• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝብን ለማውደም ውጤታማው መንገድ ታሪካቸውን የሚረዱበትን መንገድ ማስካድና ጨርሶውኑ መደምሰስ ነው”

January 12, 2015 10:30 am by Editor 7 Comments

“ሕዝብን ለማውደም ውጤታማው መንገድ ሰዎች ታሪካቸውን የሚረዱበትን መንገድ ማስካድና ጨርሶውኑ በመደምሰስ ነው” የሚለው የእንስሶች እርሻ ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ብሒል ሰሞኑን ከፍተኛ መነጋሪያ ሆኗል፡፡ ለዚሁም መነሻው በየተራ እንዲወድሙ ከተደረጉት የሕዝብ የማንነት መገለጫዎች መካከል አንደኛ ቅርስ የሆነው የጣይቱ ሆቴል መውደምን ተከትሎ ነው፡፡

የእንስሶች እርሻ መጽሐፍ ህወሃት በተሰነጠቀበት ወቅት የእነ መለስ መገለጫ ነው ተብሎ በስፋት ኢትዮጵያ ውስጥ ሲነበብ የነበረ መጽሐፍ እንደነበር ይታወሳል፡፡ የውኅዳኑ ደጋፊ ሪፖርተርም በየሳምንቱ እየተረጎመ ያቀርበው እንደነበር ጋዜጣው ምስክር ነው፡፡

ጋሼ ጳውሎስ ኞኞ በጻፈው “አጤ ምኒልክ” መፅሐፍ ገጽ 328-330 የሆቴሉ ታሪክ እንዲህ ይነበባል፡፡

በአዲስ አበባ የእንጦጦ ማርያም ቤተክርስቲያን ተሠርታ በምትመረቅበት ጊዜ በመላ ኢትዮጵያ ያሉ መኳንንት ለምረቃው ተጠርተው ነበር፡፡ ለተጠራው እንግዳ ማሳረፊያ እንጦጦ አይበቃ ስለነበር እቴጌ ጣይቱ ከእንጦጦ ተራራ ሥር ያለው ሕዝብ ሁሉ ለሚጠራው እንግዳ መጠለያ ቤት እንዲሰጥ ለመኑ፡፡ እንግዳ የሚያሳድር ሁሉ ሽሮ፣ በርበሬና ቅቤ፣ ዱቄትና ሥጋ ከቤተ መንግሥቱ እየወሰደ እንግዶቹን እንዲያስተናግድ አዘዙ፡፡ በዚህ ዓይነት የእንጦጦ ቤተ ክርስቲያን ምረቃ ተፈጸመ፡፡ ከዚህም በኋላ ለሚመጣው እንግዳ ማረፊያና መመገቢያ ችግር እየሆነ መጣ፡፡

ምኒልክ “እህእ” እያሉ ወሬ ያጠያይቁ ጀመር፡፡ “በፈረንጅ አገር ሆቴል የሚባል ቤት ስላለ ማንኛውም እንግዳ ገንዘቡን እየከፈለ ያርፍበታል፤ ምግቡንም ይበላበታል” አሏቸው፡፡ በዚህ መሠረት ሥራው እንዲጀመርአዝዘው ሕንጻው ተሠርቶ ሆቴል ቤቱ በ1898 ዓም በነሐሴ ወር ሥራው ጀመረ፡፡ ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ስለ ሆቴል ቤቱ ሲያብራሩ “ስሙም ሆቴል ተባለ” ይላሉ፡፡ ኃላፊነቱም፣ ሥራውንም እቴጌ ጣይቱ ተክበው ይመሩና ያስተዳድሩ ጀመር፡፡ በ1900 ዓም ጥቅምት 25 ቀን ምኒልክ በአዲስ አበባ ያሉ ዲፕሎማቶችንና የውጭ አገር ሰዎችን ጋብዘው ሆቴሉን አስመረቁ፡፡ የመጀመሪያው ሥራ አስኪያጅም ሙሴ ፍሬደሪክ ሐል ነበር:: በኋላ ግን አቶ ዘለቃ አጋርደው ተሾሙ፡፡

እንደ አገር አባባል ጣይቱ እጅ የሚያስቆረጥም ወጥ እያሠሩ ገበያ ቢጠብቁ ጠፋ:: እንኳን ምግብ መብላት ከግሪኮች ሻይ ቤት ገብቶ ሻይ መጠጣት ነውር ነበረና ጣይቱ ጠዋት የሚያሠሩት ወጥ ለሠራተኞቹ የማታ ራት ይሆን ጀመር፡፡ የሚስታቸው ገበያ ማጣት ያሳሰባቸው አጤ ምኒልክ አንድ ቀን ከችሎት ሊነሱ ሲሉ በአካባቢያቸው ላሉ መኩዋንንቶች “ጣይቱ ምግብ የሚሸጥበት ቤት ከፍታለችና ኑ እንሂድና ልጋብዛችሁ” ብለው ወሰዱዋቸው፡፡ መኳንንት በላ ጠጣና ምኒልክ 30 ብር ከፈሉ፡፡

በማግሥቱ እንደተለመደው ገበያ ቢጠበቅ ጠፋ ቀጥሎም ጠፋ፤ ቀጥሎም ጠፋ፡፡ እንደገና ምኒልክ ሆቴል ገብቶ መብላት ነውር ያለ መሆኑን ለመኳንንቱ ገልፀው እንደገና ምሣ ጋበዙ፡፡ በሌላው ቀን አሁንም ገበያ አልተገኘም፡፡ ቢጠበቅ ቢጠበቅ ድርሽ የሚል ሰው ጠፋ፡፡ በሌላ ቀን ደግሞ አጤ ምኒልክ ከችሎት ሊነሱ ሲሉ በዙሪያቸው ላሉ መኳንንት “ሰማችሁ ወዳጆቼ” አሉ:: “በፈረንጅ አገር አንድ ቀን አንድ ሰው የጋበዘ እንደሆነ ያ የተጋበዘ ሰው በሌላ ቀን ደግሞ ብድሩን ይከፍላል ብድሩን ካልከፈለ ግን እንደ ነውር ይቆጠርበታል፡፡” ብለው ንግግራቸውን ሳይጨርሱ መኳንንቱ “እርስዎን ፈርተንና አፍረን ነው እንጂ የሚሆንልን ከሆነ የምኒልክን ብድር ለመመለስ እኔ አለሁ” እያለ ተራ በተራ ከሆቴል ቤት ምኒልክንና ጣይቱን ይጋብዝ ጀመረ፡፡ ገበያ እየደራ ሄደ፡፡ ምሳችንን እቴጌ ሆቴል ሄደን እንብላ የሚለው ስለበዛም ስሙ እቴጌ ሆቴል ተባለ፡፡

ዛሬ በታላላቅና በሌሎችም ሆቴል ቤቶች ጋሻና ጦር እየተሰቀለ እናያለን፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አደራረግ የተጀመረው በምኒልክ ነው፡፡

[እምዬ ምኒልክ መጋቢት 3፤ 1900ዓም ለደጃዝማች ሥዩም የላኩት መልዕክት እንዲህ ይነበባል]

ይድረስ ለደጃዝማች ሥዩም፤

“. . . የላክኸው የዝሆን ጥርስ አልጋና ተምቤን የተሠራ ጋሻ ደረሰልኝ፡፡ ጋሻ ግን ለግራኝ ተብሎ ተሠርቶ እንደሆነ ነው እንጂ ሌላ ሰው ይይዘዋል ተብሎ አልተሠራም፡፡ ነገር ግን ለሆቴል ቤት ለላንቲካ እንዲሆን አደረግሁት. . . ”

**********************************
?
አይመስለኝም ነበር እሳት ወኔ ኖሮት
ጣይን የሚገላት
ወልዮልሽ አራዳ … …. ወዮልሽ ሃገሬ
ማን ሊያሞቅሽ ነዉ
አድማስ ተደርምሶ ጣይሽ ጠልቃ ዛሬ?
(Binu Ye Tsehay ፌሰቡክ)


“ሕዝብን ለማውደም ውጤታማው መንገድ ሰዎች ታሪካቸውን የሚረዱበትን መንገድ ማስካድና ጨርሶውኑ በመደምሰስ ነው” ጆርጅ ኦርዌል፡፡

taitu hoteltayitu hotelItegue-Taitu-Hoteltaitu hTaituHotelTaitu-hotelTaitu_hTaytu-Hotel


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. እምሩ ዘለቀ says

    January 12, 2015 07:22 pm at 7:22 pm

    እርማት
    ከ ሚስተር ሃል በኋላ የሆቴሉ አስተዳዳሪ የኔ አባት ዘለቀ አግደዉ (በጂሮንድ) ነበሩ ።

    Reply
    • Editor says

      January 12, 2015 07:32 pm at 7:32 pm

      ክቡር እምሩ ዘለቀ

      እርማቱን አንባቢያን እንዲያዩት አቅርበነዋል:: ከላይ ያተምነው ጽሁፍ እንዳለ የተወሰደው ከጳውሎስ ኞኞ መጽሃፍ በቀጥታ ተቀድቶ በመሆኑ ያንን ማስተካከል የሚያስቸግር መሆኑን እርስዎም የሚረዱልን ይመስለናል::

      ለላኩልን ማስተካከያ ከልብ እናመሰግናለን::

      አርታኢ/Editor
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ/Golgul: the Internet Newspaper
      http://www.goolgule.com
      editor@goolgule.com

      Reply
  2. aradaw says

    January 13, 2015 08:57 pm at 8:57 pm

    It is sad to see this, specially if you grow up next to this historic & gigantic (for us at the time) hotel. I remember going there and watch by the fence the national and international food ball players. At the time it was a home for football players and and we go out there and see and admire them. Watching the revolver door was a hue fun. We have never been inside for a longtime. After the opening of other big hotels it popularity diminished price went down and I and my friends finally got a chance to see the inside. It was a miracle to see inside after a longtime admirer from out side. Now, it is gone, one of my things to do is a spent at lease a night there. The building might be gone but its memory will never go away. It is outside the hotel I have the chance to touch the hands of Mengistu Worku, Luchiano, Italo, Gila, Awad, Getachew, Asmelash, Kiflom and others (forgot the names) after their triumph to win the African cup may fifty or fifty one year ago.

    Reply
  3. Damota says

    January 14, 2015 02:40 am at 2:40 am

    What about Sheraton? I HOPE WOYANA WILL NEVER BURN IT

    Reply
  4. Arbechew says

    January 15, 2015 11:40 pm at 11:40 pm

    The Wayene’ and there followers will be burn in Addis Ababa soon once and for ever. And also Ethiopian people will have to burn what ever history they have that is for sure.

    Reply
  5. Meweded says

    January 18, 2015 01:29 am at 1:29 am

    I am really sorry to hear Taytu burns, but it is Woyane history’s too. How can Woyane burn his own history. I know some resist Ethiopian believe it is only some group of Ethiopian history. This day some people start to divide our hero in there race. Moreover, I fill sham to read we have some people who start to think Ethiopian history as their own history only. Even if Menelik abused & killed a number of Ethiopian brothers and sisters his was the leader of one Ethiopia. This writer heart my filling b/c Menelik abused our brothers for the luck of knowledge but you did this with full of access to know everything.

    Reply
  6. Daniel G/E/A says

    January 18, 2015 09:35 pm at 9:35 pm

    ወይን ከሀገራችንና ከታሪካችን ወይንም ደግሞ ከስልጣኔው ርቀን ወደሗላ የቀረን ካልሆነ በስተቀር
    ልዩ ምልክታችን የሆነው ታሪካችንና የስልጣኔአችን መጀመርያ የሆኑት ቅርሶቻችን ሲወድሙና ሲጋዩ
    ትውልድ ዝም ማለቱ ምን አይነት እርግማን ደርሶብን ይሆን ?
    ማዳንና መንከባከብ ባንችልና ቢያቅተን እንዄ ሀዘናችንን መግለጵ እንዴት ያቅተን
    ኧረ ኢትዮጲያ የማናት?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule