• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ የጎሣ ፌደራሊዝም ሲፈተሽ

April 5, 2016 12:03 am by Editor Leave a Comment

የወያኔ አስተዳደር የማዕከላዊውን የመንግሥት ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ በሀገሪቱ ተግባራዊ ያደረገው የፌደራል ሥርዓት ጎሣን መሠረት ማድረጉ የሚታወቅ ነው። እንደ ወያኔ አገላለጽ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ደም መፋሰስን ያስቀረና ሀገሪቱንም ከመበታተን አደጋ የሚታደግ ነው ይላል። ይሁን እንጂ በተግባር እየተፈፀመ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ስንፈትሽ ይህ ወያኔ-ሰራሽ የሆነው የጎሣ ፌደራሊዝም ዓላማም ሆነ እያስከተለ ያለው ውጤት ከዚህ በተቃራኒ ሆኖ እናገኘዋለን።

በመጀመሪያ ምንም እንኳን በሕገ መንግሥቱ ላይ “ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብት አላቸው” ቢልም በተግባር ግን አምስት ብሔሮች ብቻ የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው አድርጓል። ሌሎች ከሰባ አምስት በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች ወይ ባለብዙ ብሔር ክልል በመፍጠር በዚያ እንዲታቀፉ ሲያደርግ፤ አልያም በሌሎች አምስቱ ክልሎች ውስጥ ህዳጣን /Minority/ ሆነው እንዲኖሩ ተደርጓል።

ከዚህም መገንዘብ የሚቻለው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ከሰማንያ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች በሚኖሩበት ሀገር ውስጥ ጎሣን ብቻ መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝምን ተግባራዊ ማድረግ እንደማይቻል ነው። በመሆኑም የሚከተለውን ጥያቄ እንድናነሳ እንገደዳለን፡- ወያኔ ይህን የጎሣ ፌደራሊዝም የሙጥኝ ብሎ ሩብ ምዕተ-ዓመት ለምን መጓዝ ፈለገ? በእኔ እምነት ይህን ያደረገው በሁለት ምክንያት ይመስለኛል።

ሀ. የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው በተደረጉ አምስቱ ክልሎች ተቀባይነትን /Internal Legitimacy/ ለማግኘት።

ለ. የወያኔን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የበላይነትን የሚቃወም ሕብረ-ብሔራዊነቱ የተጠናከረና በአንድነት የሚቆም ማኅበረሰብ እንዳይፈጠር ለመከላከል። ለምሣሌ በተለያዩ ወቅቶች በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ፣ በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ ቢሆንም በአንዱ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ በሌላ ክልል የሚኖረው ህዝብ በአይመለከተኝም ስሜት ጉዳዩን እንዲያየው ተደርጓል፤ እየተደረገም ነው።

በሌላ በኩል ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ህዝብና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላይ እያሳደረ ያለው ተፅዕኖና እያስከተለ ያለው ችግር የሚከተለውን ይመስላል።

ሀ. ባለብዙ ብሔር በሆኑ ክልሎች ውስጥ በየጊዜው የሚያገረሽ ማንነትን መሰረት ያደረገ ግጭት መከሰት።

ለ. በነዚህ ባለብዙ ብሔር ክልሎች ውስጥ የተፈጥሮ ሀብት ክፍፍልን፣ የድንበር ወሰንን እንዲሁም በክልልና በወረዳ ምክር ቤቶች ውስጥ በሚኖር የውክልና ጥያቄን መሰረት ያደረገ ውጥረት እና ግጭት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል።

ሐ. ዜጎች በሀገሪቱ በየትኛውም ክልል ተንቀሳቅሰው የመሥራት፣ የመኖርና ሀብት የማፍራት መብታቸው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንዲገታ ተደርጓል።

መ. ዜጎች በችሎታቸው ሳይሆን በብሔር ማንነታቸው በመመዘናቸው፤ የሀገሪቱ ቢሮክራሲ የተንዛዛና መልካም አስተዳደር የጎደለው እንዲሁም ለከፍተኛ ሙስናና ምዝበራ የተጋለጠ እንዲሆን አድርጓል።

ሠ. ሀገራዊ ራዕይ ያላቸውና የወያኔን መንግሥት መገዳደር የሚችሉ ሕብረ ብሔራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይፈጠሩ፤ ይልቁንም ብሔር ተኮር የሆኑ ድንክ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ አሸን እንዲፈሉ በማድረጉ፤ ወያኔን በሠላማዊ የፖለቲካ ትግል ማስወገድ እንዳይቻል አድርጓል።

ረ. ወያኔ ሆን ብሎ በሚያሰረጨው ታሪካዊ-ቅሰጣ /Historical Revisionism/ መሰረት በተለያዩ ክልሎች መካከል ከፍተኛ የሚባል ጥላቻ እንዲነግሥ ከማድረጉ ባሻገር፤ ነገን በደም እንዲፈላለጉ እያደረገ ይገኛል።

በአጠቃላይ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም ወያኔ እንደሚለው በሀገሪቱ ደም መፋሰስን የሚያስቆም ሳይሆን፤ ይልቁን እንደ ባልከን ሀገሮች ከፍተኛ ለሚባል ደም መፋሰስና መበታተን የሚዳርግ ትልቅ አደጋን ያዘለ ነው። በመሆኑም በዜጎች መካከል ግንዛቤን ከመፍጠር ጀምሮ በሀገራችንና በህዝባችን ላይ ያንዣበበውን አደጋ ከወዲሁ ለማስቀረት ወያኔን በጋራ ልናስወግደው ይገባል።

ተስፋዬ ገብረዮሐንስ (ከጀርመን)

tesfayejohn@hotmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule