• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተጠርጣሪ ጥላሁን ያሚና አብዲ አለማየሁ ፍርድ ቤት ቀረቡ

July 24, 2020 05:44 am by Editor Leave a Comment

አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት ጥላሁን ያሚ እና አብዲ አለማየሁ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

በከሰአት በኋላ በነበረው ችሎትም የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ በቡራዩና አዲስ አበባ በተፈጠረ አመጽና ሁከት በደረሰ የሰውና የንብረት ጉዳት የተጠረጠሩ 8 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

በጠዋቱ ችሎት በቀዳሚነት የቀረቡት ጥላሁን ያሚ እና አብዲ አለማየሁ ላይ መርማሪ ፖሊስ የሰራውን የምርመራ ስራ ይፋ አድርጓል።

በዚህም የምስክር ቃል መቀበሉን፣ ወንጀሉ የተፈጸመበት ስፍራን በቴክኒክ ማስረጃ ማረጋገጡን፣ ግብረ አበሮቻቸውን በቁጠጥር ስር አውሎ ምርመራ እየሰራ መሆኑን፣ አርቲስት ሃጫሉ የተገደለበትን ሽጉጥ ከተጠርጣሪዎች ቤት ከተቀበረበት ጓሮ ማውጣቱን እና በምርመራ ማረጋገጡን አስረድቷል፡፡

ከዚህ ባለፈም በተጠርጣሪዎች እጅ ላይ የተገኘ ስልካቸውን ወደ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት መላኩን የአስከሬን ምርመራ ውጤት እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጾ ድርጊቱ የታቀደ መሆኑን በምርመራ ማረጋገጡን ተናግሯል።

ከተጠርጣሪዎቹ በስተጀርባ ያለውን በጥንቃቄ እየመረመረ መሆኑን በመጥቀስም ከኢትዮ ቴሌኮም ያገኘውን በስልካቸው የተላከ ሰፊ መልዕክት እየተነተነ መሆኑን አስረድቷል።

ለተጨማሪ ምርመራም 14 ቀን ጠይቋል።

ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የእስር አያያዛቸው ብርሃን የማያገኙበት መሆኑን አቤቱታ አስመዝግበዋል።

ፍርድ ቤቱም አያያዛቸው እንዲስተካከል ለፖሊስ ትዛዝ በመስጠት ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን በመፍቀድ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለነሃሴ 1 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰቷል።

በሌላ በኩል ከሰአት በነበረ የችሎት ውሎ የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ በቡራዩና አዲስ አበባ በተፈጠረ አመጽና ሁከት በደረሰ የሰውና የንብረት ጉዳት የተጠረጠሩ በጃምባ ሁሴን መዝገብ የተካተቱ 8 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

መርማሪ ፖሊስ ባሳለፍነው ሃምሌ 7 ቀን 2012 ዓ.ም በተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ የሰራውን ምርመራ አቅርቧል።

በዚህም በ5ኛና 6ኛ ተጠርጣሪዎች ላይ የወንጀል ተሳትፎ መለየቱን 10 የተከሳሽ 20 ደግሞ የምስክር ቃል መቀበሉን ገልጿል።

በአዲስ አባባ ገቢዎች ቢሮ፣ መንገዶች ባለስልጣን፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ የደረሰውን አጠቃላይ ከ136 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን ማስረጃ ሰብስቤያለሁም ብሏል።

በቡራዩ በተነሳ ሁከት 4 ሰዎች መሞታቸውን እና አራት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል ጠቁሟል።

ከተለያዩ ተቋማት ማስረጃ ለመሰብሰብ ተጨማሪ ምርመራ ለማከናወን 14 ቀን ተጨማሪ ጊዜ የጠየቀ ሲሆን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃም የተጠቀሰው ምክንያት ተጨማሪ ጊዜ የሚያሰጥ አይደለም ለማሰር ብቻ ነው ሲሉ ተቃውመዋል።

ተጠርጣሪዎች ከቤተሰብ ጋር እንደማይገኛኙ በድጋሚ አቤቱታ አስመዝግበዋል።

ፖሊስም ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን የአቶ በቀለ ገርባ ሁለት ልጆችን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎችን ለቀናል እኛ ለማሰር ብቻ አይደለም እየሰራን ያለነው ለምርመራ ነው ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱም በድጋሚ አያያዛቸው እንዲስተካከል እና ከቤተሰብ ጋር በጥንቃቄ እንዲገናኙ ትዕዛዝ በመስጠት ለፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ሰባት ቀን ጊዜ ፈቅዷል።

የምርመራ ውጤቱን ለመጠባበቅም ለሃምሌ 24 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

በታሪክ አዱኛ፤ ፋና

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: abdi alemayehu, chilot, jawar, jawar massacre, tilahun yami, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule