የዐለማችን ሁኔታ በጣም እየተወሳሰበ መጥቷል። በየአገሮች ውስጥ የማህበራዊና የፖለቲካ ጥያቄዎች ሳይፈቱ የሃይማኖት ጥያቄ ራሱን የቻለ አጀንዳ ሆኖ በመምጣት ብዙ አገሮችን እያተራመሰ ነው። በተለይም የሶስተኛው ዓለም ተብለው በሚጠሩ አገሮች ውስጥ ያለው የፖለቲካ አወቃቀር ምሁራዊ ብስለት ስለሚጎድለው፣ አፍጠው አግጠው የሚመጡ እንደ ሃይማኖት የመሳሰሉ ጥያቄዎችን በውውይትና በክርክር ከመፍታት ይልቅ ግብግቡ ወደ አመጽ በማምራት አክራሪዎች በሚባሉትና በመንግስታት መሀከል የሚደረግ ዐይነት ፍጥጫ እየሆነ በመምጣት ላይ ነው። መንግስታት ወደ ዕምነት ያመራውን የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል በጭፍኑ በአክራሪነት በመወንጀል በተለኮሰው እሳት ላይ ቤንዚን እየነሰነሱበት ነው። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ሃይማኖት፣ ፖለቲካና ህብረተሰብ!
Archives for March 2013
የትናንቷን እሁድ በወፍ በረር ስንቃኛት
ዛሬ እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር እሁድ መጋቢት 15 ቀን 2005ዓ.ም ነው፡፡ የዚህችን ዕለት ውሎየን ነው እንግዲህ የማካፍላችሁ፡፡ እኔም እንዳቅሜ የቤተሰቤን ፍላጎት አፍኜ አልጀዚራን ብቻ በመክፈት በማየው ነገር ሁላ በንዴት ስፎገላ ነው የትም ሳልሄድ ቤቴ ተከርችሜ የዋልኩ፡፡ እርግጥ ነው ከሰዓት በኋላ የኢትዮጵያንና የቦትስዋናን የዓለም እግር ኳስ አፍሪካዊ የማጣሪያ ጨዋታ ተከታትያለሁ - ሀገሬ አንድ ለዜሮ በማቸነ‹ፏ›ም ተደስቻለሁ፡፡ የተቀረውን ግን አታንሱት - እኔ ግን ላነሳው ነኝ፡፡ (አይ የኛ ሀገር ነገር! በ‹ቸ›ና በ‹ሸ› አጠቃቀም ሳይቀር እንናቆር ነበር እኮ! ምን ቢዞርብን ይሆን!) በነገራችን ላይ ዘመነ ምፅዓት አሁን ካልሆነ መቼም አይሆንም፡፡ ይህ ድምዳሜየ በዛሬው ውሎዬ ብቻ የተደረሰበት እንዳይመስላችሁ - ዛሬ አጠናከረልኝ እንጂ የቆዬ ነው፡፡ በዚያ ላይ በለሲቱ … [Read more...] about የትናንቷን እሁድ በወፍ በረር ስንቃኛት
ነጋሶ ሞገቱ ወይስ ተሞገቱ?
“ ... አንተም ሆንክ ማንም ኢትዮጵያዊ ውጪ ያሉትን ጨምሮ ቢደግፉን ደስ ይለናል። በዚህ መንገድ ሂዱ ብለው እንዲጠመዝዙን ግን አንፈልግም። … ሰላማዊ ትግል የምትሉት ለውጥ አያመጣም ይሉናል። እንደዚህ የምትሉ ከሆነ ከፈለጋችሁ ገንዘብ አትርዱን እንላቸዋለን … ኢህአዴግን እንደ መንግስት እውቅና አንሰጠውም" ከዶ/ር ነጋሶ የተመረጡ መልሶች መካከል የተጠቀሱ ናቸው። በዚህና በሌሎች ምክንያቶች ዶ/ር ነጋሶ ሊሞገቱ ሄደው ሞገቱ የሚል ርዕስ ለጽሁፌ መረጥኩ። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አንድነትን በመወከል ሬዲዮ ፋና በሚያዘጋጀው የ"ሞጋች" ቃለ ምልልስ ክፍለ ጊዜ ላይ ተገኝተው ነበር። ቃለ ምልልሱ ከመጀመሩ በፊት "ጋዜጠኛው" ፕሮግራሙ ፈረንጆቹ እንደሚሉት "ሃርድ ቶክ አይነት ነው" አለ። ይህን ጊዜ ቀልቤን ሳበኝ። የቢቢሲው የሃርድ ቶክ ክፍለጊዜና የጠያቂው ጠልቆ የመግባት ችሎታ ታየኝና ዶ/ር … [Read more...] about ነጋሶ ሞገቱ ወይስ ተሞገቱ?
ከእሁድ እስከ እሁድ
አንድ ላስቲክ ውሃ 10 ብር!! በአፋር የቡሬ ነዋሪዎች ለከፍተኛ የውሃ ችግር መዳረጋቸውን ውሃ የሚሸጥበትን ላስቲክ በፎቶ በማያያዝ የጎልጉል የአይን ምስክር ከስፍራው አስታውቋል። በክልሉ የጎልጉል ተከታታይ የሆኑ እንደገለጹት በመጠጥ ውሃ ችግር እየደረሰ ያለው ችግር ከፍተኛና ህይወትን የሚፈታተን ነው። አካባቢው የጦር ቀጠና ከመሆኑ አንጻርና የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር አሳሳቢ እንደሆነ ያስታወቀው የአይን ምስክር "እባካችሁ የሚሰማ ካለ ንገሩልን" ሲል ጥሪ አስተላልፏል። የውሃ ችግር ጊዜ የሚሰጥ ባለመሆኑ አንድ ላስቲክ ውሃ 10 ብር ለመግዛት መገዳዳቸውን፣ በዚህም ቢሆን እንደ ልብ ማግኘት እንደማይቻል አመልክቷል። በስፍራው ያለውን የውሃ ችግር አስመልክቶ ሎጊያ የሚገኝ ጎልጉል የአይን ሪፖርተር አስተያየቱን እንዲሰጠን ጠይቀነው የበኩሉን ማጣራት ካደረገ በኋላ ችግሩ መኖሩን … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
እውነት! የገብሬል ለት!
በገብሬል ዋዜማ፣ መጋቢት 18 ቀን 2005 ዓ ም፣ የእነስክንድር ይግባኝ ቀጠሮ የተያዘበት ዕለት ነው። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about እውነት! የገብሬል ለት!
ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የተሰጠ መግለጫ
ቀን፤ 21/03/2013 ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በUK እና በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሁሉ። የተቀበሉትን የክህነት ኃላፊነት ጠብቀው በንጽሕና በመቆም እግዚአብሔርንና ሰውን ከማገልገል ይልቅ ሥጋዊ ጥቅምን አስቀድመው የተነሱ ጥቂት የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ካህናት በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ በሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና በምእመኑ መካከል ጸብና ጥላቻ ቀስቅሰው ሁከት እንዲሰፍን በማድረግ ባለፈው ሳምንት ለንደን ወደ ሚገኘው የኢህአዲግ መንግሥት ኤምባሲ በመሄድ ቤተ ክርስቲያንን ያህል ነገር እንደ ግል ንብረት ለማስረከብ እንፈልጋለን በማለት ከጠየቁ በኋላ ከዛ በማስከተል ቤተ ክርስቲያኗን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በመባል በኢህአዲግ መንግሥት ጣልቃ … [Read more...] about ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የተሰጠ መግለጫ
Graziani and the TPLF, an Ethiopian saga.
‘The Duce will have Ethiopia, with or without the Ethiopians’. Rodolfo Graziani I am writing this as a proud Ethiopian because Graziani’s promise to the Fascist dictator was thwarted by my gallant ancestors. If it was not for the bravery and sacrifice of our grandparents, to day our country will be referred to as ex Italian Colony, we will be conversing in Italian, our national dish would be spaghetti and my name will probably be Mario. Please don’t knock it because my country being referred to … [Read more...] about Graziani and the TPLF, an Ethiopian saga.
World Bank told to investigate links to Ethiopia ‘villagisation’ project
An independent panel has called for an investigation into a World Bank-funded project in Ethiopia following accusations from refugees that the bank is funding a programme that forced people off their land. In a report, seen by the Guardian, the inspection panel – the World Bank's independent accountability mechanism – calls for an investigation into complaints made by refugees from the Anuak indigenous group from Gambella, western Ethiopia, in relation to the bank's policies and … [Read more...] about World Bank told to investigate links to Ethiopia ‘villagisation’ project
“የህዳሴው ግድብ” ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም
“በራሳችን መሐንዲስ፣ በራሳችን ገንዘብ፣ በራሳችን የተባበረ ክንድ እንገነባዋለን" በማለት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመስቀል አደባባይ ታላቅ ህዝባዊ ድጋፍና "መዓበላዊ መነቃቃት" ፈጠሩበት የተባለለት የ"ህዳሴው" ግድብ 51 በመቶ ድርሻ የኢትዮጵያ እንዳልሆነ ነዋሪነታቸው በአውሮፓ የሆነ ዲፕሎማት በተለይ ለጎልጉል ገለጹ። ስማቸው ምስጢር እንዲሆን የጠየቁት ዲፕሎማት እንዳሉት 51 በመቶ ባለድርሻ የሆነችው አገር አውሮፓ የምትገኝ የኢትዮጵያ አጋር አገር ናት። ለጊዜው የባለድርሻዋን አገር ስም መግለጽና የውሉን ዝርዝር ይፋ ማድረግ ያልፈለጉት ዲፕሎማት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ የፈለገችውን ውሳኔ በራስዋ ለማስተላለፍ እንደማትችል፤ ያላት ድርሻ 49 በመቶ ብቻ በመሆኑ ድምጽን በድምጽ በሚሽረው በአብላጫ ድምጽ ህግ መሰረት በግድቡ ላይ የሚወሰነው ውሳኔ 51 በመቶ ባለድርሻ በሆነችው … [Read more...] about “የህዳሴው ግድብ” ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም
“የመለስ አስተምህሮት” ጉባኤ ታዳሚዎች
ኦህዴድ ዘግይቶ ምርጫውን ይፋ ያደረገበት ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ባህር ዳር ለሚካሄደው ዘጠነኛው የኢህአዴግ ጉባኤ የተሰየሙትን የየድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስም ዝርዝር ኢህአዴግ ይፋ አድርጓል። ጉባኤው "በመለስ አስተምህሮዎች ጠንካራ ድርጅትና የልማት ሃይሎች ንቅናቄ ለህዳሴያችን" በሚል መሪ ቃል ከቅዳሜ ጀምሮ በባህር ዳር ከተማ ነው የሚካሄድ ሲሆን ጉባኤው አራት ቀናት እንደሚፈጅ ይፋ ተደርጓል። በጉባኤው ያለፉት ሁለት ዓመታት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈጻጸምና ቀጣይ እቅዶች ላይ ይወያያል፣ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ምርጫን አስመልክቶ በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ ይኖራል ተብሎ እንደማይጠበቅ ከወዲሁ ለማወቅ ተችሏል። ፋና ያወጣው የኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር እንደሚከተለው ነው፡፡ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ … [Read more...] about “የመለስ አስተምህሮት” ጉባኤ ታዳሚዎች









