• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሬቻ የጅምላ ጭፍጨፋ ሃውልት እንዲሰራ ሃሳብ ቀረበ

October 6, 2016 10:19 am by Editor 1 Comment

የትግራይ ህዝብ ከማን አገዛዝ ነጻ እንዲወጣ እንደሚፈለግ በውል ባይታወቅም ራሱን “የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር” የሚለው ህወሃት በቢሾፍቱ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያካሄደው የጅምላ ጭፍጨፋ የሚዘክር ሃውልት እንዲቆም ሃሳብ መቀረቡ ተሰማ። የኢሬቻን ክብረ በዓል ለማክበር የተሰባሰቡ የኦሮሞና የሌሎች ቦታዎች ተወላጆች ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ጭፍጨፋ ትውልድ ሁሉ በማንና እንዴት እንደተፈጸመ እንዲያውቅ፣ እንዲማርና የተከፈለው ዋጋ ምን ያህል እንደሆነ እንዲረዳ፣ እንዲሁም ምስክር ሊሆን በሚያስችለው መልኩ ሃውልቱ እንደሚታነጽ ለማወቅ ተችሏል።

ለመብታቸው የተነሱና በሰላማዊ መንገድ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን “በቃህ፣ ልቀቀን” በማለታቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላለፉት አስራ አንድ ወራት ሲገደሉ፣ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉና ሲሰቃዩ መቆይታቸው ይታወሳል። ባለፈው ሳምንት ቢሾፍቱ የኢሬቻን ክብረ በዓል ላይ በተገኙ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ የተፈጸመው ግን አእምሮ ያላቸው ሁሉ ሊቀበሉት ያልተቻላቸው የግፍ ሁሉ ግፍ ሆኖ ተመዝግቧል።irreecha80

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ባሰሙ ወገኖች ላይ የደረሰው ይህ ታሪክ የማይረሳው ጭፍጨፋ ያስቆጣው ድፍን የኢትዮጵያን ህዝብ ነው። ክልል፣ ቦታ፣ ዘር፣ አካባቢና እምነት ሳይለይ ድፍን አገርን እንባ ያራጨው የጅምላ ጭፍጨፋ ያላሳዘነው የህዝብን ጩኸት “አንሰማም” ላሉት ክፍሎችና ድርጅታቸው ብቻ መሆኑ ደግሞ ሃዘኑን የከፋ እንዳደረገው በተለያዩ ዘዴዎች የሚወጡ የህዝብ አስተያየቶች ያረጋግጣሉ።

አንድም ጉዳት ያላደረሱ፣ ለማድረስም ባልሞከሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ላይ የህወሃት አንጋቾች በመርዝና በጥይት ያደረሱት ዘገናኝ ጭፍጨፋ በታሪክ ሁሉ ሲታወስ እንዲኖር በኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ መግባባት አለ። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችም ድጋፍ እንደሚሰጡ ማቅማማት የለም። ለጎልጉል ሃሳባቸውን የሰነዘሩ የስዊትዘርላንድ ነዋሪና የብሄሩ አባል “አሁን ቅድሚያ የሚሰጣቸው የነጻነት ስራዎች ቢኖሩም የዚህ ጭፍጨፋ ሰነድና መረጃዎች በጥንቃቄ ይከማቻሉ” ብለዋል። ሃውልቱ ህወሃት ያልተፈጠረ ታሪክ እየሠራ ሕዝብን ለመከፋፈል እንደተጠቀመባቸው ሳይሆን በመረጃና በማስረጃ የተደገፈ እንደሚሆን ተነግሯል።

ሌላ የሚኖሶታ ነዋሪ  የኦሮሞ ተወላጅ “ህወሃትና የኦሮሞ ህዝብ መካከል ለሚኖረው ግንብ  የሃውልቱ መሰራት ለትውልድ የሚዘልቅ መልስ ነው” ብለዋል። በማህበራዊ ገጾችም “ተስፋ ቁረጡ፣ ካሁን በኋላ እርቅ ጠይቆ ኦሮሞ ላይ ቁማር መጫወት አይቻልም” በሚል ስሜታቸው የመረረ መሆኑንን የሚገልጹ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

የጅምላ ጭፍጨፋውን ተከትሎ በሚኖሶታ የኦሮሞ ተወላጆች ባካሄዱት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ “ህዝብ እየጨፈጨፉ ዛፍ ሥር በመቀመጥ ይቅርታ መጠየቅ ያከተመበት አስተሳሰብ ነው” ሲሉ አቶ ጃዋር መሐመድ ተናግረዋል። ተሰብሳቢዎቹም በጭብጨባ ተቀብለውታል። አሁን ትግሉ የደረሰበት ደረጃ ወደፊት የመጓዝ ብቻ እንደሆነም ተጠቁሟል።

የሃውልቱ መገንባት ዋና አስፈላጊነት ግፍን ለማስታወስና ሁልጊዜ አንድን ወገን እየወቀሱ ለመኖር ሳይሆን ተመሳሳይ የመብት ጭቆና በድጋሚ እንዳይደርስ የተከፈለውን መስዋዕትነት በማሰብ እንዳይደገም ለማስተማር ነው ተብሏል። ከንግዲህ ወዲህ የኢሬቻ በዓል የሚከበረው ህወሃት የፈጸመውን ይህንን ጭፍጨፋ ሳይዘከር ስለማይሆን በሃውልቱ ጉዳይ ላይ ተጎጂ ወገኖች በሙሉ እንዲተባበሩ ሃሳብ ተሰጥቷልተነግሯል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Angile says

    October 8, 2016 06:19 am at 6:19 am

    የህዝብ ጥያቄ ስልጣን በአንድ አንስተኛ ጠባብ እጅ ስለወደቀ እኩል ተካፍለን አገራችን በጋራ እናስተዳድር ነው። የ 100 ሚሊዮን ህዝብ አገር በጥቂቶች መተዳደር ይብቃ። የአደራ መንግስት ሁሉንም ያካተተ ይቋቋም ነው ያለው ህዝቡ። ጥገና ሳይሆን ለውጥ። ሰው መቀያየር ሳይሆን የስርዐት ለውጥ። አባ ድላን አንስቶ ተሾመ ቶጋን መተካት ሳይሆን ምሁራንን የአገር ሽማግሌዎችን ተቃዋሚዎችን ያካተተ የአደራ መንግስት በአስቸኳይ ይቋቋም ነው ጥያቄው መልሱም እሱ ብቻ ነው።
    20 ሚሊዮን ብር ብቻ?
    ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡

    አዲስ አበባ ቄራ አካባቢ አንድ ቤት ለሽያጪ ወጥቷል፡፡ እድሜው በ18 እና 20 መካከል የሆነ ልጅ የመጀመሪያ ቤት ገዢ ሆኖ ከቦታው ይገኛል፡፡ ሻጪዎችም ከእድሜን ልጅነት፣ ከሀገሪቱ ሁኔታና ከዋጋው ውድነት አንፃር ለመቀለድ በማሰብ ከቤቱ ዋጋ በእጥፍ ጨምረው 20 ሚሊዮን ብር ነው ይሉታል፡፡ ለመሳቅና ልጁንም በማስደንገጥ ለማባረር አስበው እንደ ቀልድ ያደረጉት የ20 ሚሊዮን ብር ጨዋታ ግን ቁም ነገር ሆነና ቤቱን ልየው፣ ዋጋ ቀንሱ ወይም ሌሎችን በዚህ ወቅት መጠየቅ የሚገባቸውን ሳይጠይቅ ኑ እንፈራረም አለና አስደነገጣቸው፡፡ ለማመን ባለመቻላቸውና እየቀለደባቸው አንደሆነም ገምተው ለመቆጣት እየቃጣቸው እያሉ የ2 ሚሊዮን ብር ቼክ አወጣና የመፈራረሚያ ቅድሚያ ክፍያ አሳያቸው፡፡ እነሱም ያልጠበቁትን ግብይት እንዳደረጉ በመረዳት ካቀዱት ዋጋ በእጥፍ አትርፈው ቤቱን 20 አመት ለማይሞላ ልጅ በ20 ሚሊዮን ብር ሸጡ፡፡

    ይህም ብቸኛው ክስተት ሳይሆን በስፋትና በጥልቀት በየዘርፉ በየቀኑ የሚፈፅሙት ወንጀል ነው፡፡

    ትልቁ ጥያቄ ግን ይህ ልጅ ማን ነው የሚለው ብቻ ሳይሆን የማን ልጅና ዘመድ ነው የሚለው ነው፡፡ ልጁ ሕውሓት ነው፡፡ ወላጆቹና ዘመዶቹም ያው ሕውሓቶች ሲሆኑ አነማን ናቸው የሚለው ግን መጣራት ቢኖርበትም ሁሉም በዚህ አይነት ወንጀል ተሰማርተው ስለሚገኙ ሁሉም ናቸው ብሎ በሀዘን ማለፍ ሳይሆን በነሱ እየተበደለ ያለ ህዝብ በውስጡ ሰላም አግኝቶ፣ አንድነትን ፈጥሮና በጋራ ተነስቶ ሊያስወግዳቸው ይገባል፡፡ ወንጀላቸው ብዛቱ፣ አይነቱና ይዘቱ በየቀኑ አዲስና ህዝብ ሊቋቋመው የማይችል ሆኗል፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule