• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

January 7, 2013 01:38 pm by Editor Leave a Comment

ጋብቻ በጠብመንጃ

ካለፈው የካቲት ወር ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የ“ጠብመንጃ ጋብቻ” አሁን በከፍተኛ ቁጥር ቀጥሎ እንዳለ ሰሞኑን ተሰምቷል፡፡ በላስቬጋስ የሚካሄደው ይኸው የጋብቻ ሥነስርዓት በቅርቡ በአንደኛ ደረጃ ት/ቤት በተተከፈተ ተኩስ ህጻናት ከሞቱ በኋላ ይቋረጣል ተብሎ ቢጠበቅም ሳይሆን ቀርቷል፡፡

ከተለያየ የዓለማችን ክፍል በመምጣት 500ዶላር አካባቢ በሚከፈልበትና በጠብመንጃ ሱቅ ውስጥ በሚካሄደው በዚህ ሥነስርዓት ሙሽሮች የተለያዩ ጠብመንጃዎች፣ ዑዚ መትረየስ፣ ኤኬ47፣ ወዘተ (ታንክ ሲቀር) የጦር መሣሪያዎችን በመያዝ ቃለመሃላቸውን ከፈጸሙ በኋላ ለእነርሱ ብቻ በተዘጋጀ ቦታ ላይ የዒላማ ተኩስ በማድረግ ጋብቻቸውን በተኩስ ያደምቁታል፡፡

ወ/ሮ የመከላከያ ሚ/ር

ከተመሠረተ ጀምሮ ከወንዶች በስተቀር እንስት ሚኒስትር ያላየው የአሜሪካው የመከላከያ ሚ/ር (ፔንታጎን) ምናልባት የመጀመሪያዋን ሴት የመከላከያ ሚኒስትር ሊያገኝ ይችላል፡፡

ቀድሞ በመ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን የነበሩትና ከአስራአምስት ወራት በፊት ከልጆቼ ጋር ጊዜ ማሳለፍ እፈልጋለሁ በማለት ሥራቸውን የለቀቁት ሚሼል ፍሎርኒይ ፕሬዚዳንት ኦባማ ሊሾሟቸው ይችላሉ ከተባሉት ምክትል ሚ/ሩ አሽተን ካርተርና ሪፓብሊካኑ ሴናተር ቸክ ሔግል በቀዳሚነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በአሁኑ ጊዜ በሐዋይ የባሕር ግዛት ሽርሽር ላይ ሲሆኑ በዚህ ሳምንት ተመራጩን ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ስድስት ተኩሳ አንድ ሳተች

በአሜሪካ የጆርጂያ ጠቅላይ ግዛት ነዋሪ በሆነችው ግለሰብ ቤት በመግባት ለመዝረፍ የሞከረው ሌላ እንዳሰበው አላጋጠመውም፡፡ ከሁለት መንትያ ልጆቿ ጋር የነበረችው እናት በሯ ሲንኳኳ እንደተለመደው ከበር በር እየዞሩ ዕቃ ከሚያሻሽጡ አንዱ መስሏት ሳትከፍት ትቀራለች፡፡  

ሁኔታው ግን እንዳሰበችው ሳይሆን ቀርቶ ዘራፊ ቤቷ መምጣቱን ስትገነዘብ በቶሎ ልጆቿን ይዛ ከጣራ ሥር በሚገኘው ትንሽ ክፍል (አቲክ) ውስጥ ትደበቃለች፡፡ ግን ባዶ እጇን አልነበረችም፤ ሽጉጥዋን ጥይት አጉርሳለች፡፡ ዘራፊው ክፍሉን ሁሉ በርብሮ እርሷና ልጆችዋ ወዳሉበት ሲደርስ፤- ተጠንቀቅ፣ አነጣጥር፣ ተኩስ!! ስድስቱን ጥይት ለቀቀችበት፤ አምስቱ ዒላማውን ሲመታ አንዱ ብቻ ሳተው፡፡ ፊቱን ይዞ እያለቀሰ እንደምንም አምልጦ ደሙን እያዘራ ወደመኪናው ቢገባም ብዙም ርቆ ለመሄድ አልቻለም፡፡ መንገድ ስቶ ከዛፍ ጋር ተላትሞ እዚያው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎታል፡፡ ቤት ያልነበረው አባወራ “ባለቤቴ ጀግና ነች፤ ራስዋንና ልጆችዋን በመከላከል አንድ የመሣሪያ ባለቤት ማድረግ የሚገባውን አድርጋለች” በማለት አወድሷታል፡፡

ዝነኛው ብስክሌተኛው ሊናዘዝ ነው

ባለፈው ጥቅምት ወር ሰባት ጊዜ ያሸነፈውን የፈረንሳይ ዙር ማዕረግ የተገፈፈው የዓለማችን ዝነኛ ብስክሌተኛ የነበረው አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ በይፋ ኃይልና አበረታች ዕጽ መውሰዱን በማመን ይቅርታ ሊጠይቅ ይችላል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡

በተደጋጋሚ የተነሳበትን የአበረታች ዕጽ ጉዳይ ሲክድ የነበረው አርምስትሮንግ ባለፈው ጥቅምት በእርሱ ላይ የወጣው ዘገባ “የስፖርቱ ዓለም ከተለመደው ታይቶ የማይታወቅ እጅግ የተወሳሰበ፣ እጅግ ዘመናዊና በባለሙያ የተጠና እንዲሁም የተሳካ የዕጽ ፕሮግራም” ማካሄዱን መስክሮበታል፡፡ ከብስክሌት ውድድር ዕድሜልኩን የተወገደው አርምስትሮንግ ጥፋቱን በይፋ በመናዘዝ ቅጣቱን ለማቅለልና ለወደፊት በሌሎች ስፖርቶች ለመወዳደር ማሰቡን ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡

ባዶ ተስፋ

ከጥቂት ወራት በፊት ሳንዲ የተባለችው ዓውሎነፋስ የቀላቀለችው ዝናብ የአሜሪካንን በርካታ ምስራቃዊ ጠቅላይ ግዛቶችን ባጥለቀለችና ንብረቶችን ባወደመች ጊዜ የጉዳቱን ተጠቂዎች ፕሬዚዳንት ኦባማ ሲጎበኙ ዶና ቫንዛንትን ሲያጽናኑ የተቀረጸው በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ትኩረት ስቦ ነበር፡፡

የአነስተኛ ንግድ ባለቤት የሆኑት ዶና በወቅቱ ከኦባማ ለእርሳቸውና ለሌሎች የጉዳቱ ተጠቂዎች መልሰው እንዲቋቋሙ ከመንግሥት ፈጣን ርዳታ እንደሚደረግላቸው ተስፋ የተሰጣቸውም ቢሆንም በቅርቡ ባደረጉት ቃለምልልስ እርሳቸውና ሌሎች ተጠቂዎች አንዳችም ምላሽ ከፕሬዚዳንቱ እንዳላገኙ፤ ተስፋው ባዶ እንደሆ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ሌላም ሰሞኑን “የመከላከያ ሠራዊቱን ስለሚደግፉ ምስጋናችን እንገልጽልዎታለን” የሚል ፈጽሞ ግለሰቧ ያልጠየቁት ዓይነት ደብዳቤ ከኦባማ እንደደረሳቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ምስሉን ያገኘነው ከፌስቡክ ነው፡፡ የ“ጀግናው” ሞት ያስቆጨው በሃዘኑ እስከዚህ ደርሷል፡፡ በገና በዓል ሥጋ ባንበላም፤ “የገና በዓል አይሞትም” ብለን ሥጋ ቤት ባንከፍትም፤ ሥጋ በፎቶና በቲቪ እያየን በዓሉን በቁጭት ብናሳልፈውስ?

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule