• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን ይውረድ የሽግግር መንግስት ይቋቋም

September 20, 2016 11:11 pm by Editor Leave a Comment

በአገራችን፣ ህወሓት በመጀመሪያ በትግራይ ከ40 አመት በፊት በመላ ኢትዮጵያ ደግሞ በበላይነት በሚቆጣጠረው ኢህአዴግ ከ25 አመት በፊት የጀመረው የግድያና የአፈና ስርዓት አሁንም በመቀጠል ላይ ነው፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ ተቋማዊ ባደረገው የዘውግ ፖለቲካ ምክንያት ህዝባችን ተከፋፍሎ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ውስጥ በተወሰኑ ክልሎች እንደ ባዕድ የሚታዩበት ሁኔታ ከተከሰተ ቆይቷል።

ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣኑን ፍፁማዊ ለማድረግ ሃይማኖትን በመሳሪያነት ስለሚጠቀም በክርስቲያኖች ውስጥና በሙስሊሞች ውስጥም ወደ ግጭት የሚያመራ ክፍፍል ፈጥሯል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ስርዓቱን ለማቆየት የተገነባው የዘውግና የሃይማኖት ክፍፍል ስርዓቱን ለማስወገድ ወደሚጠቅም መሳሪያነት እየተቀየረ ነው፡፡

በአገራችን ያሉ ዋናዎቹ ችግሮች፡

1. ህወሓት/ኢህአዴግ ገዳይ፣አፈኝና ከፋፋይ መሆኑና ህዝባችን በህይወት የመኖር ዋስትና ማጣቱ፣ ሰብአዊና ዴሞከራሲያዊ መብቶቹ መረገጣቸውና ባገሩ ውስጥ በነፃነት መኖር አለመቻሉ ናቸው።

በኢህአዴግ ውስጥ ህወሓት፡

1.1 ጉልበት በሚጠቀሙ ተቋሞች፡ በሰራዊቱ፣ በደህንነትና በእስር ቤቶች፣
1.2 በአስተሳሰብ ላይ ጫና በሚያደርጉ ተቋሞች፡ በመገናኛ ብዙሃንና በሃይማኖታዊ አመራሮች፣
1.3 በውጭ ጉዳይ
1.4 ከፍተኛ ያገሪቱን ሃብት በመቆጣጠርና በመዝረፍ በዘውግ ላይ የተመሰረተ ቡድናዊ የበላይነት
ይዟል፡፡

እነዚህን ችግሮች ለማስወገድ ወሳኙ እርምጃ ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን አስወግዶ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት ነው፡፡

ይህን ኣላማ ለማሳካት በትግሉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍታት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከነዚህም ችግሮች ውስጥ በሚከተሉት ላይ ትኩረት ያስፈልጋል፡፡

በአገራችን ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች፡

1. ህወሓት/ኢህአዴግ በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ሊያካሂድ ይችላል፡፡

አባይ ፀሃየና ስዩም መስፍን በትግራይ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ እነሱ „የዘር“ የሚሉትና ከሆሎካስትና ከሩዋንዳ እልቂት ጋር የሚያመሳስሉትና የእርስ በርስ ጦርነት አስከትሎ አገሪቷን የሚበታትን አደጋ እንደሚያሰጋ የሚገልፁት ማስፈራሪያ አለ፡፡

ይህ ማስፈራሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ለመግታትና የኢትዮጵያ አንድነትን ለመጠበቅ እርምጃ የሚወስዱ አስመለስለው ተቃውሞ ያነሳባቸውን ህዝብ ለመጨፍጨፍ የሚጠቀሙበት የለመዱት ስልት ነው፡፡ አባይ ፀሃየና ስዩም መስፍን የትግራይን ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መመስረት አላማቸው እንደሆነ በማኒፌስቶ ከገለፁት ጥቂት የህወሓት መስራቾች ውስጥ ስለሆኑ ለኢትዮጵያ አንድነት ተቆርቋሪዎች መስለው የመቅረብ የሞራል ብቃት የላቸውም፡፡ እንደዚሁም ሁለቱ ሰዎች የዘውግ ልዩነት ተቋማዊ እንዲሆን ካደረጉ በሁዋላ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን በዘረኝነት መፈረጃቸው ከቅንነት የመነጨ ቅስቀሳ አይደለም፡፡

ስለዚህ ሰራዊቱና የመንግስት ታጣቂው ሃይል የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች በወገኑ ላይ የጭፍጨፋ ወንጀል እንዳያስፈፅሙት መቃወም አለበት፡፡

2. ህዝብን የሚያጋጩ ስህተቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ በሚወስዳቸው የጭካኔ እርምጃዎች ምክንያት በህዝብ ውስጥ ስጋት ሰፍኗል፡፡ በዚህ የውጥረት ሁኔታ ስሜታቸውን መቆጣጠር የማይችሉና በህዝብ ውስጥ ግጭት የሚያስከተሉ እርምጃዎችን የሚወስዱ ግለሰቦችና ቡድኖች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ በህዝብ ውስጥ ግጭት ሲከሰት ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሊጠቀምበት
ይችላል፡፡

ስለዚህ ሁሉም ፍትህ፣ ሰላምና አንድነት የሚፈልጉ ወገኖች ለዘመናት አብሮ በኖረውና ነፃነቱን በጠበቀው ህዝብ ውስጥ ግብታዊ ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥረት እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡

የስም ዝርዝር᎓

1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ

በመጨረሻም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ወደ 16 የምንሆን የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ መግለጫ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ አሁን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቁጥራችን ከእጥፍ በላይ መብዛቱ ያነሳነው ሃሳብ በብዙ ሰዎች አእምሮ እንዳለና እየተጠናከረ እንደሚሄድ ያመለክታል፡፡

ሌሎችም በዲያስፖራው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የትግራይ ህዝብ ከጥንትም ለወደፊትም እጣ ፈንታው ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መሆኑንና ጥቅሙና ህልውናው የሚጠበቀው በፍትህ፣ በዴሞክራሲ፣ በእኩልነትና በአንድነት ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሲሆን ብቻ መሆኑን ተገንዝበው፤ የህወሓት ባለስልጣኖች በስልጣናቸው ላይ ለመቆየት የሚያደርጓቸውን መሰሪ ቅስቀሳዎች በማጋለጥና የሚፈፅሟቸውን ጭፍጨፋዎች በማውገዝ ድምፃቸውን እንዲያስሰሙና ወደ ትግሉ እንዲቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በዚህ መግለጫ ይዘት ላይ የሚስማሙና አስተያየቶች ያሏቸው ሰዎች ወደሚከተለው ኣድራሻ መፃፍ ይችላሉ፡፡

ethiocivic@gmail.com

8 መስከረም 2009

(ከአንድ ወር በፊት የትግራይ ተወላጆች የመጀመሪያውን መግለጫ አውጥተው ነበር – እዚህ ላይ ይገኛል)

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule