• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን ይውረድ የሽግግር መንግስት ይቋቋም

September 20, 2016 11:11 pm by Editor Leave a Comment

በአገራችን፣ ህወሓት በመጀመሪያ በትግራይ ከ40 አመት በፊት በመላ ኢትዮጵያ ደግሞ በበላይነት በሚቆጣጠረው ኢህአዴግ ከ25 አመት በፊት የጀመረው የግድያና የአፈና ስርዓት አሁንም በመቀጠል ላይ ነው፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ ተቋማዊ ባደረገው የዘውግ ፖለቲካ ምክንያት ህዝባችን ተከፋፍሎ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ውስጥ በተወሰኑ ክልሎች እንደ ባዕድ የሚታዩበት ሁኔታ ከተከሰተ ቆይቷል።

ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣኑን ፍፁማዊ ለማድረግ ሃይማኖትን በመሳሪያነት ስለሚጠቀም በክርስቲያኖች ውስጥና በሙስሊሞች ውስጥም ወደ ግጭት የሚያመራ ክፍፍል ፈጥሯል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ስርዓቱን ለማቆየት የተገነባው የዘውግና የሃይማኖት ክፍፍል ስርዓቱን ለማስወገድ ወደሚጠቅም መሳሪያነት እየተቀየረ ነው፡፡

በአገራችን ያሉ ዋናዎቹ ችግሮች፡

1. ህወሓት/ኢህአዴግ ገዳይ፣አፈኝና ከፋፋይ መሆኑና ህዝባችን በህይወት የመኖር ዋስትና ማጣቱ፣ ሰብአዊና ዴሞከራሲያዊ መብቶቹ መረገጣቸውና ባገሩ ውስጥ በነፃነት መኖር አለመቻሉ ናቸው።

በኢህአዴግ ውስጥ ህወሓት፡

1.1 ጉልበት በሚጠቀሙ ተቋሞች፡ በሰራዊቱ፣ በደህንነትና በእስር ቤቶች፣
1.2 በአስተሳሰብ ላይ ጫና በሚያደርጉ ተቋሞች፡ በመገናኛ ብዙሃንና በሃይማኖታዊ አመራሮች፣
1.3 በውጭ ጉዳይ
1.4 ከፍተኛ ያገሪቱን ሃብት በመቆጣጠርና በመዝረፍ በዘውግ ላይ የተመሰረተ ቡድናዊ የበላይነት
ይዟል፡፡

እነዚህን ችግሮች ለማስወገድ ወሳኙ እርምጃ ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን አስወግዶ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት ነው፡፡

ይህን ኣላማ ለማሳካት በትግሉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍታት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከነዚህም ችግሮች ውስጥ በሚከተሉት ላይ ትኩረት ያስፈልጋል፡፡

በአገራችን ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች፡

1. ህወሓት/ኢህአዴግ በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ሊያካሂድ ይችላል፡፡

አባይ ፀሃየና ስዩም መስፍን በትግራይ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ እነሱ „የዘር“ የሚሉትና ከሆሎካስትና ከሩዋንዳ እልቂት ጋር የሚያመሳስሉትና የእርስ በርስ ጦርነት አስከትሎ አገሪቷን የሚበታትን አደጋ እንደሚያሰጋ የሚገልፁት ማስፈራሪያ አለ፡፡

ይህ ማስፈራሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ለመግታትና የኢትዮጵያ አንድነትን ለመጠበቅ እርምጃ የሚወስዱ አስመለስለው ተቃውሞ ያነሳባቸውን ህዝብ ለመጨፍጨፍ የሚጠቀሙበት የለመዱት ስልት ነው፡፡ አባይ ፀሃየና ስዩም መስፍን የትግራይን ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መመስረት አላማቸው እንደሆነ በማኒፌስቶ ከገለፁት ጥቂት የህወሓት መስራቾች ውስጥ ስለሆኑ ለኢትዮጵያ አንድነት ተቆርቋሪዎች መስለው የመቅረብ የሞራል ብቃት የላቸውም፡፡ እንደዚሁም ሁለቱ ሰዎች የዘውግ ልዩነት ተቋማዊ እንዲሆን ካደረጉ በሁዋላ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን በዘረኝነት መፈረጃቸው ከቅንነት የመነጨ ቅስቀሳ አይደለም፡፡

ስለዚህ ሰራዊቱና የመንግስት ታጣቂው ሃይል የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች በወገኑ ላይ የጭፍጨፋ ወንጀል እንዳያስፈፅሙት መቃወም አለበት፡፡

2. ህዝብን የሚያጋጩ ስህተቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ በሚወስዳቸው የጭካኔ እርምጃዎች ምክንያት በህዝብ ውስጥ ስጋት ሰፍኗል፡፡ በዚህ የውጥረት ሁኔታ ስሜታቸውን መቆጣጠር የማይችሉና በህዝብ ውስጥ ግጭት የሚያስከተሉ እርምጃዎችን የሚወስዱ ግለሰቦችና ቡድኖች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ በህዝብ ውስጥ ግጭት ሲከሰት ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሊጠቀምበት
ይችላል፡፡

ስለዚህ ሁሉም ፍትህ፣ ሰላምና አንድነት የሚፈልጉ ወገኖች ለዘመናት አብሮ በኖረውና ነፃነቱን በጠበቀው ህዝብ ውስጥ ግብታዊ ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥረት እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡

የስም ዝርዝር᎓

1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ

በመጨረሻም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ወደ 16 የምንሆን የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ መግለጫ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ አሁን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቁጥራችን ከእጥፍ በላይ መብዛቱ ያነሳነው ሃሳብ በብዙ ሰዎች አእምሮ እንዳለና እየተጠናከረ እንደሚሄድ ያመለክታል፡፡

ሌሎችም በዲያስፖራው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የትግራይ ህዝብ ከጥንትም ለወደፊትም እጣ ፈንታው ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መሆኑንና ጥቅሙና ህልውናው የሚጠበቀው በፍትህ፣ በዴሞክራሲ፣ በእኩልነትና በአንድነት ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሲሆን ብቻ መሆኑን ተገንዝበው፤ የህወሓት ባለስልጣኖች በስልጣናቸው ላይ ለመቆየት የሚያደርጓቸውን መሰሪ ቅስቀሳዎች በማጋለጥና የሚፈፅሟቸውን ጭፍጨፋዎች በማውገዝ ድምፃቸውን እንዲያስሰሙና ወደ ትግሉ እንዲቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በዚህ መግለጫ ይዘት ላይ የሚስማሙና አስተያየቶች ያሏቸው ሰዎች ወደሚከተለው ኣድራሻ መፃፍ ይችላሉ፡፡

ethiocivic@gmail.com

8 መስከረም 2009

(ከአንድ ወር በፊት የትግራይ ተወላጆች የመጀመሪያውን መግለጫ አውጥተው ነበር – እዚህ ላይ ይገኛል)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule