• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት አስመረቀ

September 8, 2021 12:34 pm by Editor Leave a Comment

በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ስር የሚገኘው ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከሪፐብሊካን ጋርድ የተመለመሉ በቪአይፒ እና በቁልፍ መሰረተ ልማት ጥበቃ የሰለጠኑ መኮንኖችን አስመርቋል።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት ትልቅ ሃላፊነትና እምነት የተጣለባቸው ሲሆን፤ የሀገርን ብሔራዊ ደህንነት በማረጋገጥ ረገድም ከፍተኛ ሚና ሲያበረክቱ እንደነበር ገልጸዋል።

በተለይ ከሀገራዊ ለውጡ ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ፈተናዎችን በከፍተኛ ወኔና ትዕግስት በመፍታት ያበረከቱት አስተዋጽኦ አስቸጋሪ ጊዜዎችን ለማለፍ እንዳስቻለ ያስታወሱት አቶ ተመስገን፤ በቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃትና ጥብቅ በሆነ የስራ ዲሲፒሊኒ ለመወጣት የሚስችላቸውን ስልጠና ከዩኒቪርሲቲ ኮሌጁ መቅሰማቸውን አመልክተዋል።

አቶ ተመስገን የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸውን ስልጠና እንዲያገኙ ላስቻሉት ለዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ አካለት ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሪፐብሊካን ጋርድ ምክትል አዛዥ ብ/ጀነራል አብድሮ ከድር፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት በርካታ ሀገራዊ ግዳጆችን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል።

አሁንም አሸባሪው ህወሓት በተለያዩ አቅጣጫዎች የከፈተውን ጦርነት ለመመከት ከሌሎች ሃይሎች ጋር በመቀናጀት ከፍተኛ ጀብዱ እየፈጸሙ ነው ብለዋል።

“በብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የተሰጠው ስልጠና ሀገራችን ከእኛ የምትጠብቀውን ግዳጅ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም እገዛ ያደርጋል” ያሉት ብ/ጀነራል አብድሮ፤ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ አመራሮች ስልጠናው ከውጥኑ ጀምሮ እስከ ፍጻሜው የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ እገዛ በማድረጋቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ከልጠናውም የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ ለተሰጣቸው ስምሪት አጋዥ የሚሆን በጣም ጠቃሚ ግብዓት መገኘቱን መስክረዋል።

የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት ከተሰጣቸው ሀገራዊ ተልዕኮ አንጻር ውጤታማ ስምሪት እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው ስልጠና እንደተሰጣቸው አመልክተዋል።

የቪአይፒ እና የቁልፍ መሰረተ ልማት ጥበቃ የዘመናችን የብሔራዊ ደህንነት ስምሪት ወሳኝ አካል ናቸው ያሉት የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ በዚህ ረገድ አቅማቸውንና ክህሎታቸውን የሚያሳድግ የንድፈሀሳብና የተግባር ስልጠና መውሰዳቸውን አመልክተዋል።

የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2013 በጀት ዓመት ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ጀማሪ ኦፊሰሮች ከሰጠው ተከታታይ ስልጠና በተጨማሪ፤ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ፣ ለገቢዎችና ጉምሩክ፣ ለክልሎች እንዲሁም ለተለያዩ ተቋማት ባለሙያዎችና አመራሮች በመረጃ፣ በደህንነትና በተያያዥ መስኮች በርካታ ስልጠናዎች ስጥቷል።

በቀጣይም ለአካባቢው እና ለጎረቤት ሀገራት አቻ የመረጃና ደህንነት ተቋማት በመረጃና ደህንነት ዘርፎች የተለያዩ ስልጠናዎችን ለመስጠት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ስምምነት መፈፀሙን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያደረሰው መረጃ ያመለክታል። (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule