• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

January 29, 2013 08:39 am by Editor Leave a Comment

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ”

የሱሰኛነት ነገር ሲነሳ ሰሞኑን ከወደ ሚሽጋን ጠቅላይግዛት የተሰማው ጉድ የሚያሰኝ ነው፡፡ የ43ዓመቷ ሊሳ በቀን ሦስት ሩብ መጠን ያለው የድመት ጸጉርጥቅል እንደምትበላ ተናግራለች፡፡

“የድመት ጸጉር የመብላት ሱሰኛ ነኝ” በማለት የምትናገረው ይህች ግለሰብ ሱሰኝነቱ የጀመራት የዛሬ 15ዓመት እነደሆነና እስካሁ 3200 ጥቅርል እንደበላች ታስረዳለች፡፡ ጥቅልሉን ከወለል፣ ከሶፋ፣ … እንደምታዘጋጅ ገልጻ በጣም አሪፍ የሆነው ግን በቀጥታ ከድመቷ የምታገኘው እንደሆነ ተናግራለች፡፡

ማርገዝ –› መጠጣት –› ጽንሱ ማበላሸት –› ዳረጎት ማግኘት

ከደቡብ አፍሪካ አስደንጋጭ ነገር ከተሰማ ጥቂት ቀናት ቢያልፉም የዜናው አስደንጋጭነት ግን እስካሁንም እውን ነው፡፡ ከመንግሥት የሚገኝ ጥቂት ዳረጎት ተጠቃሚ ለመሆን እርጉዞች ልጆቻቸውን በሽተኛ ሆነው እንዲወለዱ እያደረጉ ነው፤ በተለይ ችግረኛ በሆኑ ከተሞች የሚኖሩ፡፡

የደቡብ አፍሪካ ቤተሰቦች ከመንግሥት ከሚያገኙት ጥቂት ጥቅማጥሞች መካከል በአንድ ልጅ 250 ራንድ ወይም በዶላር 28.40 ያገኛሉ፡፡ ልጁ በሽተኛ ከሆነ ድጎማው 1200 ራንድ ወይም በዶላር 137.28 ይሆናል፡፡ ስለዚህ በእርግዝና ወቅት በሽተኛ ልጅ በመውለድ ከመጠን በላይ የሚጠጡ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጠዋት ሦስት ሰዓት ጀምሮ በቀን ከአምስት እስከ ስድስት ጠርሙስ እንደሚጠጡ ተነግሯል፡፡

ጠ/ሚ/ር ሻሮን ሊነቁ ይሆን?

የዛሬ ሰባት ዓመት አካባቢ በድንገት ባጋጠማቸው የደም መርጋት በሽታ ራሳቸውን ስተው የሚገኙት የቀድሞው የእስራኤል ጠ/ሚ/ር ኤሪያል ሻሮን ሰሞኑን በጭንቅላታቸው ውስጥ ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ሁኔታ መመልከታቸውን ሐኪሞቻቸው ገልጸዋል፡፡

የ84ዓመቱ ሻሮን ተመልሰው ሊነቁ የሚችሉበት ሁኔታ እጅግ ዝቅተኛ እንደሆነ ሐኪሞች ቢናገሩም በአሁኑ ጊዜ ግን በጭንቅላታቸው ውስጥ የመስማትና አንዳንድ ክስተቶችን የማመላለስ ድርጊት እየተካሄደ እንደሆነ የሚጠቁም የምርመራ መረጃ ማግኘታቸውን ሐኪሞቹ ተናግረዋል፡፡

ለወራት ራሳቸውን ስተዋል፣ ሞተዋል፣ እያገገሙ ነው፣ ተመልሰው ሥራ ጀምረዋል፣ … ሲባልላቸው ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የቀብር ሥነስርዓታቸው የተጠናቀቀው አቶ መለስ እንደ ሻሮን “አሉ እየተባሉ” በሞትና ሕይወት ውስጥ ቢቆዩላቸው ምኞታቸው መሆኑን በወቅቱ ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ተመኝተውላቸው ነበር፡፡

ካስወለድክ ትታሰራለህ!

ከተለያዩ ሴቶች የአራት ልጆች አባት የሆነው ሲም ቴይለር ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ልጅ ቢጨምር ወደ እስር ቤት እንደሚወርድ ፍርድቤት ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

ለልጆቹ ማሳደጊያ ባመክፈል ወደ 100ሺህ ዶላር ዕዳ ለበት የኦሃዮ ጠቅላይ ግዛት ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ የዳኛውን ውሳኔ የተቃወመ ሲሆን ለማሳደጊያ ገንዘብ ባይሰጥም ልጆቹንም እንደሚገባው ሲከባከብ እንደኖረ ተናግሯል፡፡ ጠበቃው በበኩላቸው “ፍርድቤቱ በደንበኛዬ መኝታቤት ጉዳይ ላይ ነው ውሳኔ የሰጠው” በማለት የዳኛውን ውሳኔ ተቃውመዋል፡፡ ግለሰቡ ገንዘቡን እንደሚከፍል ሁኔታዎችን ካመቻቸ የማስወለድ መብቱ እንደገና ሊታይ እንደሚችል ዳኛው ተናግረዋል፡፡

የፍቅራቸው ፊኛ ሲፈነዳ

ጥንዶቹ ለመጋባት ሲወስኑ ዕቅዱ አየር ላይ የጋብቻው ሥነስርዓት እንዲሆን ነበር፡፡ በያዝነው የአውሮጳውያን ወር መጀመሪያ አካባቢ የታሰበው የጋብቻ ሥነስርዓት እንደታሰበው አልተጠናቀቀም፡፡

በደቡብ ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ከነሙሽሮቹ ወደ 14የሚጠጉ ሰዎች የተጫኑበት የእሣት ፊኛ ሙሽሮቹ የጋብቻ ቃልኪዳናቸውን ከፈጸሙ በኋላ በአየር ላይ እንዳለ እክል ስለገጠመው ፓይለቱ ፊኛውን ባስቸኳይ ወደ ምድር እንዲወርድ ሲያደርግ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት ግን እንደሌለ አብሮ ተዘግቧል፡፡ ሙሽሮቹ ግን አሁን ተስፋ አልቆረጡም – ገና አለ ገና – እንደግማለን ብለዋል፡፡

17 ቢሊዮን መሬት መሰል ፕላኔቶች

በቅርቡ ከአሜሪካው የጠፈር ምርምር ማዕከል (ናሳ) በተገኘው መረጃ እያንዳንዳችን ቢያንስ አንድ የግላችን ፕላኔት ሊኖረን እንደሚችል ነው፡፡

በኬፕለር የጠፈር አርቆ መመልከቻ የተገኙት ፕላኔቶች ምድርን የሚመስሉ ሲሆን ተንታኞች ባገኙት መረጃ መሠረት ምድርን የሚመስሉ 17 ቢሊዮን ፕላኔቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ ነው፡፡ ምድርን መምሰላቸው ብቻ ሳይሆን በተመራማሪዎች አስተሳሰብ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ግምትም አለ፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ከጥቂት ቀናት በፊት በፈረንሳይ የሚገኝ ድርጅት በየጊዜው የትዊተር መልዕክት ሲተላለፍ የብርሃን ብልጭታ በማሳየት የትዊተር እንቅስቃሴ የሚከታተል የዓለማችንን ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡ ጨለማው አህጉር አሁም ጨለማ እንደወረሰው ነው፡፡

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule