• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እንዲህ ነው

March 10, 2016 12:42 am by Editor Leave a Comment

ዛሬ በስልጣን ላይ ያለው ጉደኛ ቡድን ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በየጊዜው ቅርጹንም ሆነ ይዘቱን ሲቀያይር መኖሩን መስራቾቹ ነግረውናል። አንዳንዱን እያየንም ታዝበናል። ከመገለጫዎቹ ጥቂቶቹ አንባገነንነት፣ ገዳይነት፣ አፋኝነትና ጠባብነት ወይም ዘረኝነት እንዲሁም ጥላቻ ናቸው።

ከዚህ ጥቅል ተፈጥሮው ሌላ ስልጣን ከያዘም ጊዜ ጀምሮ የሚታዩበት ግልፅ ባህርያት አሉ። አንደኛው እውነታን መካድ ወይም አለመቀበል ነው። አይኑ ስር ያለውን ግልፅ እውነታ አይቀበለም። በተለይ ተቃውሞ ወይም ውድቀት ወይም የሃሳብ ልዩነት ከሆነ በጭራሽ አይደራደርም። አዘውትሮ የሚጠቀምበት አሰልች ስልት ለእውነታው ወይም ለችግሩ ሃሰተኛ ባለቤት መፈለግ ነው። ይህም ተቃዋሚ ፓርቲ፣ አክራሪ ቡድን፣ ፀረሰላም ሃይል፣ ፀረልማት፣ ወዘተ ሊሆን ይችላል። እንዴት ያለ በሽታ ነው ጃል! ትክክለኛውን ህመም ለይቶ ትክክለኛ መድሃኒት ከመፈለግ ይልቅ ያለምክንያቱ ምክንያት መፈለግ።

ሁለተኛ መለያ ባህሪው ደግሞ እንቢተኝነት ነው። ኢህአዴግ ግትር ነው። እየተሸነፈ አሸናፊነቱን አያምንም። እየወደቀ አለሁ ይላል። እየጠፋ መልማቱን ይሰብካል።

ውድቀቱን እየጣለ ስኬቱን ብቻ ያወራል። የሚያሳዝነው ታዲያ የሚወድቀው ብቻውን ሳይሆን ከሃገር ጋር መሆኑ ነው። ብቻውን ቢወድቅ ኖሮ የእጁን አገኘ ማለት ብቻ ይበቃ ነበር።

ሌላው ጠባዩ ጥላቻና ቅራኔ ነው። ልዩነት የህልውናው መሰረት ነው። የሚፈልገው ልዩነት ብቻ ሳይሆን ጥላቻን የሚወልድ ልዩነት። የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነቱ ሳይሆን በልዩነቱ እንዲታወቅ ይፈልጋል። ብሄር ብሄረሰቦች የሚላቸው ቡድኖች እንዲስማሙ አይፈልግም። ፍቅራቸውን የሞት ያህል ይፈራዋል። እነርሱ ሲጣሉ ሽማግሌ ሆኖ በበላይነት መኖር ይፈልጋልና እነርሱ መስማማት የለባቸውም። ያሁኑ የአማራና ዖሮሞ በበለጠ መቀራረብ እንቅልፍ የነሳውም በዚህ ባህሪው ምክንያት ነው።

የመጨረሻውና እጅግ አደገኛው ባህሪው ሃገሪቱን በራሱ ያገዛዝ ዘይቤ ራሱ ነግሶ ለመኖር የሚያሳየው ቅዠት ነው። ለኢህአዴግ ከአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊነት ውጭ ሃይማኖት  የለም። ከልማታዊ መንግስት ውጪ አማራጭ ከንቱ ነው። ለኢትዮጵያ ከጎሳ ፌደራሊዝም በላይ ላሳር ነው። በጥቅሉ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግር መፍትሄው የኢህአዴግ አስተሳሰብና የኢህአዴግ ዘለአለማዊ አገዛዝ ነው። ታዲያ ከዚህ በላይ ጨርቅን ጥሎ ማበድ የት አለ ጎበዝ?

በመጨረሻም ለኢህአዴግና የሃገሬ ሰዎች ምክር ብጤ አለኝ።

በመጀመሪያ ለኢህአዴግ፣

ኢህአዴግ፣ እባክህ አስተሳሰብህም ሆነ አገዛዝህ ፎርሿልና ንቃ። የኢትዮጵያ ወቅታዊ ችግር ለዘለቄታዊ የሚፈታው በማን አለብኝነት፣ በትእቢት፣ በእብሪትና ፉከራ ሳይሆን ባስተዋይነት፣ በሆደሰፊነት፣ በምክክርና በፍቅር ነው። ይህን ሳትገነዘብ ቀርተህ በያዝከው  የጥፋት ጎዳና ዘመቻህን እቀጥላለሁ የምትል ከሆነ ግን መጨረሻህ እንጦረጦስ ባይሆን ከምላሴ ጸጉር!

ያገሬ ሰዎች፣ ተቃዋሚ ሃይላትና ዳያስፖራ፣

ይህን የታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያን ህዝብ ያንድነት ጎጆ እንደገና አሳምረን ለመስራት እንጠቀምበት። የህዝብን አንድነት የሚያውክና ለቡድናዊ ጥቅም ካልሆነ በቀር ለህዝብ የማይጠቅም ጥላቻን በመዝራት ለኢህአዴግ ላገርና ህዝብ መምቻ ዱላ አናቀብለው። አሁን የሚታየውን የመቀራረብ መንፈስ አበልፅጋችሁ ቀጥሉ። የችግራችን መፍትሄው ፍቅር ነው። ከተቀራረብንና በሰለጠነ መንገድ ከተወያየን የተበላሸውን ጠግነን የጎደለውን ሞልተን ህዝብ የሚኮራባት ሃገረ ኢትዮጵያን መፍጠር የማንችልበት ምንም ምክንያት የለም። እናም ተባበሩ! ልዩነትን ጤንነት እንጂ በሽታ አታድርጉት። ይህ ወቅት የፍትህና ዴሞክራሲ አንባ የሆነች ታላቋን ኢትዮጵያ የምንፈጥርበት አጋጣሚ ነውና ሁላችንም እናስተውል።

ቸር ይግጠመን

ህሩይ ደምሴ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule