• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት አስመረቀ

September 8, 2021 12:34 pm by Editor Leave a Comment

በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ስር የሚገኘው ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከሪፐብሊካን ጋርድ የተመለመሉ በቪአይፒ እና በቁልፍ መሰረተ ልማት ጥበቃ የሰለጠኑ መኮንኖችን አስመርቋል።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት ትልቅ ሃላፊነትና እምነት የተጣለባቸው ሲሆን፤ የሀገርን ብሔራዊ ደህንነት በማረጋገጥ ረገድም ከፍተኛ ሚና ሲያበረክቱ እንደነበር ገልጸዋል።

በተለይ ከሀገራዊ ለውጡ ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ፈተናዎችን በከፍተኛ ወኔና ትዕግስት በመፍታት ያበረከቱት አስተዋጽኦ አስቸጋሪ ጊዜዎችን ለማለፍ እንዳስቻለ ያስታወሱት አቶ ተመስገን፤ በቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃትና ጥብቅ በሆነ የስራ ዲሲፒሊኒ ለመወጣት የሚስችላቸውን ስልጠና ከዩኒቪርሲቲ ኮሌጁ መቅሰማቸውን አመልክተዋል።

አቶ ተመስገን የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸውን ስልጠና እንዲያገኙ ላስቻሉት ለዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ አካለት ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሪፐብሊካን ጋርድ ምክትል አዛዥ ብ/ጀነራል አብድሮ ከድር፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት በርካታ ሀገራዊ ግዳጆችን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል።

አሁንም አሸባሪው ህወሓት በተለያዩ አቅጣጫዎች የከፈተውን ጦርነት ለመመከት ከሌሎች ሃይሎች ጋር በመቀናጀት ከፍተኛ ጀብዱ እየፈጸሙ ነው ብለዋል።

“በብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የተሰጠው ስልጠና ሀገራችን ከእኛ የምትጠብቀውን ግዳጅ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም እገዛ ያደርጋል” ያሉት ብ/ጀነራል አብድሮ፤ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ አመራሮች ስልጠናው ከውጥኑ ጀምሮ እስከ ፍጻሜው የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ እገዛ በማድረጋቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ከልጠናውም የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ ለተሰጣቸው ስምሪት አጋዥ የሚሆን በጣም ጠቃሚ ግብዓት መገኘቱን መስክረዋል።

የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላት ከተሰጣቸው ሀገራዊ ተልዕኮ አንጻር ውጤታማ ስምሪት እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው ስልጠና እንደተሰጣቸው አመልክተዋል።

የቪአይፒ እና የቁልፍ መሰረተ ልማት ጥበቃ የዘመናችን የብሔራዊ ደህንነት ስምሪት ወሳኝ አካል ናቸው ያሉት የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት፤ የሪፐብሊካን ጋርድ አባላቱ በዚህ ረገድ አቅማቸውንና ክህሎታቸውን የሚያሳድግ የንድፈሀሳብና የተግባር ስልጠና መውሰዳቸውን አመልክተዋል።

የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2013 በጀት ዓመት ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ጀማሪ ኦፊሰሮች ከሰጠው ተከታታይ ስልጠና በተጨማሪ፤ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ፣ ለገቢዎችና ጉምሩክ፣ ለክልሎች እንዲሁም ለተለያዩ ተቋማት ባለሙያዎችና አመራሮች በመረጃ፣ በደህንነትና በተያያዥ መስኮች በርካታ ስልጠናዎች ስጥቷል።

በቀጣይም ለአካባቢው እና ለጎረቤት ሀገራት አቻ የመረጃና ደህንነት ተቋማት በመረጃና ደህንነት ዘርፎች የተለያዩ ስልጠናዎችን ለመስጠት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ስምምነት መፈፀሙን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያደረሰው መረጃ ያመለክታል። (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule