• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል

June 12, 2022 05:40 pm by Editor Leave a Comment

የወሎ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተርና የስነ ጽሁፍና ፎክሎር መምህሩ ብርሃኑ አሰፋ (ዶ/ር) ሀገራችን ኢትዮጵያ ረዥም ዘመናትን ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ የመጡ በየአከባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው ባህላዊ የግጭት አፈታትና የእርቅ ተቋማት አሏት ብለዋል።

ለአብነት በወሎ አከባቢ ያሉትን ብናነሳ በራያና አከባቢው ዘወልድ፣ በተሁለደሬና አከባቢው አበጋር፣ በምዕራብ ወሎ አማሬና በሀብሩ አከባቢ ሸህ ለጋን መጥቀስ ይቻላል ያሉት መምህሩ በየአከባቢው ያሉት የግጭት አፈታቶቹ እንደየአከባቢው ባህል፣ ልማድ፣ እምነት እና የአኗኗር ኹኔታ መጠሪያቸውና የአከዋወን ኹኔታቸው ቢለያይም ግጭትን የመፍታትና እርቅን የማውረድ እሳቤያቸው ተመሳሳይ ነው ብለዋል።

እነዚህ የግጭት መፍቻ ተቋማት በማኅበረሰቡ እምነትና ስነ ልቦና ላይ የተመሰረቱና አስታራቂዎቹም በማኅበረሰቡ ከፍተኛ ግምትና ተቀባይነት የተሰጣቸው በመኾናቸው ውጤታማነታቸውና የእርቁ ዘላቂነት ተመራጭ ያደርጋቸዋልም ብለዋል።

መምህሩ ሀገራችን በየወቅቱ እያጋጠሟት ላሉ የግጭት ችግሮች እነዚህን ባህላዊ የግጭት አፈታት መንገዶችን በመጠቀም ዘላቂ መፍትሄን ማምጣት ይቻላል ብለዋል።

ብሄራዊ የምክክርና የእርቅ መድረኩም እነዚህን ታላላቅ የግጭት መፍቻ ተቋማትን የሚመሩ አስታራቂ ሽማግሌዎችን በማካተት ቢካሄድ የሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል።

በተለይም ወጣቱ በምዕራባውያን በእቅድ የተመራ የባህል ወረራ ተወስዶ እነዚህን ባህላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች በተገቢው ስለማያውቃቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ባህሎቹን በማጥናትና በማስተዋወቅ ሚዲያዎችም በተገቢው ለሕዝቡ በማስገንዘብ ባህሎቻችንን ትውልዱ እንዲያውቃቸውና ዘመኑን በዋጀ መልኩ እንዲገለገልባቸው ሊሰሩ ይገባል፤ መንግስትም ለእነዚህ ተቋማት ተገቢውን እውቅና ሊሰጥ ይገባል ብለዋል ዶ/ር ብርሃኑ አሰፋ። (አሚኮ)

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule