተመልካችና ለካሜራ ተመሳሳይ ልብስ ለብሶ በግድ አንድ ነኝ ሲል ማየቱ ብዙም የሚገርም አይደለም” የሚለው አስተያየት በስፋት እየተሰጠ ነው። “በግድ አንድ” ሆነው በየክልሉ ስብሰባ የሚያካሂዱት እህት ፓርቲዎች … [Read more...] about የኦህዴድ ምርጫ ውጤት ተራዘመ
ህጻናት እየራባቸው መማር አቅቷቸዋል!
ህጻናት እየራባቸው ትምህርት መማር እንዳቃታቸው ሸገር አዲስ ኤፍ ኤም ያነጋገራቸው መምህራንና ተማሪዎች ተናገሩ። ሸገር ያነጋገራቸው ተማሪዎች በየተራ እንደተናገሩት በምግብ ችግር ትምህርታቸውን መከታተልና ክፍል ውስጥ ትኩረት ማድረግ ተስኗቸዋል። “ሌሎች ምሳ ያላቸው ምሳ ሲበሉ እኔ የቤት ስራ እሰራለሁ። ወይም ቤተክርስቲያን እሄዳለሁ” በማለት አንድ ተማሪ ሲናገር፣ ሌላኛው ምሳ የሚባል ነገር እንደማያውቅ ገልጿል። በርሃብ ምክንያት ትምህርታቸውን በወጉ መከታተል ያልቻሉ ተማሪዎች ጉዳይ እንዳሳሰባቸው መምህራኑ ሲናገሩ ሸገር አስደምጧል። በሰሙት ዜና ረፍት ያጡ በርካታ ወገኖች ስልክ በመደወል ተማሪዎቹ በትምህርት ቤታቸው ውስጥ የምሳ አገልግሎት እንዲያገኙ የበኩላቸውን ለማድረግ ሲነጋገሩና ቃል ሲገቡ ለመስማት ተችሏል። አዲስ አበባ በኑሮ ውድነት ሳቢያ የሚበሉ ያጡ፣ በክፍል ውስጥ ረሃብ … [Read more...] about ህጻናት እየራባቸው መማር አቅቷቸዋል!
ከእሁድ እስከ እሁድ
"ፀላእትና ክንከራታትሞም ኢና" "ህወሓትን እናስቀድም ... 'ጠላቶቻችንን እናውድም'!" ሦስት ቀናት የፈጀው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ ትናንት ተጠናቋል። ለጉባኤው የሚሆን ኣጀንዳ ለመለየትና ልዩነታቸው ለማጥበብ ህወሓቶች ሲነታረኩ ቆይተው ቀጣዩ 11ኛ የህወሓት ድርጅታዊ ጉባኤ በሰላም ለማጠናቀቅ የተስማሙ ይመስላሉ ሲል ኢትዮ ሚዲያ መድረክ የመቀሌ ዘጋቢውን አብርሃም ደስታን ጠቅሶ ዘገበ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በሁለት ተከፍለው ዘለፋና የጠብ መንፈስ የተሞላበት ጭቅጭቅ ከተካሄደ በኋላ ሌላ ሦስተኛ ቡድን ተፈጥሮ “ህወሓትን እናስቀደም፣ ልዩነታችን ወደ ጎን ትተን የጋራ ጠላቶቻችንን እንታገል፣ ሁለታቹ (ቡድኖቹ) የህዝብ ድጋፍ የላችሁም፤ ስለዚህ በሁለት ከተከፈልን ህወሓት ህልውናው ያበቃል።” በሚል ተማጽኖ ማሰማታቸውን ድረገጹ አመልክቷል። በዶ/ር ቴድሮስ ኣድሓኖም የተመራ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
Appeal To Pope Francis I Re: A Vatican Justice Delayed For Over 75 Years
March 19, 2013 His Holiness Pope Francis I The Vatican Rome. Your Holiness, Please allow me, Your Holiness, to express, in the most respectful and sincere manner, my heartfelt congratulations on your historic election as the prelate of the apostolic Catholic Church. My delight is strengthened further by the international acclamation of your election as well as the recognition of your abiding concern for the poor of the earth as well as respect for human rights and justice. I would like to … [Read more...] about Appeal To Pope Francis I Re: A Vatican Justice Delayed For Over 75 Years
ኢትዮጵያ በ21ኛው ክፍለ ዘመን
‹‹የሰው ልጆች ሀሉ፣ በነጻነታቸው፣ በከብራቸውና በመብቶቻቸው እኩል ሆነው የተፈጠሩ ናቸው። የማሰብና የኀሊና ችሎታ ስለ ታደሉ እርስ በርሳቸው፣ በወንድማማችነት፣ መንፈስ ሊተያዩ ይገባል።›› ዓለም አቀፍ የሰብአቂ መብቶች አዋጅ ለአንድ አፍታ፤ ለትንሽ፤ ደቂቃ፣ እባክችሁን፣ ልባችሁን፣ ሰጡኝ። „የመጀመሪያው ትውልድ፣ አገር ይገነባል፣አንድነትን ያጠነክራል። ነጻነትንም በጠላት እንዳይነጠቅ፣ይጠብቃል። ሁለተኛው፣ትውልድ፣ ቁጭ ብሎ ይበላል። ተቆጭ፣መካሪና ተቃዋሚ የሌለው ሦሰተኛ ትውልድ ደግሞ እናት አገሩን ይሸጣል። የተቀረው፣ የተወናበደው ትውልድ ደግሞ፣ አባቶች እንደሚሉት፣ የወሬ ቡዋልተኛ ሁኖ፣ አብሮ ተፈቃቅሮ፣ መሥራቱን ጥሎ፣ እርስበራሱ፣ እነደ አውሬ፣ ይቦጫጨቃል። በመጨረሻውም፣ ሁሉም ባሪያ ሁነው ፣ ይጋዛሉ። የትም ቦታ ወድቀውም ይቀራሉ።“ ይህ ብዙ ቦታ፣ከጥንት ጀምሮ፣ የሚታይ፣ … [Read more...] about ኢትዮጵያ በ21ኛው ክፍለ ዘመን
2nd Annual International Ethiopian Women Conference
Naked TPLF Fascism exposed
As the United Nations fails to declare the current ethnic Apartheid rule in Ethiopia a crime against humanity and as the ICC remains reluctant to charge hordes of Tigre warlords for genocide and war crimes committed over the course of 21 years of brutal minority rule, flagrant human rights violations are spiraling out of control in lawless Ethiopia Where federal police members and feared Tigre People Liberation Front, TPLF, cadres go as far as dousing non- Tigre citizens with petrol and set … [Read more...] about Naked TPLF Fascism exposed
የማን ሆነሽ ትባርኪያለሽ
"እስቲ እቺን ብላልኝ፣ እቺንም ጠጣልኝ፣ ብሎ አሳድጎኝ፤ ኧረ ለመሆኑ 40 ዓመት ሲሞላው ላባት ልጅ ኣይደርስም ማን ይሆን ያለው ፣ (ሙሉው ግጥም እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about የማን ሆነሽ ትባርኪያለሽ