• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ለባስልጣናት ለሚታዘዝ ፍ/ቤት (ቃላችንን) አንሰጥም” እነ በቀለ ገርባ

August 11, 2016 06:03 pm by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ፈደራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር አባላት አቶ ጉርሜሳ አያኖ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ አዲሱ ቡላላ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 ተከሳሾች ዛሬ ልደታ ምድብ ፍርድ ቤት ቀርበው የሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ከዚህ የሚከተለው ነው።

ጉርሜሳ አያኖ፤ “ክሱ ግልፅ አልሆነልኝም እኔ ፖለቲከኛ ስሆን የመድረክ ፓርቲ-አባል ነኝ፡፡ የእኛ ፓርቲ ህገመንግስቱን ተከትሎ የተቋቋመ ህጋዊ ፓርቲ ነው፡፡ የተከሰስኩት ግን የኦነግ አባል ነህ በሚል ነው፣ እኔ እስከማውቀው አንድ ሰው የሁለት ድርጅት አባል መሆን አይችልም፡፡ ይሄ ክስ መንግስት መሬቴን አሳልፌ አልሰጥም ያለዉን የኦሮሞን ህዝብ በጅምላ አሸባሪ ብሎ እየከሰሰ ነዉ ያለው ስለዚህ ቃሌን ለዚህ ፍ/ቤት አልሰጥም፡፡”

ደጀኔ ጣፋ፤ “የኢትዮጵያ ፍ/ቤት በግልፅ ህገመንግስቱን እያፈረሰ ያለ ተቋም ስለሆነ ለዚህ ፍ/ቤት ቃሌን አልሰጥም፣ ከአሁን ወዲህም ወደዚህ ፍ/ቤት መምጣት አልፈልግም፣ ውሳኔውም ግልጽ ስለሆነ ባለሁበት ሆኜ ይድረሰኝ! የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እኛ ላይ የተፈጸመውን በደል እንዲያውቅልን እፈልጋለሁ፡፡”

አዲሱ ቡላላ፤ “የደረሰኝ ክስ የሚመስል ድርሰት ግራ አጋብቶኛል፡፡ እኔ የመድረክ ፓርቲ እንጂ የኦነግ አባል አይደለሁም፣ ለህዝቤ ብዬ ባደረግኩት ነገር በሙሉ ደስተኛ ነኝ፣ በአዲሱ ስም የተመሰረተው ክስ በኦሮሞ ላይ የተመሰረተ ክስ መሆኑን ሁሉም ሰው እንዲያውቅልኝ እፈልጋለሁ፤ እኔ ለዚህ ፍትህ አልባ ፍ/ቤት ቃሌን መስጠት አልፈልግም ተመካክራችሁ ውሳኔውን ባለሁበት አድርሱኝ!”

በቀለ ገርባ፤ “ባለፈዉ ቀጠሮ የክስ መቃወሚያችን ላይ ወንጀሉ ተፈጸመ የተባለው ኦሮሚያ ክልል ሆኖ ሳለ ለምን በፌዴራል መንግስት እንዳኛለን?! በክልላችን በቋንቋችን እንዳኝ ብለን አቤቱታ አቅርበን ነበር ቢሆንም የሰማን የለም፡፡ እኛን ግን ገብቶናል ለምን ክሳችን በፌዴራል እንዲታይ እንደተደረገ፣ ፍ/ቤቱ በተጻፈለት መሰረት ሊፈርድብን ነዉ፡፡ ይህ ፍ/ቤት ታዞ እንደሚሰራ ከዚህ በፊት ስምንት አመት ያለጥፋቴ ተፈርዶብኝ እኔ በራሴ ህይወት ችግሩ ደርሶብኝ አይቻለሁ ስለዚህ ለዚህ ፍ/ቤት ቃሌን አልሰጥም፡፡”

በዓለምአቀፍ ደረጃ በአሸባሪነት በሚታወቀው ህወሃት፣ “አሸባሪ” ተብለው በግፍ የተከሰሱት እነ በቀለ ገርባ በዚህ መልኩ ተቃውሟቸውን ቢገልጹም ፍርድ ቤቱ ግን ክደው እንደተከራከሩ መዝግቧል።

(ዜናውን ያጠናከርነው ከቪኦኤ ዘገባና #oromoprotest ነው)


ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule