• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ ዝሆኖችም “ተሸብረዋል”

March 20, 2015 11:19 pm by Editor 1 Comment

ኢህአዴግ በሥልጣን በቆየባቸው 25 ያህል ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ከሚገኙ መቶ ዝሆኖች ውስጥ ከዘጠና በላይ የሚሆኑት ሞተዋል፣ ወደ ጎረቤት አገር ተሰድደዋል፣ የደረሱበት አይታወቅም፣ . . . ሲሉ የዓለም የመገናኛ ብዙሃን ዛሬ (አርብ) ዘግበዋል፡፡

የዝሆኖችን ግድያ ለማስቆም በሚል የብአዴኑ ደመቀ መኮንን ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ስድስት ቶን የሚመዝን ጌጣጌጥ እንዲቃጠል እሣቱን በለኮሱበት ጊዜ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየበት 25 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ዝሆኖች ቁጥር ከ90በመቶ በላይ ለምን ሊቀንስ እንደቻለ የተናገሩት ነገር የለም፡፡

ኢህአዴግ ከቻይና ጋር ከተፋቀረበት ጊዜ ጀምሮ የዝሆን ቀንድ ንግድ እየተጧጧፈ እንደሄደ የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በዚህም “ጮማ” ንግድ ውስጥ ቢጂንግን፣ ሲንጋፖርን፣ ታይላንድን፣ … መመላለሻቸው ያደረጉ ቱባ ባለሥልጣናትና ደላሎቻቸው ይጠረጠራሉ፡፡ የቡድሃ ሃይማኖት እጅግ በተስፋፋባቸው በሩቅ ምስራቅ አገራት የዝሆን ጥርስ እጅግ ተፈላጊ ሲሆን ዋንኞቹ አስተላላፊዎች ደግሞ የዘመኑ የቻይና ቱጃሮች ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ  የዝሆን ጥርስ ለሩዝ መብያ ስንጥር (chopsticks)፣ ለተለያዩ ዓይነት ጌጣጌጥ፣ ለቤት ውስጥ ዕቃ፣ ወዘተ ተፈላጊነት አለው፡፡

ivory 2ቻይና በዝሆን ጥርስ ገቢ ንግድ ላይ የአንድ ዓመት ማዕቀብ ጥያለው ብትልም በአፍሪካ ያሰማራቻቸው ባለሃብቶቿ ከየአገሩ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን ንግዱን እንደተቆጣጠሩት የእንስሳት መብት ተከራካሪዎች ይናገራሉ፤ ወደ አፍሪካ በሚያስገቡት ኮንቴይነር የአፍሪካን ሃብት ጭነው እንደሚልኩ በስፋት የሚነገር ነው፡፡ ይህም የቻይና አካሄድ በዚሁ ከቀጠለ በአፍሪካ የዝሆን ዝርያ የማይኖርበት ደረጃ ላይ እንደሚደርስ ይገመታል፡፡

በአንዳንድ ኤክስፐርቶች ግምት ሁኔታው ካልተሻሻለ እኤአ በ2025 አፍሪካ ዝሆን አልባ ትሆናለች ይላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ደግሞ መሻሻል ካልተደረገበት የኢትዮጵያ ዝሆኖች እስከዚያ ስለ መዝለቃቸው ግምት መስጠት አይቻልም፡፡ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየባቸው 25ዓመታት ውስጥ 90በመቶው ዝሆኖች ካለቁ የቀሩት 10 በመቶው አሉ የተባለው “ምርጫው” እስኪያልፍ ነው በማለት አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡ (የመግቢያው ፎቶ AFP: Zacharias Abubeker)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    March 21, 2015 07:16 pm at 7:16 pm

    >> በቀድሞ ግዜ ሻእቢያ ህወአት ኦነግና ኦብነግ አሸባሪዎች በነበሩ ግዜ ዙሪያውን ጦርነት ሲከፍቱ የኬንያ፣ የሱዳን፣ ዩጋንዳና ታንዛኒያ አሳዳሪዎች የጦር መሳሪያ ለአሸባሪዎቻችን እየረዱ በኢሊኮብተር ድምፅ የዱር አራዊቶቻችንን እያስበረገጉና አቀጣጫ እያስቀየሩ ዛሬ በቱሪስት መስዕብነታቸው የሚታወቁት የዛሬው ልማታዊ መንግስት የድሮ የጥፋት ቡድን ሙሉ በሙሉ ተሳታፊነት የተመሳጠሩበት የሀገር ሀብት ብዝበዛ ነበር ። ዛሬም በኮንቴነር ክብሪት ያመጡልሃል ጭረህ እናዳታቃጥለው ጥሬ ሀብትህን በኮንቴነር ያሸሻሉ አሁንም ቻይና ኑሪ!!አንደኛ ቻይና፣ ሁለተኛ ቻይና ሶስተኛ ቻይና ያለው ተጠቅላይ ሚ/ር ማን ነበር?
    *** የብአዴኑ ደመቀ መኮንን ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ስድስት ቶን(፮ቶን) የሚመዝን ጌጣጌጥ እንዲቃጠል እሣቱን በለኮሱበት ጊዜ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየበት 25 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ዝሆኖች ቁጥር ከ90በመቶ በላይ ለምን ሊቀንስ እንደቻለ የተናገሩት ነገር የለም፡፡… “ዝሆኖችም ተወይኖባቸዋል”!!…
    ” ግን ደመቀና ዝሆኖች ሲሞቱ የት ነበሩ? ሕዝብና የዝሆን ቀንድ ለማቃጠል ብቅ ማለታቸው በም/ጠ/ሚ ማዕረግ የእሳት አደጋ አቃጣይ ባለሙሉ ባለሥልጣን መሆናቸው ነው?ይህን ወደ ገንዘብ ለውጦ ለድሃ ማብላት ቀሪውን መከላከል ነው ጥሩ ወይንስ በሙቀት ላይ ሙቀት መፍጠር ወሬ!?
    ** በእርግጥ ቻይና ለአንድ ኣመት ብቻ የዝሆን ጥርስ ንግድ ገቢ ላይ ማዕቀብ በመጣሏ ማስቀመጫ ስለሌለ ከሚባነን ሕዝብ እያየ ጨዋነታችንን እናሳይ ተብሎ ይሆን!? እነንህ ሰዎች ገድለው ቀብረው ፈርሸው ማስተዛዘን የተካኑ አደሉምን!? መራጭ ይወድቃል ከምራጭ አሉ…ወይ የምርጫ ዋዜማ ጨዋ መምሰል!ሠላም ለሁሉም በቸር ይግጠመን>>>>>>

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule