• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ “ሰላይ” ነው – ዲና ሙፍቲ

June 5, 2015 08:30 am by Editor 3 Comments

* “አቶ መለስ በጣም ይናፍቁናል”

አሸባሪነት በኢትዮጵያ ሊስፋፋ ያልቻለው ሕዝቡ በሙሉ ሰላይ በመሆኑን ዲና ሙፍቲ አስታወቁ፡፡ ከአገር ተሰድደው የሚውጡት አብዛኛዎቹ ገጠሬ ወጣቶች እንደሆኑና ሟቹ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዳሴ አባት በጣም እንደሚናፍቋቸው ተናገሩ፡፡

ቀድሞ በቃል አቀባይነት ሲሰሩ የነበሩት በአሁኑ ወቅት ደግሞ በኬኒያ ተወካይ የሆኑት አቶ ዲና ሙፍቲ ስታንዳርድ ዲጂታል ከተባለ የኬኒያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎች ድርጅታቸውን በመወከል  ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የአልሸባብና መሰል ታጣቂዎች የአሸባሪነት ተግባር በኢትዮጵያ ለማድረስ ያልቻሉበት ምክንያት ምንድርነው ተብለው ለተጠየቁት ሲመልሱ ሕዝቡ ሰላይ እንዲሆን የሰለጠነ መሆኑን በመጥቀስ ማንኛውንም ተጠርጣሪ ድርጊት ህዝቡ ሲያይ ሪፖርት እንደሚያደር ተናግረዋል፡፡ ሠራዊቱም እስኪበቃው ድረስ በዚህ ትምህርት አእምሮው የተሞላና የተጠመቀ በመሆኑ ጥቃቱ ሊኖር እንዳልቻለ አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእስልምና ትምህርት ወደ አክራሪነት እንዳይሄድ ኢህአዴግ በየመድረሳው ከሚገኙ የሃይማኖት አስተማሪዎች በየጊዜው የሥራ ራፖር የሚያገኝ መሆኑን እንደተጨማሪ ማስረጃ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው እየወጡ በኬኒያ አድርገው ወደ ሊቢያና ሌሎች አገራት ይሰደዳሉ፤ በርካታዎቹ ይሞታሉ፤ በአይሲስ ይታረዳሉ፤ … በማለት ጋዜጠኛው ጥያቄውን ሳይጨርስ አቶ ዲና ፈጠን ብለው እንዲህ አሉ፤ “ወደ ሌሎች አገራት ሲሄዱ የተያዙት አብዛኛዎቹ በሰው አዘዋዋሪዎች እየተባበሉና እየተታለሉ ከአገር የወጡ ናቸው፤ በርካታዎቹ ገጠሬ ወጣቶች ናቸው፤ ከዚህ ሌላ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ባለው ዕድል ተደስተው እየኖሩ ነው፤ ኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የምታካሂድ ዴሞክራሲያዊት አገር ናት እንጂ በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ያለች አይደለም” ብለዋል፡፡

ወደ ኬኒያ ስለሚኮበልሉት ጋዜጠኞች ጉዳይ እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ስድስት ታዋቂ ጦማሪያን እና ሶስት ጋዜጠኞች በእስር ላይ ስለመሆናቸው ለተጠየቁት ዲና ሙፍቲ አሁንም ፈጣን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የሚዲያ ነጻነት ገና በዕድገት ላይ ያለ መሆኑ ያስረዱት አቶ ዲና በጋዜጠኝነት ሽፋን ህዝብን ከህዝብ ጋር ማጋጨትና ለግጭት ማነሳሳት ኢህአዴግ የማይቀበለው መሆኑን በመግለጽ አሁን በኬኒያ በስደት ያሉት እውነተኛ ጋዜጠኞች እንዳልሆኑ ተናግረዋል፡፡ በእስር ስላሉት ደግሞ የህጉ ጉዳይ ሳያልቅ አስተያየት ከመስጠት እንደሚቆጠቡ ገልጸዋል፡፡

“መለስ ይናፍቃችኋል?” ተብለው ሲጠየቁ ዲና ሙፍቲ ለሁሉም የኢህአዴግ ሰዎች መለስ በጣም እንደሚናፈቃቸውና የመለስ ራዕይ እስካሁንም እያበበ እንደሆነ አስረድተዋል፤ ሲቀጥሉም “ከአፍሪካ መሪዎች የራሱ መኪናም ሆነ ቤት ሳይኖረው የሞተ ብቸኛ መሪ መለስ ነበር፤ መለስ የመዋቅር ሰው ነበር እንጂ የራሱን ስብዕና ወይም አምልኮተ መለስ (ፐርሰናሊቲ ከልት) የገነባ አለልነበረም” ሲሉ ለቀድሞው አለቃቸው ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በአዲስ አበባ የተዘረጋው የከተማ ባቡር መንገድ ሥራ ከዛሬ ሶስት ወር በፊት የሙከራ አገልግሎቱን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ የትራፊክ መጨናነቅ በሚያስገርም ሁኔታ መቀነሱ ራሳቸውን ምስክር አድርገው አቶ ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም ከዚህ የባቡር ዝርጋታ ልምድ ኬኒያ ብዙ ልትማር እንደምትችልና የናይሮቢን ከተማ ከተመሳሳይ ችግር ማላቀቅ እንደማያስቸግር አስረድተዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Solomon Dagnahcew says

    June 5, 2015 03:24 pm at 3:24 pm

    “ከአፍሪካ መሪዎች የራሱ መኪናም ሆነ ቤት ሳይኖረው የሞተ ብቸኛ መሪ መለስ ነበር፤ መለስ የመዋቅር ሰው ነበር እንጂ የራሱን ስብዕና ወይም አምልኮተ መለስ (ፐርሰናሊቲ ከልት) የገነባ አለልነበረም” ዲና ሙፍቲ. I don’t think that Dina Mufti didn’t watch the following which was viral on social media in 2013. Click @11:08 into the video and watch https://www.youtube.com/watch?v=9wxHdqf-Es8

    Reply
  2. Ewenetu Yenger says

    June 8, 2015 08:29 am at 8:29 am

    Dina Mufti,

    Melese might not had a car registered in his name. But Ethiopians know very well the immense wealth his wife and daughter and immediate family members do posses. What did they produce to become this rich in the short period of time? nothing beyond stealing in open from Ethiopian people using the power of office the evil MZ was holding. So Dina do not insult our intelligence in this crude manner, it is not nice.

    Reply
  3. Tenager Ewnetu says

    June 9, 2015 03:46 pm at 3:46 pm

    Dina Mufti is delusional. He has started spewing his usual lies. If all who leave Ethiopia are from the country side, how come those who were slaughtered and those who lost their lives in the Mediterranean Sea are all from Addis Ababa , Kirkos, Kasaanchis ? He did not see the mourners and the so called mourners – like his foreign ministers seating in front of the tents ? Further, meles had no car and house ? Because Ethiopia was not and is not his country and hence he expatriated all the Billions of Dollars he looted.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule