• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተራራም ይሰረቃል? የራስ ዳሽኑ ፖለቲካ

September 17, 2016 10:49 pm by Editor 4 Comments

ራስ ዳሸን  ተራራ ከትግራይ “ክልል” ካርታ የመውጣቱ አሲዮ ቤሌማ  በብሄራዊ  ቴሌቪዥን ሲነገር፤ “ደፍረውናል! ንቀውናል! ብታምኑም ባታምኑም በቁም ሞተናል!” የሚለው የኮሎኔል መንግስቱ ንግግር በጆሮዬ ላይ አቃጨለ። ድፍረቱ እና ንቀቱ እንዳለ ሆኖ፣ በቁም የሞቱት ግን እኛ ሳንሆን እነሱ መሆናቸውን የሚያበስር የዜና እወጃ ነበር።

ነገሩ እንጂ ሁሉም የተለመደ ነገር ነው። ውሃ ይጠፋል፣ መብራት ይጠፋል፣ ስልክ ይጠፋል፣ ገንዘብ ይጠፋል፣ ኮንዶሚንየም ህንጻም ይጠፋል። ይህ በህወሃት ፖለቲካ ጥርሳቸውን ላልነቀሉትም አዲስ ነገር አይደለም። ዘረፋም ለነሱ አዲስ አይደለም። መንግስት ሆነው ከተቀመጡ በኋላ እንኳን 10 ቶን ቡና ሰርቀዋል፣ የመብራት ጀነሬተሮች  ሰርቀዋል፣ ከብሄራዊ ባንክ ወርቅ ሰርቀዋል … የህዝብን ድምጽም በተደጋጋሚ ሰርቀዋል። ተራራ ተሰርቆ ሲመለስ ግን የመጀመሪያው ነው።

ከኢትዮጵያ አንደኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ በከፍታ 4ኛው ተራራ ነው ራስ ዳሸን። ከሰሜን ጎንደር ከየዳ ወረዳ ተሰርቆ ለ25 አመታት ሙሉ ትግራይ ክልል ገብቶ ነበር። ወንጀሉ ወደ ትግራይ “ክልል” መግባቱ ብቻ አይደለም። አንድ ትውልድ እና በስነ-ምድር ሳይንስ በውሸት ታሪክ እንዲታነጽ መደረጉ እንጂ!

በነገራችን ላይ በመላው ሃገሪቱ መስከረም 2 ላይ መጀመር የነበረበት ትምህርት እስካሁን አልተጀመረም። ምክንያቱም ግልጽ ነው። ተማሪዎች እየተካሄደ ያለውን  አመጽ መጨረሻው ደረጃ ያደርሱታል በሚል ስጋት ነው። በሁለተኛው አለም ጦርነት ግዜ እንኳን ትምህርት አልተቋረጠም ነበር። ሂትለር ትምህርት እንዳይቋረጥ አዝዞ ነበር። ጦርነት እየተካሄደም፣ ትውልድ እንዳይጠፋ ውስጥ ለውስጥ ትምህርት ይሰጥ ነበር። የኛዎቹ  ጉዶች ግን ለአራት ወይንም አምስት ሰዎች ስልጣን ጥማት ሲባል “ትምህርት ገደል ይግባ” ያሉ ይመስላል።tigray-abay

ለመሆኑ ማን ነው ወንጀለኛው? መምህሩ፣ ህዝቡ ወይንስ ስርዓቱ? በመማርያ ካሪኩለም ውስጥ ራስ ዳሽንን ትግራይ ካርታ ውስጥ አስገብተው፣ መጽሃፍም አሳትመው ሲያበቁ ፣ የንግድ ድርጅቶቻቸውን ዳሽን ባንክ፣ ዳሽን ቢራ … እያሉ የሰየሙት የ”አማራው” ተወካዮች ከዶሮ ያልተሻለ ጭንቅላት ይዘው፣ ስብእናቸውን እና ማንነታቸውን ጥለው ፓርላማ የተባለው ጉረኖ ውስጥ ተሰግስገዋል።

አንድ ትውልድን በዘረኝነት መርዝ ብቻ ሳይሆን በዚህ አይነት ውሸት ከመረዙ በኋላ ይቅርታ መጠየቁ ምን ይበጃል? በፈተና ግዜ ራስ ዳሽን ተራራ የሚገኘው በሰሜን ጎንደር  ነው ብለው የወደቁትስ የአእምሮ ካሳ ሊከፈላቸው ነው? የህወሃት ሰዎች አፍ እንጂ ጆሮ ስለሌላቸው ጥያቄዎች እንጂ አንድም መልስ አናገኝም።

ለመጀመርያ ግዜ ከህወሃት አንደበት ይቅርታ የሚል ነገር ሰማን ልበል? አንድ የፖለቲካ ተንታኝ በአንድ ወቅት ሲናገር የበታችነት ስለሚሰማቸው ይቅርታን ከሌላው ይሿታል እንጂ ፈጽሞ አይሏትም እንዳለ ትዝ ይለኛል። ይህ አንደኛው መጨረሻውን ጠቋሚ መሆኑ ነው። በመጨረሻም እንዲህ ይሆናል። የፖለቲካ እስረኞች ይፈታሉ። ይቅርታ ማለት ይጀምራሉ። አጠር ያለች ረጅም የአብዮት ትንታኔ!

ይህ ይቅርታ ከመባሉ ሳምንታት በፊት፣ ሰላሳ ሚሊዮን አማራን ማጥፋት የሚችል ሃይል እንዳላቸው ደብረጽዮን በፌስቡክ ገጻቸው ጽፈውልናል። “አባ በጠጡ አቃቢቱን …”  እንዲሉ ይህንን የደብረጽዮን ጽሁፍ ሃይለማርያም ተቀብለው ሲያበቁ በመገናኛ ብዙሃን ቀርበው አንቦርቅቀውታል። “አብዮታዊ ሰራዊቱ ሕዝቡን እንዲገድል ትእዛዝ ሰጥቻለሁ!” ያሉ መሰለኝ። ለማመን እስኪከብድ ሂትለራዊ ቀረርቶ እና ፉከራም ሳይቀር አሰምተውናል። እነ አቦይ ስብሃት ታዲያ ጥጋቸውን ይዘው፣ በጨበጡት ብርጭቆ ሰንጥቀው እየመነጠሩዋቸው “ደፋር!” ሳይሏቸው አልቀረም። “ስልብ፣  በጌታው ብልት ይፎክራል!”  ይላሉ አበው።

ሕዝብን ለመጨረስ ትዕዛዝ  አስተላልፈናል ያሉበት አንደበታቸው ገና ሳይዘጋ ከጎንደር የሰረቅነውን ተራራ መልሰናል። ይህንን ተራራ ትግራይ ላይ አኑረነው ስለነበር ይቅርታ! ብለው መናገራቸው  ጨዋታ የመቀየር ስልት መሆኑ ነው። ሕዝብ ቀድሟቸው ባይሄድ ኖሮ ሊሸውዱት ይሞክሩ ነበር። የተለመደ ነጠላ ዜማ፣ በተመሳሳይ ግጥም –  በተመሳሳይ ዜማ ይዘው መከሰታቸው ግን ከእንሰሳ እንኳን ያልተሻሉ መሆናቸውን  የሚያሳይ ነው። ህዝቡን የሚያዩበት መነጽር አሁንም አልቀየሩትም።

ራስ ዳሽንን ከይቅርታ ጋር ለባለቤቱ መልሰናል ብለዋል። ከዚህ ቀደምም የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ተገቢ ነው ብለውናል። የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ተገቢ መሆኑን የባነኑት የአማራ ሕዝብ ሲነሳ መሆኑ ግን የፖለቲካ ጨዋታውን ቀልድ አስመስሎታል። በዚህ አላበቁም ለፈሰሰው የወገናችን ደም ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። የሰው ልጅን ህይወት እንደ እቃ ቆጥረው ሲያበቁ  በገዛ ራሱ ገንዘብ ሊክሱት ቃል መግባታቸው የባሰ ያሳምማል። የህይወት ካሳ አለ እንዴ? ለመሆኑ የአንድ ሰው ነብስ ስንት ያወጣል?

የራስ ዳሽን መመለስ ኢትዮጵያ አሁን የገባችበትን ችግር አይፈታውም። የሕወሃትን ማንነትን ግን የበለጠ ይፋ አድርጎታል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    September 18, 2016 02:21 pm at 2:21 pm

    This map was made by a mad TPLFite,so don’t think you have all the information,we will fight for our freedom as tigrians.

    Reply
  2. Tadesse says

    September 18, 2016 02:23 pm at 2:23 pm

    My last comment will be,don’t send me any thing to read.

    Reply
  3. Tadesse says

    September 18, 2016 02:42 pm at 2:42 pm

    ene yenafekegn selam new/Liya Kebede.

    Reply
  4. Nsansa says

    September 23, 2016 10:19 pm at 10:19 pm

    When I see this day dream TPLF map The Grate Renascence Dam has built for Grate Tigrai State because this dam has built 20 km from Ethio-Sudan boundry which inside the green map with Ethiopian expense they will have one of the biggest dam in Africa, I think this people are totally mindless.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule