• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል

June 12, 2022 05:40 pm by Editor Leave a Comment

የወሎ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተርና የስነ ጽሁፍና ፎክሎር መምህሩ ብርሃኑ አሰፋ (ዶ/ር) ሀገራችን ኢትዮጵያ ረዥም ዘመናትን ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ የመጡ በየአከባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው ባህላዊ የግጭት አፈታትና የእርቅ ተቋማት አሏት ብለዋል።

ለአብነት በወሎ አከባቢ ያሉትን ብናነሳ በራያና አከባቢው ዘወልድ፣ በተሁለደሬና አከባቢው አበጋር፣ በምዕራብ ወሎ አማሬና በሀብሩ አከባቢ ሸህ ለጋን መጥቀስ ይቻላል ያሉት መምህሩ በየአከባቢው ያሉት የግጭት አፈታቶቹ እንደየአከባቢው ባህል፣ ልማድ፣ እምነት እና የአኗኗር ኹኔታ መጠሪያቸውና የአከዋወን ኹኔታቸው ቢለያይም ግጭትን የመፍታትና እርቅን የማውረድ እሳቤያቸው ተመሳሳይ ነው ብለዋል።

እነዚህ የግጭት መፍቻ ተቋማት በማኅበረሰቡ እምነትና ስነ ልቦና ላይ የተመሰረቱና አስታራቂዎቹም በማኅበረሰቡ ከፍተኛ ግምትና ተቀባይነት የተሰጣቸው በመኾናቸው ውጤታማነታቸውና የእርቁ ዘላቂነት ተመራጭ ያደርጋቸዋልም ብለዋል።

መምህሩ ሀገራችን በየወቅቱ እያጋጠሟት ላሉ የግጭት ችግሮች እነዚህን ባህላዊ የግጭት አፈታት መንገዶችን በመጠቀም ዘላቂ መፍትሄን ማምጣት ይቻላል ብለዋል።

ብሄራዊ የምክክርና የእርቅ መድረኩም እነዚህን ታላላቅ የግጭት መፍቻ ተቋማትን የሚመሩ አስታራቂ ሽማግሌዎችን በማካተት ቢካሄድ የሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል።

በተለይም ወጣቱ በምዕራባውያን በእቅድ የተመራ የባህል ወረራ ተወስዶ እነዚህን ባህላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች በተገቢው ስለማያውቃቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ባህሎቹን በማጥናትና በማስተዋወቅ ሚዲያዎችም በተገቢው ለሕዝቡ በማስገንዘብ ባህሎቻችንን ትውልዱ እንዲያውቃቸውና ዘመኑን በዋጀ መልኩ እንዲገለገልባቸው ሊሰሩ ይገባል፤ መንግስትም ለእነዚህ ተቋማት ተገቢውን እውቅና ሊሰጥ ይገባል ብለዋል ዶ/ር ብርሃኑ አሰፋ። (አሚኮ)

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule