• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

January 7, 2013 01:38 pm by Editor Leave a Comment

ጋብቻ በጠብመንጃ

ካለፈው የካቲት ወር ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የ“ጠብመንጃ ጋብቻ” አሁን በከፍተኛ ቁጥር ቀጥሎ እንዳለ ሰሞኑን ተሰምቷል፡፡ በላስቬጋስ የሚካሄደው ይኸው የጋብቻ ሥነስርዓት በቅርቡ በአንደኛ ደረጃ ት/ቤት በተተከፈተ ተኩስ ህጻናት ከሞቱ በኋላ ይቋረጣል ተብሎ ቢጠበቅም ሳይሆን ቀርቷል፡፡

ከተለያየ የዓለማችን ክፍል በመምጣት 500ዶላር አካባቢ በሚከፈልበትና በጠብመንጃ ሱቅ ውስጥ በሚካሄደው በዚህ ሥነስርዓት ሙሽሮች የተለያዩ ጠብመንጃዎች፣ ዑዚ መትረየስ፣ ኤኬ47፣ ወዘተ (ታንክ ሲቀር) የጦር መሣሪያዎችን በመያዝ ቃለመሃላቸውን ከፈጸሙ በኋላ ለእነርሱ ብቻ በተዘጋጀ ቦታ ላይ የዒላማ ተኩስ በማድረግ ጋብቻቸውን በተኩስ ያደምቁታል፡፡

ወ/ሮ የመከላከያ ሚ/ር

ከተመሠረተ ጀምሮ ከወንዶች በስተቀር እንስት ሚኒስትር ያላየው የአሜሪካው የመከላከያ ሚ/ር (ፔንታጎን) ምናልባት የመጀመሪያዋን ሴት የመከላከያ ሚኒስትር ሊያገኝ ይችላል፡፡

ቀድሞ በመ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን የነበሩትና ከአስራአምስት ወራት በፊት ከልጆቼ ጋር ጊዜ ማሳለፍ እፈልጋለሁ በማለት ሥራቸውን የለቀቁት ሚሼል ፍሎርኒይ ፕሬዚዳንት ኦባማ ሊሾሟቸው ይችላሉ ከተባሉት ምክትል ሚ/ሩ አሽተን ካርተርና ሪፓብሊካኑ ሴናተር ቸክ ሔግል በቀዳሚነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በአሁኑ ጊዜ በሐዋይ የባሕር ግዛት ሽርሽር ላይ ሲሆኑ በዚህ ሳምንት ተመራጩን ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ስድስት ተኩሳ አንድ ሳተች

በአሜሪካ የጆርጂያ ጠቅላይ ግዛት ነዋሪ በሆነችው ግለሰብ ቤት በመግባት ለመዝረፍ የሞከረው ሌላ እንዳሰበው አላጋጠመውም፡፡ ከሁለት መንትያ ልጆቿ ጋር የነበረችው እናት በሯ ሲንኳኳ እንደተለመደው ከበር በር እየዞሩ ዕቃ ከሚያሻሽጡ አንዱ መስሏት ሳትከፍት ትቀራለች፡፡  

ሁኔታው ግን እንዳሰበችው ሳይሆን ቀርቶ ዘራፊ ቤቷ መምጣቱን ስትገነዘብ በቶሎ ልጆቿን ይዛ ከጣራ ሥር በሚገኘው ትንሽ ክፍል (አቲክ) ውስጥ ትደበቃለች፡፡ ግን ባዶ እጇን አልነበረችም፤ ሽጉጥዋን ጥይት አጉርሳለች፡፡ ዘራፊው ክፍሉን ሁሉ በርብሮ እርሷና ልጆችዋ ወዳሉበት ሲደርስ፤- ተጠንቀቅ፣ አነጣጥር፣ ተኩስ!! ስድስቱን ጥይት ለቀቀችበት፤ አምስቱ ዒላማውን ሲመታ አንዱ ብቻ ሳተው፡፡ ፊቱን ይዞ እያለቀሰ እንደምንም አምልጦ ደሙን እያዘራ ወደመኪናው ቢገባም ብዙም ርቆ ለመሄድ አልቻለም፡፡ መንገድ ስቶ ከዛፍ ጋር ተላትሞ እዚያው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎታል፡፡ ቤት ያልነበረው አባወራ “ባለቤቴ ጀግና ነች፤ ራስዋንና ልጆችዋን በመከላከል አንድ የመሣሪያ ባለቤት ማድረግ የሚገባውን አድርጋለች” በማለት አወድሷታል፡፡

ዝነኛው ብስክሌተኛው ሊናዘዝ ነው

ባለፈው ጥቅምት ወር ሰባት ጊዜ ያሸነፈውን የፈረንሳይ ዙር ማዕረግ የተገፈፈው የዓለማችን ዝነኛ ብስክሌተኛ የነበረው አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ በይፋ ኃይልና አበረታች ዕጽ መውሰዱን በማመን ይቅርታ ሊጠይቅ ይችላል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡

በተደጋጋሚ የተነሳበትን የአበረታች ዕጽ ጉዳይ ሲክድ የነበረው አርምስትሮንግ ባለፈው ጥቅምት በእርሱ ላይ የወጣው ዘገባ “የስፖርቱ ዓለም ከተለመደው ታይቶ የማይታወቅ እጅግ የተወሳሰበ፣ እጅግ ዘመናዊና በባለሙያ የተጠና እንዲሁም የተሳካ የዕጽ ፕሮግራም” ማካሄዱን መስክሮበታል፡፡ ከብስክሌት ውድድር ዕድሜልኩን የተወገደው አርምስትሮንግ ጥፋቱን በይፋ በመናዘዝ ቅጣቱን ለማቅለልና ለወደፊት በሌሎች ስፖርቶች ለመወዳደር ማሰቡን ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡

ባዶ ተስፋ

ከጥቂት ወራት በፊት ሳንዲ የተባለችው ዓውሎነፋስ የቀላቀለችው ዝናብ የአሜሪካንን በርካታ ምስራቃዊ ጠቅላይ ግዛቶችን ባጥለቀለችና ንብረቶችን ባወደመች ጊዜ የጉዳቱን ተጠቂዎች ፕሬዚዳንት ኦባማ ሲጎበኙ ዶና ቫንዛንትን ሲያጽናኑ የተቀረጸው በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ትኩረት ስቦ ነበር፡፡

የአነስተኛ ንግድ ባለቤት የሆኑት ዶና በወቅቱ ከኦባማ ለእርሳቸውና ለሌሎች የጉዳቱ ተጠቂዎች መልሰው እንዲቋቋሙ ከመንግሥት ፈጣን ርዳታ እንደሚደረግላቸው ተስፋ የተሰጣቸውም ቢሆንም በቅርቡ ባደረጉት ቃለምልልስ እርሳቸውና ሌሎች ተጠቂዎች አንዳችም ምላሽ ከፕሬዚዳንቱ እንዳላገኙ፤ ተስፋው ባዶ እንደሆ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ሌላም ሰሞኑን “የመከላከያ ሠራዊቱን ስለሚደግፉ ምስጋናችን እንገልጽልዎታለን” የሚል ፈጽሞ ግለሰቧ ያልጠየቁት ዓይነት ደብዳቤ ከኦባማ እንደደረሳቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ምስሉን ያገኘነው ከፌስቡክ ነው፡፡ የ“ጀግናው” ሞት ያስቆጨው በሃዘኑ እስከዚህ ደርሷል፡፡ በገና በዓል ሥጋ ባንበላም፤ “የገና በዓል አይሞትም” ብለን ሥጋ ቤት ባንከፍትም፤ ሥጋ በፎቶና በቲቪ እያየን በዓሉን በቁጭት ብናሳልፈውስ?

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule