• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እንዲህ ነው

March 10, 2016 12:42 am by Editor Leave a Comment

ዛሬ በስልጣን ላይ ያለው ጉደኛ ቡድን ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በየጊዜው ቅርጹንም ሆነ ይዘቱን ሲቀያይር መኖሩን መስራቾቹ ነግረውናል። አንዳንዱን እያየንም ታዝበናል። ከመገለጫዎቹ ጥቂቶቹ አንባገነንነት፣ ገዳይነት፣ አፋኝነትና ጠባብነት ወይም ዘረኝነት እንዲሁም ጥላቻ ናቸው።

ከዚህ ጥቅል ተፈጥሮው ሌላ ስልጣን ከያዘም ጊዜ ጀምሮ የሚታዩበት ግልፅ ባህርያት አሉ። አንደኛው እውነታን መካድ ወይም አለመቀበል ነው። አይኑ ስር ያለውን ግልፅ እውነታ አይቀበለም። በተለይ ተቃውሞ ወይም ውድቀት ወይም የሃሳብ ልዩነት ከሆነ በጭራሽ አይደራደርም። አዘውትሮ የሚጠቀምበት አሰልች ስልት ለእውነታው ወይም ለችግሩ ሃሰተኛ ባለቤት መፈለግ ነው። ይህም ተቃዋሚ ፓርቲ፣ አክራሪ ቡድን፣ ፀረሰላም ሃይል፣ ፀረልማት፣ ወዘተ ሊሆን ይችላል። እንዴት ያለ በሽታ ነው ጃል! ትክክለኛውን ህመም ለይቶ ትክክለኛ መድሃኒት ከመፈለግ ይልቅ ያለምክንያቱ ምክንያት መፈለግ።

ሁለተኛ መለያ ባህሪው ደግሞ እንቢተኝነት ነው። ኢህአዴግ ግትር ነው። እየተሸነፈ አሸናፊነቱን አያምንም። እየወደቀ አለሁ ይላል። እየጠፋ መልማቱን ይሰብካል።

ውድቀቱን እየጣለ ስኬቱን ብቻ ያወራል። የሚያሳዝነው ታዲያ የሚወድቀው ብቻውን ሳይሆን ከሃገር ጋር መሆኑ ነው። ብቻውን ቢወድቅ ኖሮ የእጁን አገኘ ማለት ብቻ ይበቃ ነበር።

ሌላው ጠባዩ ጥላቻና ቅራኔ ነው። ልዩነት የህልውናው መሰረት ነው። የሚፈልገው ልዩነት ብቻ ሳይሆን ጥላቻን የሚወልድ ልዩነት። የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነቱ ሳይሆን በልዩነቱ እንዲታወቅ ይፈልጋል። ብሄር ብሄረሰቦች የሚላቸው ቡድኖች እንዲስማሙ አይፈልግም። ፍቅራቸውን የሞት ያህል ይፈራዋል። እነርሱ ሲጣሉ ሽማግሌ ሆኖ በበላይነት መኖር ይፈልጋልና እነርሱ መስማማት የለባቸውም። ያሁኑ የአማራና ዖሮሞ በበለጠ መቀራረብ እንቅልፍ የነሳውም በዚህ ባህሪው ምክንያት ነው።

የመጨረሻውና እጅግ አደገኛው ባህሪው ሃገሪቱን በራሱ ያገዛዝ ዘይቤ ራሱ ነግሶ ለመኖር የሚያሳየው ቅዠት ነው። ለኢህአዴግ ከአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊነት ውጭ ሃይማኖት  የለም። ከልማታዊ መንግስት ውጪ አማራጭ ከንቱ ነው። ለኢትዮጵያ ከጎሳ ፌደራሊዝም በላይ ላሳር ነው። በጥቅሉ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ችግር መፍትሄው የኢህአዴግ አስተሳሰብና የኢህአዴግ ዘለአለማዊ አገዛዝ ነው። ታዲያ ከዚህ በላይ ጨርቅን ጥሎ ማበድ የት አለ ጎበዝ?

በመጨረሻም ለኢህአዴግና የሃገሬ ሰዎች ምክር ብጤ አለኝ።

በመጀመሪያ ለኢህአዴግ፣

ኢህአዴግ፣ እባክህ አስተሳሰብህም ሆነ አገዛዝህ ፎርሿልና ንቃ። የኢትዮጵያ ወቅታዊ ችግር ለዘለቄታዊ የሚፈታው በማን አለብኝነት፣ በትእቢት፣ በእብሪትና ፉከራ ሳይሆን ባስተዋይነት፣ በሆደሰፊነት፣ በምክክርና በፍቅር ነው። ይህን ሳትገነዘብ ቀርተህ በያዝከው  የጥፋት ጎዳና ዘመቻህን እቀጥላለሁ የምትል ከሆነ ግን መጨረሻህ እንጦረጦስ ባይሆን ከምላሴ ጸጉር!

ያገሬ ሰዎች፣ ተቃዋሚ ሃይላትና ዳያስፖራ፣

ይህን የታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያን ህዝብ ያንድነት ጎጆ እንደገና አሳምረን ለመስራት እንጠቀምበት። የህዝብን አንድነት የሚያውክና ለቡድናዊ ጥቅም ካልሆነ በቀር ለህዝብ የማይጠቅም ጥላቻን በመዝራት ለኢህአዴግ ላገርና ህዝብ መምቻ ዱላ አናቀብለው። አሁን የሚታየውን የመቀራረብ መንፈስ አበልፅጋችሁ ቀጥሉ። የችግራችን መፍትሄው ፍቅር ነው። ከተቀራረብንና በሰለጠነ መንገድ ከተወያየን የተበላሸውን ጠግነን የጎደለውን ሞልተን ህዝብ የሚኮራባት ሃገረ ኢትዮጵያን መፍጠር የማንችልበት ምንም ምክንያት የለም። እናም ተባበሩ! ልዩነትን ጤንነት እንጂ በሽታ አታድርጉት። ይህ ወቅት የፍትህና ዴሞክራሲ አንባ የሆነች ታላቋን ኢትዮጵያ የምንፈጥርበት አጋጣሚ ነውና ሁላችንም እናስተውል።

ቸር ይግጠመን

ህሩይ ደምሴ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule