• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በፖለቲካ ፓርቲና አክቲቪስት ጫጫታ የሠራዊቱ ተልዕኮው አይደናቀፍም፤ እርምጃ እንወስዳለን–ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ

September 25, 2020 01:27 am by Editor 1 Comment

ሕገ-መንግሥቱን በጣሰ መልኩ በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን ሲሉ በኢፌዴሪ መከላከያ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹምና የኦፕሬሽናል ጉዳዮች ኃላፊ ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ። 

የኢትዮጵያ የብር ኖት መቀየርን ተከትሎ ሠራዊቱ በህገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። 

ከዚህ ቀደም አገልግሎት ላይ ሲውል የነበረው የአብዮታዊ ሠራዊት መገንቢያ ሰነድ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ እንዳላደረገው ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታውሰዋል። 

ስለሆነም በአገራዊ ሪፎርሙ አዲስ የሠራዊት መገንቢያ ሰነድ አገልግሎት ላይ መዋሉን ጠቁመው÷ አሁን ላይ ሰራዊቱ ያለ ምንም ፖለቲካ ወገንተኝነት ህዝብንና ሀገርን ህልውና እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። 

በመሆኑም ሠራዊቱ “የማንም ፖለቲካ ፓርቲ መጠቀሚያ አይደለም፣ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲና አክቲቪስት ጫጫታ ከተልዕኮው አይደናቀፍም ሲሉም ነው የተናገሩት። 

ሠራዊቱ ጠንካራ ውስጣዊ አደረጃጀት እንዳለው የጠቆሙት ጄኔራሉ ከዚህ አንጻር ፖለቲከኞች በየትኛውም የፖለቲካ ቅስቀሳቸው ላይ የመከላከያ ሠራዊቱን የሚመለከት አጀንዳ ማራመድ የለባቸውም ብለዋል። 

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተራዘመው አገራዊ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት ህገ-መንግስቱን የተከተለ መሆኑንም ጀኔራል ብርሃኑ አብራርተዋል። 

በህገ መንግስቱ መሰረት ሥልጣን የሚያዘው በምርጫ ብቻ እንጂ ‘ሽግግርና ባለአደራ’ በሚል ትርምስ አይደለም ሲሉም ነው የተናገሩት። 

ከዚህ አንጻር ከመስከረም 30 በኋላ መንግሥት የለምና እንደፈለኩ እሆናለው የሚል አካሄድ ህገ-ወጥ መሆኑን ገልጸዋል። 

ህገ-መንግሥቱን በጣሰ መልኩ ‘በሃይል ፍላጎቴን’ አሳካለሁ በሚል የትኛውም አካል ላይ ሠራዊቱ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድም ገልጸዋል። 

ጀኔራል ብርሃኑ አክለውም የኢትዮጵያ የብር ኖት መቀየርን ተከትሎ ሠራዊቱ በህገ-ወጥ ገንዘቦች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጠንካራ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። 

ነገር ግን ሠራዊቱ ህገ-ወጥ በሚል ሰበብ ገንዘብ እየነጠቀ እንዲወስድ ፈቃድ ተሰጥቶታል በሚል የሃሰት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙ አካላት እንዳሉም ነው የገለጹት። 

ሠራዊቱ ከተገነባበት እሴት ይህን እንዲያደርግ ፈጽሞ አይፈቅድለትም ብለዋል።

በህገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋዋር የተያዘ ገንዘብ በአንድ ቋት ተሰብስቦ የጸጥታ መዋቅሩን ለማጠናከር እንደሚውል በማብራራት። 

ሆነ ብለው በተደራጀ መልኩ የሀገር ኩራት የሆነውን የመከላከያ ሠራዊት ስም ጥላሸት የሚቀቡ አካላት እንዳሉም ተናግረዋል። 

ከዚህ ቀደም ከውስጥ ምንጭ አገኘነው በሚል ሰበብ የመከላከያ ሠራዊት ስም የሚያጠፉ ጽሁፎችን ያሳተሙ ግለሰቦች መኖራቸውን ለአብነት አንስተዋል። 

ድርጊቱ ከባድ ወንጀል ቢሆንም በትዕግስት መታለፉን ጠቅሰው፤ ከዚህ በኋላ በመሰል ተግባር የሚሳተፉ ማናቸውንም አይነት ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቀቀዋል። 

ሠራዊቱ በአሁን ወቅት ማናቸውንም አይነት ተልዕኮዎችን በብቃት ማከናወን በሚያስችል ሙሉ ቀመና ላይ መሆኑንም ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ብርሃኑ ጁላ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Comments

  1. make mitku says

    October 8, 2020 09:59 am at 9:59 am

    really yours documents

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule