• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይህ ረሃብ “ፖለቲካዊ ችጋር” ነው!!

August 19, 2015 09:05 am by Editor Leave a Comment

ህወሃት ለአገራችን የቀመመው የበቀልና የተላላኪነት ፖለቲካ ገና ጦሱ አልጀመረም። ግን ሊመጣ ግድ ነው። በንጉሡ ወቅት ተርበናል። በደርግ ጊዜ ተርበናል። ኢህአዴግ ከመጣ ጀምሮ የታዩት ርሃቦች ግን ለየት ያሉ ናቸው። ስለዚህ ርሃቡም ሆነ ችጋሩ ፖለቲካዊ ነው ቢባል ያስማማል። ኢሣ የግጦሽ ሳር ሲያጣ ወደ ጎረቤቶቹ ያመራ ነበር። አፋር ተመሳሳይ ችግር ሲገጥመው ከብቶቹን እየነዳ ችግርን አሳልፎ ይመለስ ነበር። መጠነኛ አለመስማማት /በግጦሽ መሬት/ ከመፈጠሩ ውጪ “እገሌ ነህ” በሚል ጎጥ ለይቶ ሲጋደል አልተሰማም።

ዛሬ ህወሃት ሌሎችን እንደራሱ ለማሳነስና ለመበጣጠስ ሲል በዘርና በጎሳ መባላትን በአዋጅ ደንግጎ፣ በህግ አጽድቆ፣ ባገር ሚዲያ ጥላቻን እየሰበከ ተፋቅረው የኖሩትን አባልቷቸዋል። እያባላም ነው። ብዙ ሳይቆይ ራሱንም ጨምሮ የሚበላውን እሳት በየቀኑ እያጋመውም ይገኛል። እናም ሰሞኑን አደባባይ የወጣው ርሃብ ሰለባ ከሆኑት መካከል “እንደቀድሞ ከብት እየነዱ ምግብ ፍለጋ መጓዝ ስለማይቻል፣ ወገኖቻችን ውሃ እያሉ አለቁ። ተደብቆ እንጂ ብዙ ህዝብ አልቋል” ሲሉ ነግረውናል። ይህ ፖለቲካው ያመጣው ጣጣ ኩራት ለሚሆንላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፣ ገንቡ፣ ዝረፉ፣ ልጆቻቸሁን በዶላር አስተምሩ፣ አፈናቅሉ፣ የድሃውን መሬት በሽርክና ቸብችቡ፣ ራሳችሁም ኢንቬስተር ሆናችሁ አልሙ፣ ተንበሻበሹ፣ ስከሩ፣ ዘሙቱ፣ በራባቸው ላይ አስመልሱባቸው፣ … እነ ሬድዋንን ጨምሮ።

የመለስ ሙት መሃላ

“የሚሰሩ እጆች እያሉን፣ የሚያስቡ አእምሮዎች እያሉን፣ ይህን ወጣት ኃይል ይዘን ስንዴ መለመን እናቆማለን” በማለት ድርሰት ሲደርሱልን፣ ሲተርኩልን የነበሩት አቶ መለስ “የልማት አርበኞችን” ይዘው ገጠር ገቡ። የልማት ጀግኖች ከተማ ለቀው ገጠር ከተሙ። ዕድሜ “ለኤክስቴንሽን” አገሪቱና ገበሬው ምርት ማስቀመጫ ቦታ አጡ። በአገሪቱ ታሪክ እህል ወደ ውጪ መላክ ተጀመረ በማለት ደጋግመው ሰብከውን ነበር። መለስ “ገበሬውንና አርብቶ አደሩን ማእከል አድርገን ተነስተናል። ይህ አስተሳሰብ የሚቀየረው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ብቻ ነው” እያሉ ሲምሉ ነበር። ነገር ግን ሲማልበት የነበረ ህዝብ መሬቱን ተቀማ። በሳንቲም ለሌባ “ባለሃብቶች” ተቸበቸበ። የህዋሃት ሰዎች በልማት ስም ተቀራመቱት። የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ መረጃ አብይ ዋቢ ነው። እዩት!! በቀን ሶስቴ መብላት ቀርቶ አንዴውም እርም ሆነ። ነፍስ ይማር?!

የፖለቲካ ድርቅ – ፈጀን – ገና ይፈጀናል!

ሰዎች በዘራቸው ተለየተው ከሚኖሩበት ተፈናቅለዋል። እየተፈናቀሉ ነው። በሁሉም ክልሎችና ጎረቤት አገራት “ተከብረው” የሚኖሩት ህወሃት “ምርጥ” የሚላቸው ዜጎቹ ብቻ ናቸው። ይህንኑ ሃቅ የህወሃት አመራሮች በይፋ የሚናገሩት እንጂ እኛ የፈጠርነው አይደለም። መፈናቀል ለችጋር ይዳርጋል፤ የፖለቲካ ድርቅ ነው። ሰለባዎቹ ፍቺው ስለሚገባቸው ይብቃ!!

ለም መሬት በቅንጣቢ ሳንቲም እየቸበቸቡ ደሃውን ማፈናቀል ሌላው የፖለቲካ ቸነፈር ነው። ለአራት ዓመት ህጻን “ከክልላችን ውጣ” ብሎ ደብዳቤ መስጠት የከፋ የፖለቲካ ጠኔ ነው። “ባሪያ፣ አገልጋይ፣ አሽቃባጭ፣ ሎሌ … ካልሆንክ ሥራ አታገኝም” ብሎ ማለት ጠባሳው የማያሽር የፖለቲካ ችጋር ነው።

ለምን ተነፈሳችሁ በሚል ወኅኒ ተጥለው የሚሰቃዩ ወገኖች ጉዳይ ጊዜ መልስ የሚሰጠው የፖለቲካ ሽባነት ነው። ይህም ትልቅ ችጋር ነው። ሴት እህቶቻችን በዘራቸው ተመርጠው እንዲመክኑ ማድረግ ይቅርታ ለማድረግ የሚቸግር የፖለቲካው ተስቦ ውጤት ነው። እንዲህ ያለው የነጠፈ ኅሊና የሚነዳው ፖለቲካ ከችጋር በምን ይለያል?

ከድሃው ጉሮሮ በመንጠቅ በተዘረፈ ሃብት ድንጋይ መቆለል፣ ቪላ ማስገንባት፣ ዘመናዊ ተሽከርካሪ መዘወር፣ ጠግቦ ድሆችን መርገጥ … የፖለቲካው በሽታ ከመሆን ምን ያግደዋል? ከወገን ይልቅ ባእድ የሚያስቀድም የአገር ገዢ የፖለቲካ ችጋር ያጠናገረው እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? እነዚህ ኅሊናቸው የሞተባቸውና ቂም ቀብትቶ የያዛቸው ክፍሎች የሚያሽካኩበት ህዝብ የፖለቲካው ችጋር አልመታውም? ቸነፈሩ ስንቱን ዘረረ?! የስንቱን ደጅ ዘጋ … እንዲህ እየኖርን ዛሬ ላይ ደረስን።

ዛሬም ተርበናል። ችጋር ይዞናል። ድርቅ እንስሶችን፣ ወገኖቻችንን እየቀጠፋቸው ነው። የቁጥር ጸብ ከሌለ በስተቀር ችጋሩም፣ ረሃቡም፣ ድርቁም ካቅም በላይ ሆኖ ህጻናትን፣ አረጋዊያንን፣ እንስሦችን እንደፈጀና እየፈጃቸው ስለመሆኑ መከራከሪያም ሆነ ማደናበሪያ ማቅረብ የሚቻለው የለም። ሊኖርም አይችልም።

በተመሳሳይ ጥጋብ ያሰከራቸውና በዝርፊያ ላይ ተጠምደው “ልማት ላይ ነን” የሚሉ አሉ። ሁሉም የዚያች መከረኛ አገር “እኩል ዜጎች” ተብለው ይቆጠራሉ፤ ይጠራሉ። የዚህን መጨረሻ ስናስብ እናፍራለን፣ እናዝናለን፣ አንደነግጣለን። ስጋት ያርደናል። በዚህ መልኩ አይቀጥልምና!! የቀን እንጂ የሰው ጀግና የለውም እንደሚባለው!!

“ድርቅና ችጋር ያሉ፣ የነበሩና የሚኖሩ ናቸው። አሜሪካም ሆነ አውስትራሊያ ድርቅ አለ፤ ለምን እንዲህ በመረረ መልኩ አያችሁት? ድርቅ ብርቅ ነው እንዴ?” በሚል ጥያቄ የሚያቀርቡ “የልማት መሪዎችና አርበኞች” መልሳችን “ቀን ይፍረድ” ብቻ ነው።

ረሃቡ የቆየ መሆኑ

እንደሚታወቀው የዘንድሮ ምርት ዘመን ገና መንገድ ላይ ነው። ክረምቱ አላበቃም። ስለዚህ አሁን ይፋ የሆነው ችጋር ካለፈው አመት ተንከባሎ የመጣ በመሆኑ አሁን ተከሰተ የተባለው “የዝናብ እጥረት” ምክንያት ሊሆን አይችልም። ለቪኦኤ አማርኛው ክፍል መግለጫ የሰጡት የሚቲዎሮሎጂ ባለስልጣን የዝናብ እጥረት እንደሚከሰት ለሚመለከታቸው ሁሉ አስቀድመው ማሳወቃቸውን ተናግረዋል። “የአየር ንብረት ድርቅ ገብቷል” ሲሉ አዙረውም ቢሆን ችግሩን አምነዋል። ግብርና ሚኒስቴርም ድርቅ ስለመከሰቱ ተጠየቆ አላስተባበለም። በዚህ መነሻ 14 ሚሊዮን ሕዝብ በችጋር እስኪገረፍ ድረስ፣ 24 ሚሊዮን ህዝብ ለችጋር እስኪጋለጥ “ልማታዊ ነኝ” የሚለው ህወሃትና አጫፋሪዎቹ የት ነበሩ? “ልማታዊ ነን፣ ስራ ላይ ነን” የምትሉት እናንተ “የህወሃት ምርጥ ዜጎችና አገልጋዮች” ምን መልስ ልትሰጡ ትችላላችሁ? “በቀን ሶስት ጊዜ ትበላላችሁ” በማለት በድሆች ላይ ሲሳፈጥ የነበረውን “ሌጋሲ” አምላኪዎችና የሙት መንፈስ ድቤ ደላቂዎች ራዕዩና “ከሦስት ዓመት በኋላ መልሳችሁ ምንድነው? “ከ … ጋር መጪው ጊዜ ብሩህ ነው”?!

ከፖለቲካ ችጋር ነጻ ካልወጣን ሁሌም ችጋር ነው!! መልከ ብዙ ችጋር!! (ፎቶ: ለማሳያ የቀረበ)


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule