• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ ዝሆኖችም “ተሸብረዋል”

March 20, 2015 11:19 pm by Editor 1 Comment

ኢህአዴግ በሥልጣን በቆየባቸው 25 ያህል ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ከሚገኙ መቶ ዝሆኖች ውስጥ ከዘጠና በላይ የሚሆኑት ሞተዋል፣ ወደ ጎረቤት አገር ተሰድደዋል፣ የደረሱበት አይታወቅም፣ . . . ሲሉ የዓለም የመገናኛ ብዙሃን ዛሬ (አርብ) ዘግበዋል፡፡

የዝሆኖችን ግድያ ለማስቆም በሚል የብአዴኑ ደመቀ መኮንን ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ስድስት ቶን የሚመዝን ጌጣጌጥ እንዲቃጠል እሣቱን በለኮሱበት ጊዜ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየበት 25 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ዝሆኖች ቁጥር ከ90በመቶ በላይ ለምን ሊቀንስ እንደቻለ የተናገሩት ነገር የለም፡፡

ኢህአዴግ ከቻይና ጋር ከተፋቀረበት ጊዜ ጀምሮ የዝሆን ቀንድ ንግድ እየተጧጧፈ እንደሄደ የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በዚህም “ጮማ” ንግድ ውስጥ ቢጂንግን፣ ሲንጋፖርን፣ ታይላንድን፣ … መመላለሻቸው ያደረጉ ቱባ ባለሥልጣናትና ደላሎቻቸው ይጠረጠራሉ፡፡ የቡድሃ ሃይማኖት እጅግ በተስፋፋባቸው በሩቅ ምስራቅ አገራት የዝሆን ጥርስ እጅግ ተፈላጊ ሲሆን ዋንኞቹ አስተላላፊዎች ደግሞ የዘመኑ የቻይና ቱጃሮች ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ  የዝሆን ጥርስ ለሩዝ መብያ ስንጥር (chopsticks)፣ ለተለያዩ ዓይነት ጌጣጌጥ፣ ለቤት ውስጥ ዕቃ፣ ወዘተ ተፈላጊነት አለው፡፡

ivory 2ቻይና በዝሆን ጥርስ ገቢ ንግድ ላይ የአንድ ዓመት ማዕቀብ ጥያለው ብትልም በአፍሪካ ያሰማራቻቸው ባለሃብቶቿ ከየአገሩ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን ንግዱን እንደተቆጣጠሩት የእንስሳት መብት ተከራካሪዎች ይናገራሉ፤ ወደ አፍሪካ በሚያስገቡት ኮንቴይነር የአፍሪካን ሃብት ጭነው እንደሚልኩ በስፋት የሚነገር ነው፡፡ ይህም የቻይና አካሄድ በዚሁ ከቀጠለ በአፍሪካ የዝሆን ዝርያ የማይኖርበት ደረጃ ላይ እንደሚደርስ ይገመታል፡፡

በአንዳንድ ኤክስፐርቶች ግምት ሁኔታው ካልተሻሻለ እኤአ በ2025 አፍሪካ ዝሆን አልባ ትሆናለች ይላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ደግሞ መሻሻል ካልተደረገበት የኢትዮጵያ ዝሆኖች እስከዚያ ስለ መዝለቃቸው ግምት መስጠት አይቻልም፡፡ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየባቸው 25ዓመታት ውስጥ 90በመቶው ዝሆኖች ካለቁ የቀሩት 10 በመቶው አሉ የተባለው “ምርጫው” እስኪያልፍ ነው በማለት አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡ (የመግቢያው ፎቶ AFP: Zacharias Abubeker)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    March 21, 2015 07:16 pm at 7:16 pm

    >> በቀድሞ ግዜ ሻእቢያ ህወአት ኦነግና ኦብነግ አሸባሪዎች በነበሩ ግዜ ዙሪያውን ጦርነት ሲከፍቱ የኬንያ፣ የሱዳን፣ ዩጋንዳና ታንዛኒያ አሳዳሪዎች የጦር መሳሪያ ለአሸባሪዎቻችን እየረዱ በኢሊኮብተር ድምፅ የዱር አራዊቶቻችንን እያስበረገጉና አቀጣጫ እያስቀየሩ ዛሬ በቱሪስት መስዕብነታቸው የሚታወቁት የዛሬው ልማታዊ መንግስት የድሮ የጥፋት ቡድን ሙሉ በሙሉ ተሳታፊነት የተመሳጠሩበት የሀገር ሀብት ብዝበዛ ነበር ። ዛሬም በኮንቴነር ክብሪት ያመጡልሃል ጭረህ እናዳታቃጥለው ጥሬ ሀብትህን በኮንቴነር ያሸሻሉ አሁንም ቻይና ኑሪ!!አንደኛ ቻይና፣ ሁለተኛ ቻይና ሶስተኛ ቻይና ያለው ተጠቅላይ ሚ/ር ማን ነበር?
    *** የብአዴኑ ደመቀ መኮንን ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ስድስት ቶን(፮ቶን) የሚመዝን ጌጣጌጥ እንዲቃጠል እሣቱን በለኮሱበት ጊዜ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየበት 25 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ዝሆኖች ቁጥር ከ90በመቶ በላይ ለምን ሊቀንስ እንደቻለ የተናገሩት ነገር የለም፡፡… “ዝሆኖችም ተወይኖባቸዋል”!!…
    ” ግን ደመቀና ዝሆኖች ሲሞቱ የት ነበሩ? ሕዝብና የዝሆን ቀንድ ለማቃጠል ብቅ ማለታቸው በም/ጠ/ሚ ማዕረግ የእሳት አደጋ አቃጣይ ባለሙሉ ባለሥልጣን መሆናቸው ነው?ይህን ወደ ገንዘብ ለውጦ ለድሃ ማብላት ቀሪውን መከላከል ነው ጥሩ ወይንስ በሙቀት ላይ ሙቀት መፍጠር ወሬ!?
    ** በእርግጥ ቻይና ለአንድ ኣመት ብቻ የዝሆን ጥርስ ንግድ ገቢ ላይ ማዕቀብ በመጣሏ ማስቀመጫ ስለሌለ ከሚባነን ሕዝብ እያየ ጨዋነታችንን እናሳይ ተብሎ ይሆን!? እነንህ ሰዎች ገድለው ቀብረው ፈርሸው ማስተዛዘን የተካኑ አደሉምን!? መራጭ ይወድቃል ከምራጭ አሉ…ወይ የምርጫ ዋዜማ ጨዋ መምሰል!ሠላም ለሁሉም በቸር ይግጠመን>>>>>>

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule