• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሬቻ የጅምላ ጭፍጨፋ ሃውልት እንዲሰራ ሃሳብ ቀረበ

October 6, 2016 10:19 am by Editor 1 Comment

የትግራይ ህዝብ ከማን አገዛዝ ነጻ እንዲወጣ እንደሚፈለግ በውል ባይታወቅም ራሱን “የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር” የሚለው ህወሃት በቢሾፍቱ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያካሄደው የጅምላ ጭፍጨፋ የሚዘክር ሃውልት እንዲቆም ሃሳብ መቀረቡ ተሰማ። የኢሬቻን ክብረ በዓል ለማክበር የተሰባሰቡ የኦሮሞና የሌሎች ቦታዎች ተወላጆች ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ጭፍጨፋ ትውልድ ሁሉ በማንና እንዴት እንደተፈጸመ እንዲያውቅ፣ እንዲማርና የተከፈለው ዋጋ ምን ያህል እንደሆነ እንዲረዳ፣ እንዲሁም ምስክር ሊሆን በሚያስችለው መልኩ ሃውልቱ እንደሚታነጽ ለማወቅ ተችሏል።

ለመብታቸው የተነሱና በሰላማዊ መንገድ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን “በቃህ፣ ልቀቀን” በማለታቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላለፉት አስራ አንድ ወራት ሲገደሉ፣ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉና ሲሰቃዩ መቆይታቸው ይታወሳል። ባለፈው ሳምንት ቢሾፍቱ የኢሬቻን ክብረ በዓል ላይ በተገኙ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ የተፈጸመው ግን አእምሮ ያላቸው ሁሉ ሊቀበሉት ያልተቻላቸው የግፍ ሁሉ ግፍ ሆኖ ተመዝግቧል።irreecha80

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ባሰሙ ወገኖች ላይ የደረሰው ይህ ታሪክ የማይረሳው ጭፍጨፋ ያስቆጣው ድፍን የኢትዮጵያን ህዝብ ነው። ክልል፣ ቦታ፣ ዘር፣ አካባቢና እምነት ሳይለይ ድፍን አገርን እንባ ያራጨው የጅምላ ጭፍጨፋ ያላሳዘነው የህዝብን ጩኸት “አንሰማም” ላሉት ክፍሎችና ድርጅታቸው ብቻ መሆኑ ደግሞ ሃዘኑን የከፋ እንዳደረገው በተለያዩ ዘዴዎች የሚወጡ የህዝብ አስተያየቶች ያረጋግጣሉ።

አንድም ጉዳት ያላደረሱ፣ ለማድረስም ባልሞከሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ላይ የህወሃት አንጋቾች በመርዝና በጥይት ያደረሱት ዘገናኝ ጭፍጨፋ በታሪክ ሁሉ ሲታወስ እንዲኖር በኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ መግባባት አለ። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችም ድጋፍ እንደሚሰጡ ማቅማማት የለም። ለጎልጉል ሃሳባቸውን የሰነዘሩ የስዊትዘርላንድ ነዋሪና የብሄሩ አባል “አሁን ቅድሚያ የሚሰጣቸው የነጻነት ስራዎች ቢኖሩም የዚህ ጭፍጨፋ ሰነድና መረጃዎች በጥንቃቄ ይከማቻሉ” ብለዋል። ሃውልቱ ህወሃት ያልተፈጠረ ታሪክ እየሠራ ሕዝብን ለመከፋፈል እንደተጠቀመባቸው ሳይሆን በመረጃና በማስረጃ የተደገፈ እንደሚሆን ተነግሯል።

ሌላ የሚኖሶታ ነዋሪ  የኦሮሞ ተወላጅ “ህወሃትና የኦሮሞ ህዝብ መካከል ለሚኖረው ግንብ  የሃውልቱ መሰራት ለትውልድ የሚዘልቅ መልስ ነው” ብለዋል። በማህበራዊ ገጾችም “ተስፋ ቁረጡ፣ ካሁን በኋላ እርቅ ጠይቆ ኦሮሞ ላይ ቁማር መጫወት አይቻልም” በሚል ስሜታቸው የመረረ መሆኑንን የሚገልጹ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

የጅምላ ጭፍጨፋውን ተከትሎ በሚኖሶታ የኦሮሞ ተወላጆች ባካሄዱት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ “ህዝብ እየጨፈጨፉ ዛፍ ሥር በመቀመጥ ይቅርታ መጠየቅ ያከተመበት አስተሳሰብ ነው” ሲሉ አቶ ጃዋር መሐመድ ተናግረዋል። ተሰብሳቢዎቹም በጭብጨባ ተቀብለውታል። አሁን ትግሉ የደረሰበት ደረጃ ወደፊት የመጓዝ ብቻ እንደሆነም ተጠቁሟል።

የሃውልቱ መገንባት ዋና አስፈላጊነት ግፍን ለማስታወስና ሁልጊዜ አንድን ወገን እየወቀሱ ለመኖር ሳይሆን ተመሳሳይ የመብት ጭቆና በድጋሚ እንዳይደርስ የተከፈለውን መስዋዕትነት በማሰብ እንዳይደገም ለማስተማር ነው ተብሏል። ከንግዲህ ወዲህ የኢሬቻ በዓል የሚከበረው ህወሃት የፈጸመውን ይህንን ጭፍጨፋ ሳይዘከር ስለማይሆን በሃውልቱ ጉዳይ ላይ ተጎጂ ወገኖች በሙሉ እንዲተባበሩ ሃሳብ ተሰጥቷልተነግሯል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Angile says

    October 8, 2016 06:19 am at 6:19 am

    የህዝብ ጥያቄ ስልጣን በአንድ አንስተኛ ጠባብ እጅ ስለወደቀ እኩል ተካፍለን አገራችን በጋራ እናስተዳድር ነው። የ 100 ሚሊዮን ህዝብ አገር በጥቂቶች መተዳደር ይብቃ። የአደራ መንግስት ሁሉንም ያካተተ ይቋቋም ነው ያለው ህዝቡ። ጥገና ሳይሆን ለውጥ። ሰው መቀያየር ሳይሆን የስርዐት ለውጥ። አባ ድላን አንስቶ ተሾመ ቶጋን መተካት ሳይሆን ምሁራንን የአገር ሽማግሌዎችን ተቃዋሚዎችን ያካተተ የአደራ መንግስት በአስቸኳይ ይቋቋም ነው ጥያቄው መልሱም እሱ ብቻ ነው።
    20 ሚሊዮን ብር ብቻ?
    ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡

    አዲስ አበባ ቄራ አካባቢ አንድ ቤት ለሽያጪ ወጥቷል፡፡ እድሜው በ18 እና 20 መካከል የሆነ ልጅ የመጀመሪያ ቤት ገዢ ሆኖ ከቦታው ይገኛል፡፡ ሻጪዎችም ከእድሜን ልጅነት፣ ከሀገሪቱ ሁኔታና ከዋጋው ውድነት አንፃር ለመቀለድ በማሰብ ከቤቱ ዋጋ በእጥፍ ጨምረው 20 ሚሊዮን ብር ነው ይሉታል፡፡ ለመሳቅና ልጁንም በማስደንገጥ ለማባረር አስበው እንደ ቀልድ ያደረጉት የ20 ሚሊዮን ብር ጨዋታ ግን ቁም ነገር ሆነና ቤቱን ልየው፣ ዋጋ ቀንሱ ወይም ሌሎችን በዚህ ወቅት መጠየቅ የሚገባቸውን ሳይጠይቅ ኑ እንፈራረም አለና አስደነገጣቸው፡፡ ለማመን ባለመቻላቸውና እየቀለደባቸው አንደሆነም ገምተው ለመቆጣት እየቃጣቸው እያሉ የ2 ሚሊዮን ብር ቼክ አወጣና የመፈራረሚያ ቅድሚያ ክፍያ አሳያቸው፡፡ እነሱም ያልጠበቁትን ግብይት እንዳደረጉ በመረዳት ካቀዱት ዋጋ በእጥፍ አትርፈው ቤቱን 20 አመት ለማይሞላ ልጅ በ20 ሚሊዮን ብር ሸጡ፡፡

    ይህም ብቸኛው ክስተት ሳይሆን በስፋትና በጥልቀት በየዘርፉ በየቀኑ የሚፈፅሙት ወንጀል ነው፡፡

    ትልቁ ጥያቄ ግን ይህ ልጅ ማን ነው የሚለው ብቻ ሳይሆን የማን ልጅና ዘመድ ነው የሚለው ነው፡፡ ልጁ ሕውሓት ነው፡፡ ወላጆቹና ዘመዶቹም ያው ሕውሓቶች ሲሆኑ አነማን ናቸው የሚለው ግን መጣራት ቢኖርበትም ሁሉም በዚህ አይነት ወንጀል ተሰማርተው ስለሚገኙ ሁሉም ናቸው ብሎ በሀዘን ማለፍ ሳይሆን በነሱ እየተበደለ ያለ ህዝብ በውስጡ ሰላም አግኝቶ፣ አንድነትን ፈጥሮና በጋራ ተነስቶ ሊያስወግዳቸው ይገባል፡፡ ወንጀላቸው ብዛቱ፣ አይነቱና ይዘቱ በየቀኑ አዲስና ህዝብ ሊቋቋመው የማይችል ሆኗል፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule