• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኃይል ለማመንጨት የሚረዳ ግንባታ ሊጀመር ነው ተባለ

October 12, 2021 09:52 am by Editor Leave a Comment

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኢነርጂ ከመሬት ውስጥ እንፋሎት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የሚችል ፕሮጀክት ሲሆን፣ የሀይል ማመንጫ ግንባታውን ለማካሄድ መታቀዱን በቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኢነርጂ ድርጅት የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ነዚፍ ጀማል ገልጸዋል።

ነዚፍ ለአዲስ ማለዳ እንዳስታወቁት ይህንን ግንባታ ለማካሄድ ጨረታ የወጣ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት የሀይል ማመንጫው ቁፋሮ ላይ የሚገኝ የግንባታ ሂደት ነው ብለዋል።

በፈረንጆች 2020 የወጣው የመጀመሪያ ጨረታ ሰባት ትልልቅ አለም አቀፍ የተርባይን አምራች ድርጅቶች መወዳደራቸውንና በአሁኑ ሰዓት ኹለት ድርጅቶች ስራውን ተቀብለው ለመስራት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ነዚፍ ጠቁመዋል።

በአሁኑ ሰዓት ጨረታው ላይ በቀረበው የቴክኒክ ብቃት መሰረት ከሰባት ድርጅቶች ውስጥ ኹለት ብቻ የቀሩ ሲሆን፣ በዋናነት ግንባታውን የሚያካሂደው እና በተጠባባቂነት ያለው ድርጅት ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ከእነዚህ ኹለቱ ድርጅቶች ጋር ለመፈራረም በድርድር ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት ነዚፍ በቅርቡ አሸናፊውን ድርጅት ተለይቶ የሚታወቅ ይሆናል ብለዋል።

በፈረንጆቹ 2022 ስራውን ለመጀመር ያቀደው የሀይል ማመንጫው ግንባታ የስራውን ኮንትራት ውል በ2021 ለመጨረስ እቅድ መያዙን አስታውቀዋል።

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ሃይል ለማመንጨት ይረዳል የተባለው ይህ ግንባታ፣ ከመሬት ውስጥ የሚገኘውን የእንፋሎት ሃይል ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ወደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል መስመር ማስገባት የሚችል ነው።

ቱሉ ሞዬ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ የሚገነባ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በሀገሪቷ ያለ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ከሚገነቡ ትልልቅ ግንባታዎች ውስጥ አንዱ ነው።

የጂኦተርማል ኢነርጂ ወደ ስራ ለማስገባት ከ10 ዓመት በላይ ጥናት የተካሄደበት ሲሆን፣ ከኹለት ዓመት በፊት ቁፋሮ በመጀመር ወደ ስራ የገባ የሀይል ማመንጫ ነው።

በፈረንጆች 2020 የተጀመረው የሀይል ማመንጫው የጉድጓድ ቁፋሮ በአሁኑ ሰዓት ኹለት ቁፋሮዎችን በማጠናቀቅ ሶስተኛው ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀምሮ ኹለት ሺሕ ሜትር በላይ መሰራቱን ነዚፍ ጠቁመዋል።

የመጀመሪያው ቁፋሮ የተደረገበት እንፋሎት እየወጣ መሆኑንም ነዚፍ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

ይህን እንፋሎት ምን ያህል ማመንጨት እንደሚችል በውጭ ሀገራት ባለሙያዎች ተጠንቶ፣ መረጃዎች ተሰብስበው ውጤት እየተጠበቀ ይገኛል ብለዋል። ይህ ጉድጓድ ያመነጨው እንፋሎት ላይ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት የሚረዳ ጥናት ሲሆን፣ ጥናቱ ላይ እንፋሎቱ ሳይቋረጥ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቀጥል፣ ስንት ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ሊያመነጭ ይችላል የሚል ነው።

ለመጀመሪያው የሚጠናው ጥናት አጠቃላይ ለሚቆፈሩት ማመንጫ ሀይል መረጃ ለማግኘት ያስችላልም ተብሏል።

ቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል የመንገድ ግንባታ፣ የውሃ ቁፋሮ እና ሌሎች የድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን ከ150 በላይ የስራ እድል የፈጠረ ድርጅት ነው።

ተቋሙ እንደ ድርጅት የተቋቋመው በፈረንጆቹ ታህሳስ 2017 ሲሆን፣ ሳይንሳዊው ጥናት መካሄድ ከጀመረ አስር ዓመታት አስቆጥሯል።

የቱሉ ሞዬ ሃይል ማመንጫ ለመገንባት 850 ሚሊየን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፣ በእንፋሎት ሃይል ማመንጨት የሚያስችሉ 12 ቁፋሮዎች የሚያካሄድበት ነው።

ቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል የሃይል ማመንጫ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል የከርሰ ምድርን እንፋሎት በመጠቀም ሀይል የሚያመነጭ ድርጅት ሲሆን፣ በ2017 ሀይል ለማመንጨት እና ለሀገር ወስጥ ጥቅም ለማዋል እቅድ ይዞ በመስራት ላይ ይገኛል።

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኃይል ጣቢያ፣ በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለ 150 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችል ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ተገንብቶ ወደ ስራ ሲገባ በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ውስጥ በታቀደው በሁለተኛው ምዕራፍ ወደ 150 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ አቅሙን ለማስፋፋት ያስችላል ተብሏል። (ለአዲስ ማለዳ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: geothermal, tulu moye

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule