• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሄዶ ኢትዬጵያ (hej då Ethiopia)”

April 29, 2016 03:10 pm by Editor 1 Comment

በቅርቡ በዚህ በምኖርበት አገር አንድ የልደት በአል ላይ ተጠርሼ ሄጄ ነበር፡፡ በዚሁ ዝግጅት ላይ ከዝህ በፊት በአካል አግኝቼው የማላውቀው የዚሁ አካባቢ ከበርቴ ጋር ስጨዋወት ነበር፡፡ በተለይ ከአመታት በፊት በኢትዬጵያ ታስርው ስለነበሩት የስዊድን ጋዜጠኞች ልቤ እስኪጠፋ ጠየቀኝ፡፡ እኔም የምችለውን ያህል ለመመለስ ሞከርኩ፡፡  ስንሰነባብት ያለኝ ነገር ግን ሰሞኑን በኢትዬጵያ ዙሪያ የሚሰማኝን ውጥንቅጥ ስሜት ቅልብጭ አድርጎ ገለጠልኝ። ምን አለኝ መሰላችሁ… “ሄዶ ኢትዬጵያ”። አለፍ ብሎም ስሜን በወጉ መጥራት እንደከበደው ነገረኝ። በዚህ በስዊድን አፍ “ሄዶ (hej då)” ማለት ቻው ወይንም ደህና ሁን/ሁኚ እንደማለት ነው። ከዚሁ ቤት እየወጣሁ ቃሉን በውስጤ ደጋገምኩት… ሄዶ ኢትዬጵያ … ቻው ኢትዬጵያ … በተመስጦ አሰብኩት። አዎ ልክ ነው። አሁን ሰለ ሃገሬ የሚሰማኝ ስሜት ይሄ ነው። ቻው ኢትዬጵያዬ የሚል አይነት ስሜት። ለማስረዳት ልሞክር።

ሰሞኑን በጋምቤላ ወገኖቼ ላይ የተከሰተው አሰቃቂ ክስተት ለእኔ ከመቼውም ጊዜ በላይ የገለጠልኝ ሁለት ቁም ነገሮች አሉ።

አንድ።

እኛ ኢትዬጵያውያን መከላኪያ ሰራዊት ሳይሆን ማፈሪያ ሰራዊት ነው ያለን። በእጅጉ የሚያሳፍር እና የሚያሸማቅቅ። የማንኛውም አገር መከላኪያ ሰራዊት ተቀዳሚ ተግባሩ እንዲሁም የሰራዊቱ መኖር ዋንኛ ምክንያት የአገሩን ሉአላዊነት ማስከበር መሆኑ ግልብ ነው። ከዚህም በላይ አንድን አገር እንደ አገር (solid state) ከሚያስቆጥሩ ቁልፍ እና ወሳኝ ነገሮች አንዱ ሉአላዊነት እንደሆነ ነው የሚገባኝ። ወደ እኛው ጉድ ስንመጣ ግን  ማፈሪያው ሰራዊታችን ተግባሩ እና አላማው ለየቅል ነው። እስከአሁን እንዳየነው ማፈሪያው ሰራዊታችን ለሰላማዊ ተቃውሞ የሚወጡ ኢትዬጵያውያን፣ ህጻናት እና እናቶች ሳይቀር መግደል ተቀዳሚ ተግባሩ ከሆነ ቆየት ብሎአል። በሙስና እስከ አፍንጫቸው ከተጨማለቁ የመንግስት ተቐሞች አንዱ መከላኪያ ነው። ለእኔ ይኼ ማፈሪያ የሆነ ሰራዊት ንጹሀን ኢትዬጵያውያንን መግደል እና የአገሪቱን ሀብት መዝረፍ የእለት ከእለት ተግባሩ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ።

እሺ ሌብነቱስ ይሁን። ከከርስ ባለፈ ማሰብ በማይችሉ የግለሰቦች ስብስብ ከተሞላ መስሪያ ቤት የሚጠበቅ ነው። (በነገራችን ላይ ስለ መከላከያ ሌብነት በማስረጃ ማሳየት እችላለሁ። በግሌም ያየሁት ስለሆነ)። ንጹሀን ኢትዬጵያውያንን በተደጋጋሚ መግደሉ ለአገር ሳይሆን የሕወሀት አሽከር መሆኑን መግለጫ ነው ብለን እንውሰደው። ነገር ግን የታጠቀ የውጭ ሐይል (ያውም ከደቡብ ሱዳን) ስንት እና ስንት ኪሎ ሜትር የኢትዬጵያን ዳር ድንበር በመድፈር ሰሞኑን የሰማነወን አሰቃቂ ጭፍጨፋ በኢትዬጵያውያን ላይ መድረሱ እኛ ኢትዬጵያውያን መከላከያ ሰራዊት እንደሌለን አስረግጦ የሚያሳይ ይመስለኛል። በዚህ መልኩ የኢትዬጵያ ሉአላዊነት መደፈሩ የሚያመላክተው የኢትዬጵያን መለዮ የለበሰው እና የኢትዬጵያን የጦር መሳሪያ የታጠቀው የግለሰቦች ስብስብ (ወታደር ለማለት ስለከበደኝ ነው) መከላከያ ሳይሆን በእርግጥም ማፈሪያ ነው! ይኼን አገራዊ ውርደት ተሸክመን ሌላ አገር ሄዶ ሰላም ማስከበር፤ በእሳት እየተቃጠሉ እሳት የመሞቅ ያህል ቂላቅልነት ነው። ድንቄም አሉ!

ሁለት።

እኛ ኢትዬጵያውያን መንግስት ሳይሆን ማፍያ ነው አገራችንን የሚመራት። ለይስሙላ የሚታይ የመንግስት መዋቅር ቢኖርም፣ ፓርላማውን ጨምሮ። አገሪቱን በትከክክል የሚመራው እና የሚያስተዳድረው የግለሰቦች ስብስብ ነው። ስሙ ሕወሀት ሲሆን ተግባሩ ደግሞ የማፊያ ነው። ይኸ የይስሙላ የመንግስት መዋቅር ከስም ውጪ ሌላ እርባና የለውም። በውስጡ የተሰገሰጉት ግለሰቦች ባዶ ቀፎ ናቸው። (በዚሁ በጎልጉል ጋዜጣ ላይ ከጥቂት ጊዜ በፊት “ቀፎ አይሁኑ” በሚል ሃሳቤን ለማካፈል ሞክሬአለሁ)  ። ይኸ መዋቅር የሕወሀት ፈረስ ማለት ነው። ለዚህም ይመስለኛል ” አባ ዱላ የመለስ ጥሩ ፈረስ” እየተባለ የሚቀለደው … የሚቀለደው ልበል፤ ወይስ የሚታማው፤ ወይስ የሚታወቀው እንዲያውም እንደሚታወቀው ብንለው ይቻላል። ግልጽ ስለሆነ። የበፊት ነገስቶቻችን ከፈረሶቻቸው ስም በፊት “አባ” የሚለውን ተቀጽላ በማስታወስ። ለነገሩ ፈረስ እኮ ጥሩ እንሰሳ ነው። ታዛዥ እንሰሳ። ስለ ፈረስ ካነሳሁ አይቅር … አንድ ነገር ልበል።(የፈለገ ቢሆን አንድ ኢትዬጵያዊ ያልተማረ ፈረስ እንግሊዘኛ ሊናገር አይችልም! ግብጽ ድረስ ዲፕሎማት አድርጋችሁ ብትልኩትም። በዚህ በቅንፍ ውስጥ ያለው ለሚገባው ይገባዋል።) ወደ ጉዳዬ ልመለስ። ይኸ ራሱን ሕወሀት እያለ የሚጠራው የማፊያ ቡድን በዚህ ከላይ በጠቀስኩት ፈረስ ላይ ተቆናጦ ይኸው ለ ሃያ አምስት አመታት እየጋለበን ይገኛል። እንግዲህ ማፊያው እንደማፊያ እየዘረፈ፤ እየዋሸ እና እየገደለ እዚህ ላይ ደርሰናል። ቅጥፈቱ ከመቅረናቱ የተነሳ የሚታየው ረሃብ እና የኢትዬጵያውያን ሰቆቃ በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ መርገም ነው።

ላጠቃለው፤ ስጀምር በመግቢያ ላይ ቻው ኢትዬጵያ በሚለው እደምታዬ ነበር።  አዎ የታለች ያአቺ የምናውቅት አገር? ሉአላዊ ኢትዬጵያ ወዴት ነው ያለችው አሁን?  ለመጀመሪያ ጊዜ የጥቁር ሕዝብ ድል አድራጊነት ለአለም ያሳየች ኢትዬጵያ የት ናት አሁን? ከነጻነት ተምሳሌትነት ተንደርድረን ወርደን ይኼው ዛሬ ኢትዬጵያውያን በበርሃ እየታረዱ ነው፤ በአደባባይ በተሰደዱበት በእሳት እየተቃጠሉ ነው፤ በርሃብ እየታረዙ ነው፤ በሜዲትራኒያን ባህር እየተዋጡ ነው፤ ጭራሽ ብለን ብለን ኢትዬጵያ ውስጥ ተጠልለው በሚገኙ የሌላ አገር ስደተኞች፤ ኢትዬጵያውያን እንደሚታደነ የዱር እንሰሳ በየጫካው ለመግለጽ በሚያስቸግር መልኩ እየተገደሉ ነው። ታዲያ እንዲያው ድፍረት አይሁንብኝና ጥያቄ ልጠይቅ። ሁሉንም ኢትዬጵያዊ። እንደዚህ ናት እንዴ የእኛ ኢትዬጵያ? እንዴት ነው ነገሩ? ወዴት እየሄድን ነው? እንጃ?! እኔ ግን አንድ ነገር በእርግጠኝነት ልንገራችሁ። ይኸን ማፊያ መንግስት እና ማፈሪያ መከላከያ ሠራዊት ቆመን የምናይ ከሆነ፤ እውነት እውነት ኢትዬጵያን ቻው እያልናት ነው። ማፍያስ ያው ማፍያ ነው፤ ቀፎም ያው ቀፎ ነው፤ ፈረስም ያው ፈረስ ነው። እኛ ግን ምን ሆነን ነው ቆመን የምናየው?

በዚህ አጋጣአሚ በጋምቤላ ለሚገኙ እናቶቼ፤ አባቶቼ፤ እህት እና ወንድሞቼ ፈጣሪ ጽናቱን እና ብርታቱን ይስጣችሁ።

ፈጣሪ አገራችንን ይባርክ።

ወንድምአገኝ እጅጉ
ከስቶኮልም፥ ስዊድን


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ተስፋዬ አበራ says

    May 14, 2016 07:03 pm at 7:03 pm

    ወንድሜ ወንድም አገኝ የፃፍከውን አስተያየት አንብቤዋለሁ ሀሳብህን ሙሉ በሙሉ የምጋራው ሲሆን ” ኢትዬፕያን ቻው እያልናት ነው” የሚለውን ቃል ግን አልወደድኩትም ከእኛ ይልቅ እነዚህን ጉዶች ከሀገራችን እንዴት እንደምናስወግድና እነርሱኑ በሰሩት ግፍ እና ሀጥያት ለፍርድ አቁመን ቅጣታቸውን ሲጨርሱ እነርሱንም ሆነ ስርአቱን በተግባር ቻው ቻው ማለት የለብኝ ይመስለኛል።
    ታዲያ በወሬ ሳይሆን በተግባር ሁላችንም በምንችለው መንገድ መንቀሳቀስ ይጠበቅብናል ሰዎቹ በህዝባችን እና ሀገራችን ላይ እየተፀዳዱብን ይገኛሉ ንቀውናል አዋርደውናል ጭራሽ የጋራ ሀብታችንን እየዘረፉ በውጭ ሀገራት ባንኮች ውስጥ ገንዘብ እንደሚያስቀምጡ ይታወቃል ስለሆነም ለተግባራዊ ትግል እንነሳ !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule