• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኃይል ለማመንጨት የሚረዳ ግንባታ ሊጀመር ነው ተባለ

October 12, 2021 09:52 am by Editor Leave a Comment

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኢነርጂ ከመሬት ውስጥ እንፋሎት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የሚችል ፕሮጀክት ሲሆን፣ የሀይል ማመንጫ ግንባታውን ለማካሄድ መታቀዱን በቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኢነርጂ ድርጅት የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ነዚፍ ጀማል ገልጸዋል።

ነዚፍ ለአዲስ ማለዳ እንዳስታወቁት ይህንን ግንባታ ለማካሄድ ጨረታ የወጣ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት የሀይል ማመንጫው ቁፋሮ ላይ የሚገኝ የግንባታ ሂደት ነው ብለዋል።

በፈረንጆች 2020 የወጣው የመጀመሪያ ጨረታ ሰባት ትልልቅ አለም አቀፍ የተርባይን አምራች ድርጅቶች መወዳደራቸውንና በአሁኑ ሰዓት ኹለት ድርጅቶች ስራውን ተቀብለው ለመስራት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ነዚፍ ጠቁመዋል።

በአሁኑ ሰዓት ጨረታው ላይ በቀረበው የቴክኒክ ብቃት መሰረት ከሰባት ድርጅቶች ውስጥ ኹለት ብቻ የቀሩ ሲሆን፣ በዋናነት ግንባታውን የሚያካሂደው እና በተጠባባቂነት ያለው ድርጅት ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ከእነዚህ ኹለቱ ድርጅቶች ጋር ለመፈራረም በድርድር ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት ነዚፍ በቅርቡ አሸናፊውን ድርጅት ተለይቶ የሚታወቅ ይሆናል ብለዋል።

በፈረንጆቹ 2022 ስራውን ለመጀመር ያቀደው የሀይል ማመንጫው ግንባታ የስራውን ኮንትራት ውል በ2021 ለመጨረስ እቅድ መያዙን አስታውቀዋል።

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ሃይል ለማመንጨት ይረዳል የተባለው ይህ ግንባታ፣ ከመሬት ውስጥ የሚገኘውን የእንፋሎት ሃይል ወደ ኤሌክትሪክ ሃይል በመቀየር ወደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል መስመር ማስገባት የሚችል ነው።

ቱሉ ሞዬ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ የሚገነባ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በሀገሪቷ ያለ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ከሚገነቡ ትልልቅ ግንባታዎች ውስጥ አንዱ ነው።

የጂኦተርማል ኢነርጂ ወደ ስራ ለማስገባት ከ10 ዓመት በላይ ጥናት የተካሄደበት ሲሆን፣ ከኹለት ዓመት በፊት ቁፋሮ በመጀመር ወደ ስራ የገባ የሀይል ማመንጫ ነው።

በፈረንጆች 2020 የተጀመረው የሀይል ማመንጫው የጉድጓድ ቁፋሮ በአሁኑ ሰዓት ኹለት ቁፋሮዎችን በማጠናቀቅ ሶስተኛው ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀምሮ ኹለት ሺሕ ሜትር በላይ መሰራቱን ነዚፍ ጠቁመዋል።

የመጀመሪያው ቁፋሮ የተደረገበት እንፋሎት እየወጣ መሆኑንም ነዚፍ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

ይህን እንፋሎት ምን ያህል ማመንጨት እንደሚችል በውጭ ሀገራት ባለሙያዎች ተጠንቶ፣ መረጃዎች ተሰብስበው ውጤት እየተጠበቀ ይገኛል ብለዋል። ይህ ጉድጓድ ያመነጨው እንፋሎት ላይ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት የሚረዳ ጥናት ሲሆን፣ ጥናቱ ላይ እንፋሎቱ ሳይቋረጥ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቀጥል፣ ስንት ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ሊያመነጭ ይችላል የሚል ነው።

ለመጀመሪያው የሚጠናው ጥናት አጠቃላይ ለሚቆፈሩት ማመንጫ ሀይል መረጃ ለማግኘት ያስችላልም ተብሏል።

ቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል የመንገድ ግንባታ፣ የውሃ ቁፋሮ እና ሌሎች የድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን ከ150 በላይ የስራ እድል የፈጠረ ድርጅት ነው።

ተቋሙ እንደ ድርጅት የተቋቋመው በፈረንጆቹ ታህሳስ 2017 ሲሆን፣ ሳይንሳዊው ጥናት መካሄድ ከጀመረ አስር ዓመታት አስቆጥሯል።

የቱሉ ሞዬ ሃይል ማመንጫ ለመገንባት 850 ሚሊየን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፣ በእንፋሎት ሃይል ማመንጨት የሚያስችሉ 12 ቁፋሮዎች የሚያካሄድበት ነው።

ቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል የሃይል ማመንጫ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል የከርሰ ምድርን እንፋሎት በመጠቀም ሀይል የሚያመነጭ ድርጅት ሲሆን፣ በ2017 ሀይል ለማመንጨት እና ለሀገር ወስጥ ጥቅም ለማዋል እቅድ ይዞ በመስራት ላይ ይገኛል።

የቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ኃይል ጣቢያ፣ በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለ 150 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችል ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ተገንብቶ ወደ ስራ ሲገባ በሚቀጥሉት አራት ዓመታት ውስጥ በታቀደው በሁለተኛው ምዕራፍ ወደ 150 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ አቅሙን ለማስፋፋት ያስችላል ተብሏል። (ለአዲስ ማለዳ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: geothermal, tulu moye

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule