• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትግሬ-ወያኔ አቅጣጫ ከ፪ሺህ፯ ዓ.ም. በኋላ

June 20, 2015 08:28 pm by Editor 2 Comments

  • የትግሬ-ወያኔ አመራር በቅርቡ ባደረገው ስብሰባ ዐማራን ፈጽሞ ሳያጠፋ እንቅልፍ እንደማይወስደው ዳግም አረጋገጠ!

«ትናንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ዐማራው ስለሆነ፣» እያንዳንዱ ትግሬ ዐማራን በማጥፋት እንቅስቃሴ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን፣ የወያኔ የአገር-ውስጥ እና የውጭ የስለላ ቡድኖች ከፍተኛ አመራሮች በጥናቶቻቸው እንዳሣዩ የታመኑ የሞረሽ-ወገኔ ምንጮቻችን አረጋገጡ። የመረጃ ምንጮቻችን እንደሚያስረዱት፣ አጥኚዎቹ ከሕወሓት ፖሊት ቢሮ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት የትግሬ-ወያኔን ዘረኛ አገዛዝ ያለፉትን የ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት ጉዞ መዝነው፣ ለሥልጣኑ አስጊው ማን እንደሆነ በመተንተን፣ ከ፪ሺህ፯ ዓ.ም. በኋላ የትግሬ-ወያኔ እንዴት መቀጠል እንዳለበት ዝርዝር ጥናት አቅርበዋል።

በትግሬ-ወያኔ የስለላ ተቋሞች ከፍተኛ አካሎች አማካይነት የተደረገው ይህ ዝርዝር ጥናት፣ «የመፍትሔ ኃሣብ ነው» ያለውን ለሕወሓት ፖሊት ቢሮ ማቅረቡን ምንጮቻችን ገልጸዋል። በስለላ ቡድኖቹ አንኳር የጥናት ውጤት መሠረት ወያኔ ገና «ሀ» ብሎ የትጥቅ ትግል ሲጀምር ከኢምፔሪያዝም በላይ እና በፊት «ዐማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው» ብሎ መፈረጁ ትክክል እንዳልነበር፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣን ከያዘ በኋላም ቀደም ሲል የፈጸመውን ስሕተት በማረም እና በማስተካከል ፋንታ በያዘው የቆየ የተሳሳተ ፍረጃ ገፍቶ በዐማራው ላይ ያደረሰው ጥፋት፣ እኒህ ሁሉ ተደማምረው ዐማራው «ትግሬ ጠላቴ ነው» ብሎ እንዲያስብ እና በነገዱ ዙሪያ እንዲሰባሰብ እንዳስገደደ ያመለክታል። ይህም ለተተኪው የትግራይ ትውልድ ቋሚ ጠላት የገዛ መሆኑ ተጠቅሷል። ከዚህ በተጨማሪም፣ ከሻዕቢያ ጋር የተገባው መቋጫ ያልተገኘለት ጦርነት የትግራይን ሕዝብ ከሥጋ ዘመዱ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም ያቃባ እና ቋሚ የደም ጠላት የገዛለት መሆኑ ተመልክቷል። በመሆኑም የትግራይ ሕዝብ ከላይ በኤርትራውያን፣ ከታች እና ከመሐል ደግሞ በዐማራው መካከል ሣንዲዊች ተደርጎ እንዲያዝ ያደረገ በመሆኑ፣ የወያኔ የ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት የሥልጣን ጉዞ ለመጭው የትግራይ ትውልድ ደም የገዛለት፣ የሥጋት ምንጮችን ያራባበት እንደሆነ የስለላ ቡድኖቹ የጥናት ውጤት አረጋግጧል።

የስለላ ቡድኖቹ ጥናት ለወደፊት የትግሬ-ወያኔ እንዴት በሥልጣን ላይ መቀጠል እንደሚችል የሚከተለውን ምክር መስጠቱ ታውቋል። ለጊዜው ወያኔ በሥልጣን ላይ በመሆኑ፣ ችግሩን ማስተዋል ቢሣነውም፣ የትግራይ ትውልድ በመጭዎቹ ዘመናት የሚታወቀው በሀገር ከሃዲነት፣ በኢትዮጵያ አፍራሽነት፣ ኢትዮጵያውያንን በጎሣ አቧድኖ በማጫረስ እና አገሪቱን ዝግ መሬት በማድረጉ እንደሚሆን ጥናቱ ያወሣል። ለወደፊቱም ወያኔ እንዴት መቀጠል እንዳለበት የሰጠው የመፍትሔ ኃሣብ፥ የተፈጸመውን ጥፋት በምንም መልኩ ወደኋላ ተመልሶ ማስተካከል ስለማይቻል፣ ማድረግ ያለበት በዝምታ ወደፊት መቀጠል መሆኑን፣ በአገሪቱ ውስጥ ካሉት ነገዶች ትግሬን የሚያሰጋው ሌላ ማንም ሳይሆን፣ ዐማራው መሆኑን፣ እና ይህ ነገድ በምንም ተዓምር የመደራጀት ዕድል እንዳያገኝ ወያኔ የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበት ያስገነዝባል። ለዚህም ግብ ተግባራዊነት የተነደፉ ስልቶች፦

ሀ) ዐማራዎች ከሁለት በላይ ሆነው እንዳይንቀሳቀሱ የተጠናከረ የስለላ እና የክትትል መረብ እንዲዘረጋ ማድረግ፤

ለ) ወደውጪ አገር ለመሰደድ የሚፈልገውን ዐማራ በተለያዩ ስልቶች እንዲሰደድ ሁኔታዎችን በስውር በማመቻቸት ማሰደድ፤

ሐ) በአገር ቤት ያለውን እና ለመሰደድ ፈቃደኛ ያልሆነውን ደግሞ አንገቱን ሳያቀና በልዩ ልዩ መንገዶች ማስወገድ፤

መ) አንገታቸውን ያቀኑትን በተቀነባበረ መንገድ በሐሰት በመክሰስ በፍርድ ቤት የረጅም ጊዜ እስር በማስፈረድ ዕድሜያቸውን በእስር እንዲጨርሱ እና ተከታዮቻቸው ሞራላቸው እንዲላሽቅ ማድረግ፤

ሠ) ድኃ ከዕለት ምግቡ በቀር ሌላ ነገር ማሰብ ስለማይችል፣ ዐማራውን በድኅነት ማጥ ውስጥ የሚከቱ ስልቶችን በመንደፍ ከሆዱ አልፎ ሌላ ነገር አንጋጦ እንዳያይ ማድረግ፤

ረ) ዐማራው በብዛት ተከማችቶ የሚገኝባቸውን ከተሞች እና መንደሮች በልዩ ልዩ የግንባታ ስበቦች በማፍረስ የዐማራውን የአብሮነት እና ማኅበራዊ ትሥሥር መበጣጠስ፤

ሰ) ሌሎች ነገዶች፣ በተለይ ኦሮሞዎቹ፣ ከዐማራው ጋር ምንም ዓይነት ቀና ግንኙነት እንዳይኖራቸው በሁለቱ ነገዶች መካከል ልዩነቶችን የሚያሰፉ የፕሮፓጋንዳ ሥልቶችን ቀይሶ መንቀሳቀስ፣ የሚሉ ይገኙበታል።

ለእነዚህም ስልቶች ተግባራዊነት፦

ሀ) እያንዳንዱ ትግሬ በስለላ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ማድረግ፣

ለ) የትግራይ ሕዝብ የትግሉ መሠረት እንደመሆኑ መጠን ከአሁኑ በተሻለ መንገድ የሁሉም ነገሮች ተጠቃሚ በማድረግ በሙሉ ኃይሉ ከሕወሓት ጎን እንዲሰለፍ ማድረግ፤

ሐ) ሕወሓት በሥልጣን ላይ ከሌለ የትግሬ ነገድ ዛሬ የጨበጠው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ የበላይነት የማይቀጥል ከመሆኑም በላይ በወያኔ ተባባሪነት ተጠያቂ የሚሆነው ሕዝብ ጥቂት እንደማይሆን አውቆ ለሕወሓት ኅልውና የተለመደውን ትብብር ማድረግ እንዳለበት ያላሰለሰ ትምህርትና ቅስቀሳ መስጠት የማይታለፉ ተግባሮች መሆናቸውን የጥናት ቡድኑ መክሯል።

በቅርብ ሣምንታት ይህ አዲሱ የትግሬ-ወያኔ ዕቅድ በተግባር መተርጎም መጀመሩን የሚያመለክቱ ድርጊቶች ተበራክተዋል። ለአብነት ያህል ከሦሥት ቀናት በፊት ሰኔ ፰ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ሣሙኤል አወቀ የተባለውን እና ሰማያዊ ፓርቲን ወክሎ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ለፓርላማ አባልነት የተወዳደረውን የ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ዓመት ወጣት በአሠቃቂ ሁኔታ ደብረማርቆስ ከተማ ውስጥ የገደሉት አንድ ምሣሌ ነው። ቀደም ብሎም በሚያዝያ እና በግንቦት ወራት አያሌ የዐማራ ተወላጆች ለግድያ፣ ለእሥር እና ለእንግልት መዳረጋቸው የአደባባይ ሚሥጢር ነው።

የትግሬ-ወያኔዎች እንዲህ ያስባሉ፣ ኃሣባቸውንም በተግባር ይተረጉማሉ። ዐማራውስ ራሱን ከፈፅሞ ጥፋት ለማዳን ምን ያስባል? መጥፋት ወይስ መክቶ ጥፋትን መከላከል? እንደሞረሽ ወገኔ አቋም «ጅብ ከሚበላህ፣ በልተኸው ተቀደስ» ነውና፤ ይህ አገርን እና ትውልድን አጥፊ የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ ቡድን አጥፍቶን ከመጥፋቱ በፊት እንቅስቃሴውን የሚያመክን የተግባር እርምጃ ይጠይቃል። ለዚህም ዐማራው ተደራጅቶ ራሱን እና አገሩን ከፈጽሞ ጥፋት ሊታደግ ይገባል ብለን እናምናለን። ይህ ጉዳይ «ቆይ እንመካከር፣ እንወያይ» የሚባልበት አይደለም። አፋጣኝ የተግባር እርምጃ ይጠይቃል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

mwaoipr@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    June 25, 2015 12:21 pm at 12:21 pm

    TPLF is committing all the crimes against Ethiopia/Ethiopians supported by America, UK, EU and their subsidiers.

    3 days ago I wrote this to these intruders:

    Letter to the whitehouse, World bank, IMF, UN, etc: http://www.ethiomedia.com/102shows/5081.html
    It is clear for humans as well as for the inhumans. Isn’t it? Needless to tell you but
    Ethiopians’ sufferage is due to the USA-lead globalisation scheme rather the neocolonialism scramble. Everyone dies any way, but as usual Ethiopians shall endure all forms of inhumanities and liberate humanity including the (“disguised”) inhumans!

    Reply
  2. tewodros says

    July 2, 2015 01:12 am at 1:12 am

    what do u something , ለምን የተሻለ መረብ ፈጥራችሁ ወጣቱን እንዲገናኝ አታደርጉም!!”

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule