• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አብዲ ኢሌ ባስቸኳይ ተነስቶ ለፍርድ ካልቀረበ በዓለምአቀፍ ደረጃ ተጠያቂ መሆኑ አይቀርም

August 6, 2018 02:24 am by Editor 2 Comments

በበርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂ የሆነው የህወሓት ሹመኛው የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አብዲ ኢሌ የጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር በቁጥጥር ሥር አውሎት ለፍርድ ካላቀረበው በዓለምአቀፍ ፍርድ ቤት ሊጠየቅ እንደሚችል ጎልጉል ጥቆማ ደርሶታል።

ሰሞኑን ከህወሓት ጀነራሎች የተሰጠውን የሥራ ተግባር ሲወጣ የነበረው አብዲ ከሥልጣኑ የሚለቅበትና እጁን የሚሰጥበት ቀን ዛሬ ሰኞ እንደሚሆን አንዳንድ የሶማሊ አክቲቪስቶችና የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች ሲገልጹ ቆይተዋል። በርካታዎች ጤንነቱን የሚጠራጠሩትና ከዕውቀት የጸዳው አብዲ በምክትል ጠ/ሚ/ር ደመቀ መኮንን ለተመራው ቡድን ሥልጣኑን እንደሚለቅ ቃል ገብቷል የሚለው በስፋት እየተወራ ነው። ሆኖም አረፋፍዶ ይህንኑ ሊቀለብስና በፈለገው አቅጣጫ ሊሄድ ይችላል የሚለውም ከውሳኔው ጋር አብሮ ከግምት ውስጥ የገባ ነው።

የአብዲ ኢሌይ መጨረሻ ሲጀምር በሚል ርዕስ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ሒውማን ራይትስ ዎች “We are Like the Dead’: Torture and other Human Rights Abuses in Jail Ogaden, Somali Regional State, Ethiopia” በሚል ርዕስ ያወጣውን የ88 ገጽ ዘገባ በመንተራስ በዘገበበት ወቅት የሚከተለውን ማለቱ ይታወሳል።

“ይህ የግፍ ቁልል የተከማቸበት ዘገባ፤ በኦጋዴን እስር ቤት ግፍና ስቅየት በመፈጸምና በማስፈጸም ተዋናኝ የሆኑትን የፌዴራሉ መንግሥት የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አብዲ ኢሌንና ሌሎች ከፍተኛ የሶማሊ ክልል ባለሥልጣናትን ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ የሚያደርግ ነው”።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር በአብዲ ኢሌ ላይ ፈጣን እርምጃ እንዲወስድ የግፉ ገፈት ቀማሾችና የሶማሊ ክልል ወገኖች እየወተወቱ ነው። ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉ ጎልጉል ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ደግሞ አብዲ ኢሌ በአገር ውስጥ ለፍርድ ቢቀርብ የተሻለ ይሆናል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች የዐቢይ አስተዳደር ቸልተኝነት ካሳየ ወይም የፖለቲካ አካሄዱን መስመር ለማስያዝ በሚል በሌላ አቅጣጫ ከሄደ አብዲ ኢሌ በውጭ አገር ለፍርድ እንዲቀርብ ዓለምአቀፍ የእስር ማዘዣ ሊወጣበት ይችል ይሆናል። ይህንንም ለመተግበር የቆረጡ ወገኖች እንዳሉ መረጃው ያመለክታል። የዛሬው ውሎና ውሳኔ ወደ ዓለምአቀፉ መድረክ የመሄድ ወይም አለመሄድ ሁኔታን ይወስነዋል ተብሏል።

ይህንን ዘገባ እያዘጋጀን ባለበት ወቅት ጅጅጋ ውስጥ አብዲ ኢሌን ከሥልጣኑ ለማውረድ ስብሰባ መጀመሩንና አብዲ ሲወርድ በቦታው ይተካል ተብሎ የታሰበው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ሚ/ር አህመድ ሺዴ በስብሰባው ላይ የሚገኝ መሆኑ በተለያዩ የማኅበራዊ ገጾች ላይ እየተዘገበ ይገኛል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abdi illey, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Amanuel ze Ambo says

    August 6, 2018 05:40 pm at 5:40 pm

    ሴረኛዋ እና በየበታችነት ስሜት የምትሰቃየው ለታላቋ ሀገር ኢትዮጵያ በማይመጥን ስብዕና የተከሰተችውና መቼም መች መጥበብ እንጂ መስፋትን፣ መበጥበጥ እንጂ መርጋትን ፣ሁከት እንጂ ሰላምን፣ ጠባብ አዕምሮዋ የማይቀበልላት ሁከተኛዋንና አናሳዋን ቡድን ህወሀትን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ አርቀን ካልቀበርናት ውላ ባደረች ቁጥር በምትሰራቸው የክፋት እና የተንኮል ስራዋ መብሰክሰኩ ብቻ አላዋጣም ።

    ይህች የጥፋት መልዕክተኛ እና ባንዳ ቡድን እርሷም እንደ አብዲ ኤሊ ያሉ ወፍራም ገለባዎችን በባንዳነት ቀጥራ ሀገር ለማመስና እንዲህ ልቡ እንዳበጠ ጥጋበኛ ጎረምሳ ለያዥ ለገራዥ ማስቸገሯ ተገቢ እና ተመጣጣኝ ቅጣትን ባለማግኘቷ የዜጎችን ታጋሽነት እና ሆደ ሰፊነት ከፍርሃት በመቁጠሯ ነው ። ስለዚህ ይህቺን ለአዛይ እንኳ የምታስቸግር ሙልጭልጭ ሞላጫ የጥፋት ቡድን ላትድን እና ላትለወጥ ማስታመሙ በሽታዋን ወደጤነኛው ከማስተላለፍ ውጭ አንዳችም ፋይዳ የሌለው በመሆኑ” ወያኔን ካዳነ ይልቅ የገደላት ጸደቀ” በሚል ዘመቻ የማያዳግም ርምጃ ወስዶ ሀገርን እና ሕዝባ ከዚህች ቆሻሻ ማጽዳት ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆን አለበት ።

    ባንዳዋ ቡድን መገንጠልን እንደ አይጥ መሞከሪያ ያደረገችው አብዲ ኤሊ በልኳ የተሰራ ከመሆኑ ጋር መጪውን እንዳያስብ ስብ የዘጋው ጠባብ አእምሮው ማስተዋልን ተነስቷል ፤ ዳሩ ከህወሃት ውሎ ጤነኛ ቢሆን እና የነገን ቢያስብ ነበር እጃችንን በበአፋችንአስጭኖ የሚያስገርመን!!
    ከማህጸኗ የተቀፈቀፉ (የተፈለፈሉ) አንዳንዶች ደግሞ ሊያዝጉን እና ሊያዘናጉን መሻታቸውም ይገርማል፤ ይህች የባንዳ ስብስብ ራሷ ለራሷ በሰየመችው ወያኔ በሚል ስሟ ስንጠራት እንዲህ አትበሏት ወያኔ የሚለው ስም ትግራዋይን ሁሉ ይጠቀልላልና ይሉናል ፣ ክፉ ግብሯን ገልጠን ህወሃት እንዲህ አደረገች ስንል ህወሃት ስትሉ ለውጥ ፈላጊውንም አብራችሁ እየጨፈለቃችሁ ነው እና አጥፊዋን ቡድን ህወሀት ብላችሁ አትጥሩ ይሉናል፤ ስለዚህ በእነርሱ ስሌት ይህችን ውሉደ እፉኝት ቡድን ደባዋን እና ጥፋቷን እያየን እርሷም ማጥፋቷን እያወቅን በስሟ ጠርተን እንዳናወግዛት እንዳንፋረዳትም በገደምዳሜ ጥብቅና ይቆሙላታል ።

    በእነርሱ ስሌት ይህችን ቡድን ማን ብለን እንጥራት ይሆን? ኦነግ? ግንቦት ሰባት? ምክንያቱም ከዚህ በፊት ርኩሰቷን በሙሉ በነዚህ ድርጅቶች ስም ስትሰራ ኖራለች የሚታለሉላትንም ስታታልልበት ኖራለች እንግዲህ ግላግልቶቿ እርሷ ባጠፋች ሌላው ላይ አላክኩልን ከማለት ውጭ ይሄ ሃሳባቸው በምን ይተረጎማል? እውነት እንነጋገር ከተባለ ከእባቧ እንቁላል (ከህወሀት) የርግብ እንቁላል አይጠበቅም፤ የምናየውም ይኼንኑ ነው ። ተለያይተናል ህወሃት ጸረሰላም ናት የበሰበሰች የገማች ናት እያሉ የተለዩዋት ሁሉ በቀብሯ ዋዜማ እየተጠራሩ ሊታደጓት ሲታትሩ እያየን ከዚህች እባብ እንቁላል እንዴት ርግብ እንጠብቅ???
    “”” ቢሆንም ከነፈሩት ከነኚህ መሃል ኢትዮጵያዊነትን ያልካዱ እንደነ ገ/መድህን አርዓያ እና አስገደ ገ/ሥላሴ ዓይነት እድለኞችን እንደ ብርቅ እናያለን ፤ “””

    የሆነው ሆኖ ሕወሃት መቀመቅ መውረዷ አይቀሬ ነው ይህን እርሷም በደምብ ታውቀዋለች መፈራገጧም ከመላላጥ ውጭ ምንም እንደማይፈይድላት በደምብ ታውቃለች ግብዝ ግን ስለሆነች የጀግና ሞት መሞት ያምራታል ህወሃት አህያም ናትና እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ዓይነት ብሂል አላት ፤ ህወሃት እድሜ ዘመኗን ጀግና መሆን ሳትችል እንደበረገገች እና እንደሰጋች ስለኖረች በፈሪ በትሯ ብዙዎችን አቁስላለች ገዳድላለች ፍርሃቷ ጥግ ስለሌለውም ያጠቃኛል ብላ ያሰበችው ሰው በሕዝብ መካከል ቢታይ ሕዝቡን በጅምላ ጨርሳ የምትፈልገውን ሰው አስከሬን ከፈጀቻቸው ሰዎች መሀል የምትፈልግ ጉደኛ እና ቦቅባቃ ቡድን ናት እንዲህ የኖረችው ይህች አናሳ ቡድን ሞቷን የጀግና ሞት ለማስመሰል ትደክማለች እንጂ የሞቷ ዋዜማ ላይ መሆኗን እንኳን እኛ እርሷም በደምብ ታውቀዋለች ።

    ጭቁኑ የትግራይ ህዝብ ለሃጥአኑ እና ለቀን ጅቦቹ በመጣው መቅሰፍት እንዳይጎዳ በተደጋጋሚ ተመክሯል ተዘክሯል ግን የሰማ አይመስልም ይህ በመሆኑ ዓለም በስስት የሚመለከተውን እና ከጎንህ ነን እያለ የሚያበረታውን የህዝብ ልጅ ዶር አብይን ለማስገደል የሄደበት መንገድ ቢከሽፍበትም ለጊዜውም ቢሆን መቀሌ ላይ መሽጎ ከህግ ዓይን ለመሰወር የሚያደርገው መፍጨርጨር የት እንደሚያደርሰው ጊዜ ያሳየናል፤ ይኸው አናሳው እና ፈሪው የጥፋት ቡድን መቀሌ ላይ መሽጎ ጅጅጋን በውክልና እየበጠበጠም ይገኛል አዎን ለጊዜው የፈሪ በትሩን መዝዞ ዜጎችን በጠራራ ፀሐይ ገድላል ቤተክርስቲያን አቃጥሏል አገልጋይ ካህናቶቿን ገድሏል በዚህም ፈሪው ቡድን በመግደሉ መሸነፉን በሚገባ እያረጋገጠልን ነው ። ያልገባው ግን ላፈሰሰው ደም ሁሉ በእጥፍ እደሚከፍል አለመረዳቱ ነው ።

    በመሆኑም ነገር ሲድን እና ሲሞት ያለውን ሁኔታ በውል ላልተረዳ ደናቁርት ስብስብ አናሳ ቡድን የእጁን መክፈል ተገቢ እና ብቸኛም አማራጭ ነው ፤ ከዚህ በኋላ ይህን አናሳ ቡድን ለማዳን የሚታትር እርሱ የህዝብ ጠላት እንጂ ወዳጅ ሊሆን አይችልም ሰፊ እድሉን ያልተጠቀመና የበሰበሰ ቅርፊቱን መሸለት ካልፈለገ እና መቼም መች ጥፋት እንጂ ልማት የማይገኝበትን ይህን የጥፋት ቡድን ማስታመም በታላቋ ሀገር ላይ በማላገጥ ቡድኑም መምሰል እና ማከል ነው ፤ በመሆኑም ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆኖ አጥፊውን ለማጥፋት ሁሉም ይነሳ!!!

    አሳድደህ በለው ያንን አመጸኛ ተገንጣይ ወንበዴ
    መድረሻ አሳጣው ግረፈው አሳድደህ አስኪደው በዳዴ
    ማረኝ አይለምደኝም በቃኝ ብሎ ካላመነ እንዳትለቀው
    ያንተን ማንነት ይረዳ እስኪገባው ልክህን ይወቀው
    ሲል ጥላሁን ገሰሰ እንዳዜመ ያንኑ ማድረግ ተገቢ ነው!

    ዋዜማ ላይ ያለው ድል ዕለቱን ናፍቋልና ያን ለማየት ሁሉም ይበርታ ሞት ለጠባቦች ድል ለኢትዮጵያውያን!!

    Reply
  2. Lusif says

    August 8, 2018 05:05 am at 5:05 am

    What is power? What is being powerful? What is being powerless? Lately we do not see those powerful guys on TV windows. That is powerlessness to me and wished to know what they are feeling. Power made them blind and feel and act they way they did. When in power, they may not know what they felt and did. Do they feel their irresponsible deeds when they are powerless now? If they do they are learning and regranting and deserve forgiveness. If they do not, the Ethiopian people need to say enough is enough.
    I do believe in love and forgiveness. Those obviously committed crime, but were set free through love and forgiveness, should genuinely demonstrate that they deserve, by showing at least refrain
    From other evil deeds.
    I do not by that those criminals retreated and barracked in a certain corner. To me it is like both, depriving them opportunity to regret and give them freedom to do their dirty works. That tells me that love and forgiveness do not work with those individuals. Justice is the only solution, the only solution to make them regret and ask for forgiveness.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule