• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

January 29, 2013 08:39 am by Editor Leave a Comment

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ”

የሱሰኛነት ነገር ሲነሳ ሰሞኑን ከወደ ሚሽጋን ጠቅላይግዛት የተሰማው ጉድ የሚያሰኝ ነው፡፡ የ43ዓመቷ ሊሳ በቀን ሦስት ሩብ መጠን ያለው የድመት ጸጉርጥቅል እንደምትበላ ተናግራለች፡፡

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ” በማለት የምትናገረው ይህች ግለሰብ ሱሰኝነቱ የጀመራት የዛሬ 15ዓመት እነደሆነና እስካሁ 3200 ጥቅርል እንደበላች ታስረዳለች፡፡ ጥቅልሉን ከወለል፣ ከሶፋ፣ … እንደምታዘጋጅ ገልጻ በጣም አሪፍ የሆነው ግን በቀጥታ ከድመቷ የምታገኘው እንደሆነ ተናግራለች፡፡

ማርገዝ –› መጠጣት –› ጽንሱ ማበላሸት –› ዳረጎት ማግኘት

ከደቡብ አፍሪካ አስደንጋጭ ነገር ከተሰማ ጥቂት ቀናት ቢያልፉም የዜናው አስደንጋጭነት ግን እስካሁንም እውን ነው፡፡ ከመንግሥት የሚገኝ ጥቂት ዳረጎት ተጠቃሚ ለመሆን እርጉዞች ልጆቻቸውን በሽተኛ ሆነው እንዲወለዱ እያደረጉ ነው፤ በተለይ ችግረኛ በሆኑ ከተሞች የሚኖሩ፡፡

የደቡብ አፍሪካ ቤተሰቦች ከመንግሥት ከሚያገኙት ጥቂት ጥቅማጥሞች መካከል በአንድ ልጅ 250 ራንድ ወይም በዶላር 28.40 ያገኛሉ፡፡ ልጁ በሽተኛ ከሆነ ድጎማው 1200 ራንድ ወይም በዶላር 137.28 ይሆናል፡፡ ስለዚህ በእርግዝና ወቅት በሽተኛ ልጅ በመውለድ ከመጠን በላይ የሚጠጡ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጠዋት ሦስት ሰዓት ጀምሮ በቀን ከአምስት እስከ ስድስት ጠርሙስ እንደሚጠጡ ተነግሯል፡፡

ጠ/ሚ/ር ሻሮን ሊነቁ ይሆን?

የዛሬ ሰባት ዓመት አካባቢ በድንገት ባጋጠማቸው የደም መርጋት በሽታ ራሳቸውን ስተው የሚገኙት የቀድሞው የእስራኤል ጠ/ሚ/ር ኤሪያል ሻሮን ሰሞኑን በጭንቅላታቸው ውስጥ ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ሁኔታ መመልከታቸውን ሐኪሞቻቸው ገልጸዋል፡፡

የ84ዓመቱ ሻሮን ተመልሰው ሊነቁ የሚችሉበት ሁኔታ እጅግ ዝቅተኛ እንደሆነ ሐኪሞች ቢናገሩም በአሁኑ ጊዜ ግን በጭንቅላታቸው ውስጥ የመስማትና አንዳንድ ክስተቶችን የማመላለስ ድርጊት እየተካሄደ እንደሆነ የሚጠቁም የምርመራ መረጃ ማግኘታቸውን ሐኪሞቹ ተናግረዋል፡፡

ለወራት ራሳቸውን ስተዋል፣ ሞተዋል፣ እያገገሙ ነው፣ ተመልሰው ሥራ ጀምረዋል፣ … ሲባልላቸው ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የቀብር ሥነስርዓታቸው የተጠናቀቀው አቶ መለስ እንደ ሻሮን “አሉ እየተባሉ” በሞትና ሕይወት ውስጥ ቢቆዩላቸው ምኞታቸው መሆኑን በወቅቱ ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ተመኝተውላቸው ነበር፡፡

ካስወለድክ ትታሰራለህ!

ከተለያዩ ሴቶች የአራት ልጆች አባት የሆነው ሲም ቴይለር ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ልጅ ቢጨምር ወደ እስር ቤት እንደሚወርድ ፍርድቤት ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

ለልጆቹ ማሳደጊያ ባመክፈል ወደ 100ሺህ ዶላር ዕዳ ለበት የኦሃዮ ጠቅላይ ግዛት ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ የዳኛውን ውሳኔ የተቃወመ ሲሆን ለማሳደጊያ ገንዘብ ባይሰጥም ልጆቹንም እንደሚገባው ሲከባከብ እንደኖረ ተናግሯል፡፡ ጠበቃው በበኩላቸው “ፍርድቤቱ በደንበኛዬ መኝታቤት ጉዳይ ላይ ነው ውሳኔ የሰጠው” በማለት የዳኛውን ውሳኔ ተቃውመዋል፡፡ ግለሰቡ ገንዘቡን እንደሚከፍል ሁኔታዎችን ካመቻቸ የማስወለድ መብቱ እንደገና ሊታይ እንደሚችል ዳኛው ተናግረዋል፡፡

የፍቅራቸው ፊኛ ሲፈነዳ

ጥንዶቹ ለመጋባት ሲወስኑ ዕቅዱ አየር ላይ የጋብቻው ሥነስርዓት እንዲሆን ነበር፡፡ በያዝነው የአውሮጳውያን ወር መጀመሪያ አካባቢ የታሰበው የጋብቻ ሥነስርዓት እንደታሰበው አልተጠናቀቀም፡፡

በደቡብ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ከነሙሽሮቹ ወደ 14የሚጠጉ ሰዎች የተጫኑበት የእሣት ፊኛ ሙሽሮቹ የጋብቻ ቃልኪዳናቸውን ከፈጸሙ በኋላ በአየር ላይ እንዳለ እክል ስለገጠመው ፓይለቱ ፊኛውን ባስቸኳይ ወደ ምድር እንዲወርድ ሲያደርግ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት ግን እንደሌለ አብሮ ተዘግቧል፡፡ ሙሽሮቹ ግን አሁን ተስፋ አልቆረጡም – ገና አለ ገና – እንደግማለን ብለዋል፡፡

17 ቢሊዮን መሬት መሰል ፕላኔቶች

በቅርቡ ከአሜሪካው የጠፈር ምርምር ማዕከል (ናሳ) በተገኘው መረጃ እያንዳንዳችን ቢያንስ አንድ የግላችን ፕላኔት ሊኖረን እንደሚችል ነው፡፡

በኬፕለር የጠፈር አርቆ መመልከቻ የተገኙት ፕላኔቶች ምድርን የሚመስሉ ሲሆን ተንታኞች ባገኙት መረጃ መሠረት ምድርን የሚመስሉ 17 ቢሊዮን ፕላኔቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ ነው፡፡ ምድርን መምሰላቸው ብቻ ሳይሆን በተመራማሪዎች አስተሳሰብ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ግምትም አለ፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ከጥቂት ቀናት በፊት በፈረንሳይ የሚገኝ ድርጅት በየጊዜው የትዊተር መልዕክት ሲተላለፍ የብርሃን ብልጭታ በማሳየት የትዊተር እንቅስቃሴ የሚከታተል የዓለማችንን ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡ ጨለማው አህጉር አሁም ጨለማ እንደወረሰው ነው፡፡

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule