ኢትዮጵያ ያካሄደችው ምርጫ ተአማኒና ሰላማዊ ነበር ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ተናገሩ።
ታዛቢ ቡድኑ ከምርጫ ቅስቀሳው አንስቶ እስከ ምርጫው እለት ያለውን ሂደት መከታተሉን የጠቀሱት የታዛቢ ቡድኑ መሪ የጸጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በቀር የቅስቀሳ ሂደቱ በፓርቲዎች ዘንድ ፍትሃዊነቱ የተጠበቀ ነበር ብለዋል።
የተመረጡ ጣቢያዎች ላይ ምልከታ አድርገናል ያሉት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ምርጫውን ተዘዋውረን በተመለከትንበት፣ የምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ጥንካሬ ተመልክተናል፣ መንግስት ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን አስፈላጊ የጸጥታ እርምጃ ተግባራዊ አድርጓል ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን ያደረገው ጥረትም የሚመሰገን መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
ምርጫው ከሞላ ጎደል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ነው የተካሄደው ያሉም ሲሆን አንዳንድ ቦታዎች ላይ በተለይም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች እና በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብ እና የማንገላታት ችግሮች እንደነበሩ ገልጸዋል።
በምርጫው እለት የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ መንግስት እና የጸጥታ አካላት ስራቸውን በአግባቡ መስራታቸውንም ነው የቁሳቁስ እጥረትና የመራጮች ብዛት በድምጽ አሰጣጡና በቆጠራው ሂደት ላይ ጫናን ፈጥሯል ያሉት ኦባሳንጆ የተናገሩት።
የሲቪክ ማህበረሰብ አካላት በምርጫው የሚያደርጉትን ተሳትፎ መቀጠልና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ተቋማትን፣ በተለይም ለምርጫ ቢርድ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናከሮ እንዲቀጥልም ነው የጠየቁት፡፡
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ የሚያደርገው ሰብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡
የምርጫ ውጤቱ በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትእግስት ሊጠባበቁ ይገባልም ነው ኦባሳንጆ ያሉት።
ቡድኑ በ5 ክልሎች እና 2 ከተሞች ታዛቢ ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡
ድምጽ ሰጪዎች በምርጫው ደስተኛ መሆናቸውንና የፈለጉትን በነጻነት መምረጣታቸውን ነግረውኛል ያለም ሲሆን የመራጮቹ ትዕግስት አስገራሚ ነበርም ብሏል።
ምርጫውን በ4 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች በ190 የምርጫ ጣቢያዎች ተገኝቶ መታዘቡን የገለጸው የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫው የተረጋጋና ሰላማዊ ነው ማለቱ የሚታወስ ነው፡፡
ቡድኑ የትዝብቱን የተጠቃለለ ሪፖርት ከ2 ወራት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ በመግለጫው አስታውቋል፡፡ (አዲስ ሚዲያ ኔትወርክና አል-ዐይን)
Qomchei Ambaw says
You say:
“ቡድኑ በ5 ክልሎች እና 2 ከተሞች ታዛቢ ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡
. . . . .
ምርጫውን በ4 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች በ190 የምርጫ ጣቢያዎች ተገኝቶ መታዘቡን የገለጸው የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫው የተረጋጋና ሰላማዊ ነው ማለቱ የሚታወስ ነው”
So is 4 or 5 Kilils? And how about the election report from the groupf of the eu and 13 other countries? That is too uncomfortable? Or it doesn’t fit with your comical and biased reporting gigsaw?