• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ“አምላካችሁ ባሮች” የሆናችሁ “ሰላማዊ ሰልፈኞች” ቅድሚ የምትሰጡት ለማን ነው?

August 31, 2013 02:01 am by Editor 1 Comment

እርቅን፣ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን ለማውረድ የሃይማኖት አባቶችና ሽማግሌዎች ቁልፍ ሚና አላቸው። በር ዘግተው ይጸልያሉ። ያስታርቃሉ። ይገስጻሉ። ያስጠነቅቃሉ። እንዲህ አይነት ለሌሎች ብርሃን ለመሆን የሚቃጠሉ የሃይማኖት አባቶች ያሏቸው ምንኛ የታደሉ ናቸው?

በተቃራኒው የአምላክ ባሪያዎች፣ የየእምነታቸው ባሪያዎች፣ የምዕመናን መንፈስ መጋቢዎችና ጠባቂዎች፣ ወዘተ አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚወጡ በይፋ ተነገረን። “በተገንጣይ ነጻ አውጪ” ስም እየተጠራጠረና እየተጸየፈ አገራችንን ከሚመራ ከሃዲ ድርጅት ጎን ለመቆም የሃይማኖት መሪዎች መነሳታቸው ለፈረደባት ኢትዮጵያና ለህዝቧ ከዚህ በላይ ሃፍረት የለም!! ችግሩ በውስጥም በውጭም ያለውን ይመለከታል። ይህንን ስንል ምክንያታችንን ህዝብ ይረዳዋል ብለን እናምናለን።

በሰማያዊውም ሆነ በምድራዊው ዓለም “መተፋት” አለ። የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች ከዚህ አስደንጋጭ /ለሚደነግጡት ነው/ የፈጣሪ ቅጣት ይጠበቁ ዘንድ ምን ማድረግ እንደሚገባችሁ በወጉ ታውቁታላችሁና ዝርዝር ማብራሪያና ስብከት ውስጥ አንገባም። ተግባራችንም አይደለም። ግን ልብ ያለው ልብ ይበል! ለማለት እንወዳለን። ከመተፋትና ከመናቅ፣ ብሎም ተጠቅመው እንደሚጥሉት እቃ ከመጣል ይጠብቃችሁ!!

ሰሞኑን የሃይማኖት መሪዎችን ኢህአዴግ ሰብስቧቸው ድርጅታዊ ሥራ እንዴት መሥራት እንዳለባቸው ሲያሰለጥናቸው ነበር። በግልጽ ቋንቋ “ሃይማኖታዊ ካድሬነትን” ሲያስተምራቸው ሰንብቷል ማለት ነው፡፡ ስልጠናው “ጽንፈኝነትን ተቃወሙ” የሚል ነው። የተማሩትን በተግባር ለመፈጸምና ያላቸውን ልዩ ብቃት ለመገምገም እሁድ የሰርቶ ማሳያ ሰልፍ እንዲወጡ ተጠይቀዋል፡፡ በኢህአዴግ ቋንቋ ሰልፉ “ተሞክሮ ማስፋት፣ ማስፋፋት፣ ማስረጽ፣ ማሳለጥ … ” መሆኑ ነው።

ጽንፈኝነትን መቃወምም ሆነ በሃይማኖቶች መካከል ተቻችሎ ለመኖር በህብረት መነሳት ይሁን የሚባልለትና በመርህ ደረጃ ሊደገፍም የሚገባው ጉዳይ ነው። በየትኛውም ደረጃ፣ ማህበር፣ ተቋምና የሃይማኖት ቤቶች ውስጥ የሚጠነሰስን “ጽንፈኛነት” ባግባቡ መቃወም ሃጢያትም የለውም። ዓለም በሙሉ ባንድነት በሰላማዊ ሰልፍ ጽንፈኛነትን ማስወገድ ቢችልና ሰላም ለማውረድ ባንድነት ቢሰሩ ክፋት የለውም። ወደ ኢህአዴግ ሰራሹ የተቃውሞ ሰልፍ ስንመጣ ግን ለሁሉም ወገኖች ጥያቄም፣ ማሳሰቢያም፣ ፍርሃቻም አንዳለን ለመግለጽ እንወዳለን።

የሃይማኖት መሪዎች በሙሉ ኢህአዴግ ራሱ ለፈጠረው በሽታ “ክትባት አለኝና ኑ ልክተባችሁ” ከሚለው ድብቅ አስተሳሰቡ በተለየ እንዴት በነጻ አስተሳሰብ ላይ ይቆማሉ? ብለን ስንጠይቅ መልሳችን ” አይታስብም” የሚል ይሆናል። ምክንያቱን በውጪም በውስጥም ያሉ የሃይማኖት ተቋማት በሙሉ ነጻና “ፈሪሃ አምላክ” የነገሰባቸው እንዳልሆኑ እንረዳለንና!! ከዚያም በላይ የሁሉም ወገን ስጋት ይኸው የሃይማኖት መሪዎች መገሸብ ይመስለናል። ኢህአዴግም እንዳሻው የሚነዳቸው አፈጣጠራቸውንና ጽናታቸውን ስለሚገነዘብ ነው።

ሃይማኖቶች የሰላምና የፍቅር መስበኪያ ቦታዎች ናቸው ቢባልም አንዳንድ ሰዎች በጣም ሃይማኖታቸውን ከመውደዳቸው የተነሳ ዓለም በሙሉ የእነርሱ ሃይማኖት እንዲወድላቸው ከመፈለግ የተነሳ በፍቅር የጀመሩትን እምነት አክርረው የጥላቻ መነሃሪያ ያደርጉታል፡፡ ይህ ደግሞ በተለያዩ ሃይማኖቶች ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ሲንጸባረቅ የኖረ እውነታ ነው።

ሰሞኑን ኢህአዴግ የሰበሰባቸው የሃይማኖት ድርጅቶችም መስመር ሊወጣ የሚችለውን የአክራሪነት አቋም እንዲያወግዙ ነቅተዋል፤ ሠልጥነዋል፡፡ በጉባዔው ላይ ሼክ ከድር ሙሐመድ “ሃይማኖት ሰላም ነው። አገራችን ሰላም ትፈልጋለች፤ አገራችን ስትታመም መድኃኒቷ እኛ ነን” ብለዋል። ግሩም አባባል ነው።

አቡነ ማትያስ በበኩላቸውም “የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት የሚፈታተኑ የሁላችንም ተቃራኒ ናቸው፤ ይህንን የመቋቋም ኃላፊነትና ግዴታ አለብን፤ … የየእምነታችንን ተከታዮች የአገራችሁን ሰላም ጠብቁ ብለን መስበክ የምንችልበት ሰፊ መድረክ አለን” በማለት ሃሳባቸውን በመሰንዘር ሌሎቹም የሃይማኖት ተቋማት ምን ማድረግ እንዳለባቸው መክረዋል፡፡

ለሃይማኖት መሪዎቹ የምናስተላልፈው መልዕክት ቢኖር ይህንኑ ለአገር ተቆርቋሪነታችሁን እና ሰላም ወዳድነታችሁን “ያልተጠኑት ገጾች” ላይ አስፍሯቸው ነው፡፡ ላለፉት 22ዓመታት ሰላም ሲነፍግና ህዝብን ሲጨቁን፤ ዜጎችን በግፍ እስርቤት ሲከትና በቃላት ሊነገር በማይቻል ሁኔታ ሲያሰቃይ፤ ሲገድል፣ በጅምላ ሲጨፈጭፍ፣ ከመኖሪ ቦታ ሲያፈናቅል፣ ዜጎቹን ለአረብ አገር ለግርድና ሲሸጥና ሲያሻሽጥ፣ ህጻናትን (ወንድ ህጻናትን ጨምሮ) ለወሲብ ንግድ ሲሸቅጥ፤ የአገር ድንግል መሬትን የተፈጥሮ ደን እየጨፈጨፈ በሳንቲም ሲሸጥ፣ የመናገር፣ የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ … መብትን ሲነፍግ፣ የመናገርና ሃሳብ የመስጠት መብታችን ይከበር ያሉትን ሁሉ እንደ ወራሪ ኃይል ደረትና ግምባራቸውን በጥይት ሲበሳ፣ የኢትዮጵያ እናቶችን ለዘመናት ሲያስለቅስ፣ … የኖረውን ኢህአዴግን በነካ እጃችሁ “ተው ተመከር፤ ይብቃህ፤ እረፍ!” ስትሉና ስትገዝቱት ባለመሰማታችሁ ምመናን አዝነውባኋል። አሁንም ግን ጊዜ አለና በነካ እጃችሁ ኢህአዴግንም አስጠንቅቁ፣ አውግዙ።

የሃይማኖት አክራሪነትንና ጽንፈኝነትን ብቻ ሳይሆን በነጻ አውጪ ስም የመንግሥት ሥልጣን ይዞ አገርን ላለፉት 22ዓመታት ሲያሸብር የኖረውን አክራሪውና ጽንፈኛውን ህወሃትን ራሱን “እስካሁን የረገጥከው ሰብዓዊ መብት ይበቃሃል” በማለት ሃይማኖታዊ ድርሻችሁን ተወጡ፡፡ የሰላም አስጠባቂ፣ የፍትህና የሰብዓዊ መብት አስከባሪ ካድሬ ሁኑ፡፡ በምድር ላለው ኑሮና ተድላ ሳይሆን ለመጪው ዓለም አማኞች እንዲያስቡ የምትሰብኩትን እስቲ ለአንድ ጊዜ ራሳችሁ ኑሩበትና ይህንን የሕዝብ እሮሮ በማሳወቅ ከዚህ ምድር አስተሳሰብ የላቃችሁ መሆናችሁን አሳዩ፡፡ መስዋዕትነት የሚያስከፍል ከሆነም ምዕመኖቻችሁን እንዳስተማራችሁት እናንተም ለተግባራዊነቱ በዝግጅት ቁሙ!

እሁድ በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የአክራሪነትና ጽንፈኝነትን ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣንም አብራችሁ ተቃወሙ፤ ይህን የማይገኝ ዕድል ተጠቀሙና ድምጻቸው የታፈነውን ዜጎች ድምጽ አሰሙ፡፡

የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ መግለጫ በእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡ አክራሪዎችንና ጽንፈኞችን “እረፉ” በማለት ያውግዛቸው ብሎ እንዳወጀው ሁሉ፣ በዚያውም ህወሃትንና ኢህአዴግን እንዲሁም ተላላኪዎቻቸውንና ጉዳይ አስፈጻሚ አሽከሮቻቸውን “የእስካሁኑ ይበቃችኋል፤ እረፉ፤ በነጻ አውጪ ስም አገርና ወገን ላይ የምታደርሱትን ግፍ አቁሙ” በሏቸው። እስኪ የሃይማኖት አባትነት ወግ አሳዩን!! እስኪ በታሪክ የሚዘከር ተግባር ፈጽሙ። ከኮሚኒስቶች ጉያና ትዕዛዝ ውጡና በምትሰብኩት አምላክ ፊት ስትቆሙ የማታፍሩ ሁኑ። የ”አምላካችሁ ባሮች” ቅድሚያ ለማን እንደምትሰጡ እወቁ። በሰማያዊውም ሆነ በምድራዊው ዓለም በቁም “መተፋትም” አለና!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. anoole wako says

    August 31, 2013 04:34 am at 4:34 am

    egzer ala eyalu yemesabekun sawoch egzern yemayfaru kahona bergetem egzeru yelam ??

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule