• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

January 29, 2013 08:39 am by Editor Leave a Comment

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ”

የሱሰኛነት ነገር ሲነሳ ሰሞኑን ከወደ ሚሽጋን ጠቅላይግዛት የተሰማው ጉድ የሚያሰኝ ነው፡፡ የ43ዓመቷ ሊሳ በቀን ሦስት ሩብ መጠን ያለው የድመት ጸጉርጥቅል እንደምትበላ ተናግራለች፡፡

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ” በማለት የምትናገረው ይህች ግለሰብ ሱሰኝነቱ የጀመራት የዛሬ 15ዓመት እነደሆነና እስካሁ 3200 ጥቅርል እንደበላች ታስረዳለች፡፡ ጥቅልሉን ከወለል፣ ከሶፋ፣ … እንደምታዘጋጅ ገልጻ በጣም አሪፍ የሆነው ግን በቀጥታ ከድመቷ የምታገኘው እንደሆነ ተናግራለች፡፡

ማርገዝ –› መጠጣት –› ጽንሱ ማበላሸት –› ዳረጎት ማግኘት

ከደቡብ አፍሪካ አስደንጋጭ ነገር ከተሰማ ጥቂት ቀናት ቢያልፉም የዜናው አስደንጋጭነት ግን እስካሁንም እውን ነው፡፡ ከመንግሥት የሚገኝ ጥቂት ዳረጎት ተጠቃሚ ለመሆን እርጉዞች ልጆቻቸውን በሽተኛ ሆነው እንዲወለዱ እያደረጉ ነው፤ በተለይ ችግረኛ በሆኑ ከተሞች የሚኖሩ፡፡

የደቡብ አፍሪካ ቤተሰቦች ከመንግሥት ከሚያገኙት ጥቂት ጥቅማጥሞች መካከል በአንድ ልጅ 250 ራንድ ወይም በዶላር 28.40 ያገኛሉ፡፡ ልጁ በሽተኛ ከሆነ ድጎማው 1200 ራንድ ወይም በዶላር 137.28 ይሆናል፡፡ ስለዚህ በእርግዝና ወቅት በሽተኛ ልጅ በመውለድ ከመጠን በላይ የሚጠጡ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጠዋት ሦስት ሰዓት ጀምሮ በቀን ከአምስት እስከ ስድስት ጠርሙስ እንደሚጠጡ ተነግሯል፡፡

ጠ/ሚ/ር ሻሮን ሊነቁ ይሆን?

የዛሬ ሰባት ዓመት አካባቢ በድንገት ባጋጠማቸው የደም መርጋት በሽታ ራሳቸውን ስተው የሚገኙት የቀድሞው የእስራኤል ጠ/ሚ/ር ኤሪያል ሻሮን ሰሞኑን በጭንቅላታቸው ውስጥ ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ሁኔታ መመልከታቸውን ሐኪሞቻቸው ገልጸዋል፡፡

የ84ዓመቱ ሻሮን ተመልሰው ሊነቁ የሚችሉበት ሁኔታ እጅግ ዝቅተኛ እንደሆነ ሐኪሞች ቢናገሩም በአሁኑ ጊዜ ግን በጭንቅላታቸው ውስጥ የመስማትና አንዳንድ ክስተቶችን የማመላለስ ድርጊት እየተካሄደ እንደሆነ የሚጠቁም የምርመራ መረጃ ማግኘታቸውን ሐኪሞቹ ተናግረዋል፡፡

ለወራት ራሳቸውን ስተዋል፣ ሞተዋል፣ እያገገሙ ነው፣ ተመልሰው ሥራ ጀምረዋል፣ … ሲባልላቸው ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የቀብር ሥነስርዓታቸው የተጠናቀቀው አቶ መለስ እንደ ሻሮን “አሉ እየተባሉ” በሞትና ሕይወት ውስጥ ቢቆዩላቸው ምኞታቸው መሆኑን በወቅቱ ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ተመኝተውላቸው ነበር፡፡

ካስወለድክ ትታሰራለህ!

ከተለያዩ ሴቶች የአራት ልጆች አባት የሆነው ሲም ቴይለር ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ልጅ ቢጨምር ወደ እስር ቤት እንደሚወርድ ፍርድቤት ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

ለልጆቹ ማሳደጊያ ባመክፈል ወደ 100ሺህ ዶላር ዕዳ ለበት የኦሃዮ ጠቅላይ ግዛት ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ የዳኛውን ውሳኔ የተቃወመ ሲሆን ለማሳደጊያ ገንዘብ ባይሰጥም ልጆቹንም እንደሚገባው ሲከባከብ እንደኖረ ተናግሯል፡፡ ጠበቃው በበኩላቸው “ፍርድቤቱ በደንበኛዬ መኝታቤት ጉዳይ ላይ ነው ውሳኔ የሰጠው” በማለት የዳኛውን ውሳኔ ተቃውመዋል፡፡ ግለሰቡ ገንዘቡን እንደሚከፍል ሁኔታዎችን ካመቻቸ የማስወለድ መብቱ እንደገና ሊታይ እንደሚችል ዳኛው ተናግረዋል፡፡

የፍቅራቸው ፊኛ ሲፈነዳ

ጥንዶቹ ለመጋባት ሲወስኑ ዕቅዱ አየር ላይ የጋብቻው ሥነስርዓት እንዲሆን ነበር፡፡ በያዝነው የአውሮጳውያን ወር መጀመሪያ አካባቢ የታሰበው የጋብቻ ሥነስርዓት እንደታሰበው አልተጠናቀቀም፡፡

በደቡብ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ከነሙሽሮቹ ወደ 14የሚጠጉ ሰዎች የተጫኑበት የእሣት ፊኛ ሙሽሮቹ የጋብቻ ቃልኪዳናቸውን ከፈጸሙ በኋላ በአየር ላይ እንዳለ እክል ስለገጠመው ፓይለቱ ፊኛውን ባስቸኳይ ወደ ምድር እንዲወርድ ሲያደርግ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት ግን እንደሌለ አብሮ ተዘግቧል፡፡ ሙሽሮቹ ግን አሁን ተስፋ አልቆረጡም – ገና አለ ገና – እንደግማለን ብለዋል፡፡

17 ቢሊዮን መሬት መሰል ፕላኔቶች

በቅርቡ ከአሜሪካው የጠፈር ምርምር ማዕከል (ናሳ) በተገኘው መረጃ እያንዳንዳችን ቢያንስ አንድ የግላችን ፕላኔት ሊኖረን እንደሚችል ነው፡፡

በኬፕለር የጠፈር አርቆ መመልከቻ የተገኙት ፕላኔቶች ምድርን የሚመስሉ ሲሆን ተንታኞች ባገኙት መረጃ መሠረት ምድርን የሚመስሉ 17 ቢሊዮን ፕላኔቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ ነው፡፡ ምድርን መምሰላቸው ብቻ ሳይሆን በተመራማሪዎች አስተሳሰብ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ግምትም አለ፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ከጥቂት ቀናት በፊት በፈረንሳይ የሚገኝ ድርጅት በየጊዜው የትዊተር መልዕክት ሲተላለፍ የብርሃን ብልጭታ በማሳየት የትዊተር እንቅስቃሴ የሚከታተል የዓለማችንን ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡ ጨለማው አህጉር አሁም ጨለማ እንደወረሰው ነው፡፡

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule