• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በፖለቲካ ፓርቲና አክቲቪስት ጫጫታ የሠራዊቱ ተልዕኮው አይደናቀፍም፤ እርምጃ እንወስዳለን–ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ

September 25, 2020 01:27 am by Editor 1 Comment

ሕገ-መንግሥቱን በጣሰ መልኩ በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን ሲሉ በኢፌዴሪ መከላከያ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹምና የኦፕሬሽናል ጉዳዮች ኃላፊ ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ። 

የኢትዮጵያ የብር ኖት መቀየርን ተከትሎ ሠራዊቱ በህገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። 

ከዚህ ቀደም አገልግሎት ላይ ሲውል የነበረው የአብዮታዊ ሠራዊት መገንቢያ ሰነድ ሠራዊቱን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ እንዳላደረገው ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታውሰዋል። 

ስለሆነም በአገራዊ ሪፎርሙ አዲስ የሠራዊት መገንቢያ ሰነድ አገልግሎት ላይ መዋሉን ጠቁመው÷ አሁን ላይ ሰራዊቱ ያለ ምንም ፖለቲካ ወገንተኝነት ህዝብንና ሀገርን ህልውና እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። 

በመሆኑም ሠራዊቱ “የማንም ፖለቲካ ፓርቲ መጠቀሚያ አይደለም፣ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲና አክቲቪስት ጫጫታ ከተልዕኮው አይደናቀፍም ሲሉም ነው የተናገሩት። 

ሠራዊቱ ጠንካራ ውስጣዊ አደረጃጀት እንዳለው የጠቆሙት ጄኔራሉ ከዚህ አንጻር ፖለቲከኞች በየትኛውም የፖለቲካ ቅስቀሳቸው ላይ የመከላከያ ሠራዊቱን የሚመለከት አጀንዳ ማራመድ የለባቸውም ብለዋል። 

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተራዘመው አገራዊ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት ህገ-መንግስቱን የተከተለ መሆኑንም ጀኔራል ብርሃኑ አብራርተዋል። 

በህገ መንግስቱ መሰረት ሥልጣን የሚያዘው በምርጫ ብቻ እንጂ ‘ሽግግርና ባለአደራ’ በሚል ትርምስ አይደለም ሲሉም ነው የተናገሩት። 

ከዚህ አንጻር ከመስከረም 30 በኋላ መንግሥት የለምና እንደፈለኩ እሆናለው የሚል አካሄድ ህገ-ወጥ መሆኑን ገልጸዋል። 

ህገ-መንግሥቱን በጣሰ መልኩ ‘በሃይል ፍላጎቴን’ አሳካለሁ በሚል የትኛውም አካል ላይ ሠራዊቱ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድም ገልጸዋል። 

ጀኔራል ብርሃኑ አክለውም የኢትዮጵያ የብር ኖት መቀየርን ተከትሎ ሠራዊቱ በህገ-ወጥ ገንዘቦች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጠንካራ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። 

ነገር ግን ሠራዊቱ ህገ-ወጥ በሚል ሰበብ ገንዘብ እየነጠቀ እንዲወስድ ፈቃድ ተሰጥቶታል በሚል የሃሰት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙ አካላት እንዳሉም ነው የገለጹት። 

ሠራዊቱ ከተገነባበት እሴት ይህን እንዲያደርግ ፈጽሞ አይፈቅድለትም ብለዋል።

በህገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋዋር የተያዘ ገንዘብ በአንድ ቋት ተሰብስቦ የጸጥታ መዋቅሩን ለማጠናከር እንደሚውል በማብራራት። 

ሆነ ብለው በተደራጀ መልኩ የሀገር ኩራት የሆነውን የመከላከያ ሠራዊት ስም ጥላሸት የሚቀቡ አካላት እንዳሉም ተናግረዋል። 

ከዚህ ቀደም ከውስጥ ምንጭ አገኘነው በሚል ሰበብ የመከላከያ ሠራዊት ስም የሚያጠፉ ጽሁፎችን ያሳተሙ ግለሰቦች መኖራቸውን ለአብነት አንስተዋል። 

ድርጊቱ ከባድ ወንጀል ቢሆንም በትዕግስት መታለፉን ጠቅሰው፤ ከዚህ በኋላ በመሰል ተግባር የሚሳተፉ ማናቸውንም አይነት ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቀቀዋል። 

ሠራዊቱ በአሁን ወቅት ማናቸውንም አይነት ተልዕኮዎችን በብቃት ማከናወን በሚያስችል ሙሉ ቀመና ላይ መሆኑንም ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ብርሃኑ ጁላ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column

Reader Interactions

Comments

  1. make mitku says

    October 8, 2020 09:59 am at 9:59 am

    really yours documents

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule