• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ብሄድም እመለሳለሁ”

June 13, 2015 05:33 am by Editor 3 Comments

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አራተኛ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ዌንዲ ሸርማን ሰኔ 23፤ 2007 ዓም ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ከተሰማ ጥቂት ሳምንታት የተቆጠሩ ቢሆንም ተመልሰው በከፍተኛ ባለሥልጣንነት ሊመጡ እንደሚችሉ ተጠቆመ፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ሸርማን በወቅቱ ከቴድሮስ አድሃኖም ጋር ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ያሰሙት ንግግር ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው ነበር፡፡

ባለሥልጣኗ ፈጽሞ ባልተጠበቀ ሁኔታ ለኢህአዴግ በካድሬ ደረጃ ሙገሳ ቸረው ነበር፡፡ ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ ያለውን ህዳሴ ካወደሱ በኋላ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጠ አስተዳደር ሥር እንዳለች ተናግረው ነበር፡፡ በመቀጠልም ይህንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠን በኃይል ለመጣል የሚንቀሳቀሱ በሙሉ ሊጠነቀቁ እንደሚገባቸው አሳሰቡ፡፡ ሲቀጥሉም ግንቦት ሰባትን በስም በመጥራት ሌሎችንም የኃይል እርምጃ በመውሰድ ለውጥ ለማምጣት ለሚፈልጉት ኃይላት ሁሉ “አሸባሪዎች” ናችሁ የሚል መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ከዚህ የዌንዲ ሸርማን ንግግር በኋላ በተለይ በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡ ካቀረቧቸው ጥያቄዎችም መካከል ባለሥልጣኗ ይቅርታ እንዲጠይቁ፣ ከሥልጣን እንዲነሱ፣ ወዘተ የሚሉት ጥቂቶቹ ነበሩ፡፡

ለሳምንታት የዘለቀው ተቃውሞ ጋብ እንዳለ ባለፈው ሰሞን ዌንዲ ሸርማን አሁ ካሉበት ሥልጣን ሰኔ 23 (ጁን 30) እንደሚለቁ ደብዳቤ አስገብተው መጽደቁን ይፋ አደረጉ፡፡ አለቃቸው ጆን ኬሪና ፕሬዚዳንት ኦባማ የሸርማንን ታላቅነትና የአገልግሎት ዘመን በማወደስ ታላቅ ሙገሳን ቸሯቸው፡፡

ዜናው በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የተቀናጀ ትግል ውጤት እንደሆነ ተደርጎ ሲወሰድ ተሰምቷል፡፡ በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት ላይ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት ተጽዕኖ እንዳለ ሆኖ የዌንዲ ሸርማን አሁን ከሥልጣን መልቀቅ ምናልባት ራሳቸውን ለከፍተኛ ሥልጣን ለማዘጋጀት ነው የሚሉም አሉ፡፡

በቢል ክሊንተን የአስተዳደር ዘመን በውጭ ጉዳይ መ/ቤት ሥራቸውን የጀመሩት ሸርማን፤ የሒላሪ ክሊንተን የቅርብ ወዳጅ ናቸው፡፡ ሸርማን አሁን ላሉበት ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ በ2011ዓም ብቁ ያደረጓቸው በወቅቱ የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱን የመሩት ሒላሪ ክሊንተን ነበሩ፡፡ ወ/ሮ ክሊንተን በመጪው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ከሁሉም በብቃት ላይ የሚገኙ ተወዳዳሪ ሆነው ቀርበዋል፡፡ የማሸነፋቸውም ዕድል ከፍተኛ እንደሆነ በብዙዎች እየተጠቆመ ነው፡፡

ዌንዲ ሸርማን ባሁኑ ወቅት ከሥልጣን የለቀቁበት ተደርጎ የተወሰደው ቀዳሚው ምክንያት የኑክሌር መሣሪያዎችን በተመለከተ ከኢራን ጋር ይካሄድ የነበረው ድርድር ወደ መጨረሻው በመድረሱና ሴኔቱ ረቂቅ ሕጉን በማጽደቁ እንደሆነ በስፋት ተነግሯል፡፡ ሆኖም ግን የርሳቸው ቦታ ለኑክሌር ድርድር ተብሎ ብቻ የተቀመጠ የሥልጣን እርከን እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡

ከክሊንተን ቤተሰብ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላቸው የሚነገረውና በኒውዮርክ ከታዋቂ ይሁዲ ቤተሰብ የሚወለዱት ሸርማን ሒላሪ ክሊንተንን በምርጫ ዘመቻቸው ላይ የውጭ ጉዳይን በተመለከተ በማማከርና በመሥራት ሊያገለግሉ ይችላሉ ከሚለው አስተያየት አኳያ ምናልባት ከሥልጣን መልቀቃቸው ታስቦ የተደረገ ነው የሚሉም አሉ፡፡ ይህ ከሆነ እና ሒላሪ ክሊንተን የፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን አሸንፈው ነጩ ቤተመንግሥት የገቡ ዕለት ለከፍተኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ወይም በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደርነት የሚሾሙት ዌንዲ ሸርማንን ሊሆን ይችላል፡፡

አሁን ከሥልጣን ሲለቁ ወደ መንግሥታዊ የሥልጣን እርከን የማይመለሱ የመሰለው የዌንዲ ሸርማን ጉዳይ ቀን ጠብቆ የተቃዋሚውን ኃይል ይበልጥ ሊጎዳ የሚችል እንደሆነ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የጠቆሙ ገልጸዋል፡፡ ምክንያቱም እርሳቸው አሁን ከኢህአዴግ ጋር ካላቸው ይህንን የመሰለ ቁርኝት አኳያ ወደፊት ከፍ ያለ ሥልጣን ይዘው ብቅ ካሉ በተቃዋሚው ኃይል እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጡት ተጽዕኖ እጅግ የከፋና የከረረ ሊሆን ይችላል፡፡

“ብሄድም እመለሳለሁ” የሚመስለው የዌንዲ ሸርማን የሥልጣን መልቀቅ ጉዳይ ከአሜሪካ የፖለቲካ አዘዋወር ጋር ወደፊት በሂደት የሚታይ ቢሆንም የተቃዋሚው ኃይል በተለይ በውጭ ያለው አስቀድሞ ሊሰራው የሚገባው የቤት ሥራ እንዳለ ጠቋሚ ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. melak says

    June 13, 2015 04:34 pm at 4:34 pm

    Let she come again. We will wait her under a strong Ethiopia, or if delayed somehow, on the road towards a strong Ethiopia. America is committing another historical blunder in Ethiopia and East Africa. But I don’t think USA is ignorant of the current political, economic, and social situation unfolding in the country very fast today. What matters is only unity among Ethiopians for a shared goal-overthrowing woyane to begin with.

    Ethiopia will rise again!!! Green, Yellow, and Red

    Reply
  2. Terminator says

    June 13, 2015 11:18 pm at 11:18 pm

    As in Ethiopian I will not vote for Mrs, Clinton because of the vote she while she was a senator for Ethiopian HR 2003 .not only that it her husband who put the infuriate complex ridden Tygerias in power for 24 years not only that he took 20 million dollars from Al modie in the name of charity.

    Reply
  3. Jonathan Takele says

    June 14, 2015 12:43 pm at 12:43 pm

    Shalom Ethiopians in USA:- I recommand the system like the Jewish and Isralis did, Ethiopians in USA almost 2.5 millions according to some datasn out of this data almos 1 milion they have USA citizenship and have full right to do vote for both parties so the answer on your hand just the next general election do your homework don’t give up your voice both of the parties start the campaign soon.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule