• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ “ሰላይ” ነው – ዲና ሙፍቲ

June 5, 2015 08:30 am by Editor 3 Comments

* “አቶ መለስ በጣም ይናፍቁናል”

አሸባሪነት በኢትዮጵያ ሊስፋፋ ያልቻለው ሕዝቡ በሙሉ ሰላይ በመሆኑን ዲና ሙፍቲ አስታወቁ፡፡ ከአገር ተሰድደው የሚውጡት አብዛኛዎቹ ገጠሬ ወጣቶች እንደሆኑና ሟቹ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዳሴ አባት በጣም እንደሚናፍቋቸው ተናገሩ፡፡

ቀድሞ በቃል አቀባይነት ሲሰሩ የነበሩት በአሁኑ ወቅት ደግሞ በኬኒያ ተወካይ የሆኑት አቶ ዲና ሙፍቲ ስታንዳርድ ዲጂታል ከተባለ የኬኒያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎች ድርጅታቸውን በመወከል  ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የአልሸባብና መሰል ታጣቂዎች የአሸባሪነት ተግባር በኢትዮጵያ ለማድረስ ያልቻሉበት ምክንያት ምንድርነው ተብለው ለተጠየቁት ሲመልሱ ሕዝቡ ሰላይ እንዲሆን የሰለጠነ መሆኑን በመጥቀስ ማንኛውንም ተጠርጣሪ ድርጊት ህዝቡ ሲያይ ሪፖርት እንደሚያደር ተናግረዋል፡፡ ሠራዊቱም እስኪበቃው ድረስ በዚህ ትምህርት አእምሮው የተሞላና የተጠመቀ በመሆኑ ጥቃቱ ሊኖር እንዳልቻለ አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእስልምና ትምህርት ወደ አክራሪነት እንዳይሄድ ኢህአዴግ በየመድረሳው ከሚገኙ የሃይማኖት አስተማሪዎች በየጊዜው የሥራ ራፖር የሚያገኝ መሆኑን እንደተጨማሪ ማስረጃ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው እየወጡ በኬኒያ አድርገው ወደ ሊቢያና ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፤ በርካታዎቹ ይሞታሉ፤ በአይሲስ ይታረዳሉ፤ … በማለት ጋዜጠኛው ጥያቄውን ሳይጨርስ አቶ ዲና ፈጠን ብለው እንዲህ አሉ፤ “ወደ ሌሎች አገራት ሲሄዱ የተያዙት አብዛኛዎቹ በሰው አዘዋዋሪዎች እየተባበሉና እየተታለሉ ከአገር የወጡ ናቸው፤ በርካታዎቹ ገጠሬ ወጣቶች ናቸው፤ ከዚህ ሌላ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ባለው ዕድል ተደስተው እየኖሩ ነው፤ ኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የምታካሂድ ዴሞክራሲያዊት አገር ናት እንጂ በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ያለች አይደለም” ብለዋል፡፡

ወደ ኬኒያ ስለሚኮበልሉት ጋዜጠኞች ጉዳይ እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ስድስት ታዋቂ ጦማሪያን እና ሶስት ጋዜጠኞች በእስር ላይ ስለመሆናቸው ለተጠየቁት ዲና ሙፍቲ አሁንም ፈጣን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የሚዲያ ነጻነት ገና በዕድገት ላይ ያለ መሆኑ ያስረዱት አቶ ዲና በጋዜጠኝነት ሽፋን ህዝብን ከህዝብ ጋር ማጋጨትና ለግጭት ማነሳሳት ኢህአዴግ የማይቀበለው መሆኑን በመግለጽ አሁን በኬኒያ በስደት ያሉት እውነተኛ ጋዜጠኞች እንዳልሆኑ ተናግረዋል፡፡ በእስር ስላሉት ደግሞ የህጉ ጉዳይ ሳያልቅ አስተያየት ከመስጠት እንደሚቆጠቡ ገልጸዋል፡፡

“መለስ ይናፍቃችኋል?” ተብለው ሲጠየቁ ዲና ሙፍቲ ለሁሉም የኢህአዴግ ሰዎች መለስ በጣም እንደሚናፈቃቸውና የመለስ ራዕይ እስካሁንም እያበበ እንደሆነ አስረድተዋል፤ ሲቀጥሉም “ከአፍሪካ መሪዎች የራሱ መኪናም ሆነ ቤት ሳይኖረው የሞተ ብቸኛ መሪ መለስ ነበር፤ መለስ የመዋቅር ሰው ነበር እንጂ የራሱን ስብዕና ወይም አምልኮተ መለስ (ፐርሰናሊቲ ከልት) የገነባ አለልነበረም” ሲሉ ለቀድሞው አለቃቸው ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በአዲስ አበባ የተዘረጋው የከተማ ባቡር መንገድ ሥራ ከዛሬ ሶስት ወር በፊት የሙከራ አገልግሎቱን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ የትራፊክ መጨናነቅ በሚያስገርም ሁኔታ መቀነሱ ራሳቸውን ምስክር አድርገው አቶ ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም ከዚህ የባቡር ዝርጋታ ልምድ ኬኒያ ብዙ ልትማር እንደምትችልና የናይሮቢን ከተማ ከተመሳሳይ ችግር ማላቀቅ እንደማያስቸግር አስረድተዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Solomon Dagnahcew says

    June 5, 2015 03:24 pm at 3:24 pm

    “ከአፍሪካ መሪዎች የራሱ መኪናም ሆነ ቤት ሳይኖረው የሞተ ብቸኛ መሪ መለስ ነበር፤ መለስ የመዋቅር ሰው ነበር እንጂ የራሱን ስብዕና ወይም አምልኮተ መለስ (ፐርሰናሊቲ ከልት) የገነባ አለልነበረም” ዲና ሙፍቲ. I don’t think that Dina Mufti didn’t watch the following which was viral on social media in 2013. Click @11:08 into the video and watch https://www.youtube.com/watch?v=9wxHdqf-Es8

    Reply
  2. Ewenetu Yenger says

    June 8, 2015 08:29 am at 8:29 am

    Dina Mufti,

    Melese might not had a car registered in his name. But Ethiopians know very well the immense wealth his wife and daughter and immediate family members do posses. What did they produce to become this rich in the short period of time? nothing beyond stealing in open from Ethiopian people using the power of office the evil MZ was holding. So Dina do not insult our intelligence in this crude manner, it is not nice.

    Reply
  3. Tenager Ewnetu says

    June 9, 2015 03:46 pm at 3:46 pm

    Dina Mufti is delusional. He has started spewing his usual lies. If all who leave Ethiopia are from the country side, how come those who were slaughtered and those who lost their lives in the Mediterranean Sea are all from Addis Ababa , Kirkos, Kasaanchis ? He did not see the mourners and the so called mourners – like his foreign ministers seating in front of the tents ? Further, meles had no car and house ? Because Ethiopia was not and is not his country and hence he expatriated all the Billions of Dollars he looted.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule