• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ የጎሣ ፌደራሊዝም ሲፈተሽ

April 5, 2016 12:03 am by Editor Leave a Comment

የወያኔ አስተዳደር የማዕከላዊውን የመንግሥት ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ በሀገሪቱ ተግባራዊ ያደረገው የፌደራል ሥርዓት ጎሣን መሠረት ማድረጉ የሚታወቅ ነው። እንደ ወያኔ አገላለጽ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ደም መፋሰስን ያስቀረና ሀገሪቱንም ከመበታተን አደጋ የሚታደግ ነው ይላል። ይሁን እንጂ በተግባር እየተፈፀመ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ስንፈትሽ ይህ ወያኔ-ሰራሽ የሆነው የጎሣ ፌደራሊዝም ዓላማም ሆነ እያስከተለ ያለው ውጤት ከዚህ በተቃራኒ ሆኖ እናገኘዋለን።

በመጀመሪያ ምንም እንኳን በሕገ መንግሥቱ ላይ “ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብት አላቸው” ቢልም በተግባር ግን አምስት ብሔሮች ብቻ የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው አድርጓል። ሌሎች ከሰባ አምስት በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች ወይ ባለብዙ ብሔር ክልል በመፍጠር በዚያ እንዲታቀፉ ሲያደርግ፤ አልያም በሌሎች አምስቱ ክልሎች ውስጥ ህዳጣን /Minority/ ሆነው እንዲኖሩ ተደርጓል።

ከዚህም መገንዘብ የሚቻለው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ከሰማንያ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች በሚኖሩበት ሀገር ውስጥ ጎሣን ብቻ መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝምን ተግባራዊ ማድረግ እንደማይቻል ነው። በመሆኑም የሚከተለውን ጥያቄ እንድናነሳ እንገደዳለን፡- ወያኔ ይህን የጎሣ ፌደራሊዝም የሙጥኝ ብሎ ሩብ ምዕተ-ዓመት ለምን መጓዝ ፈለገ? በእኔ እምነት ይህን ያደረገው በሁለት ምክንያት ይመስለኛል።

ሀ. የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው በተደረጉ አምስቱ ክልሎች ተቀባይነትን /Internal Legitimacy/ ለማግኘት።

ለ. የወያኔን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የበላይነትን የሚቃወም ሕብረ-ብሔራዊነቱ የተጠናከረና በአንድነት የሚቆም ማኅበረሰብ እንዳይፈጠር ለመከላከል። ለምሣሌ በተለያዩ ወቅቶች በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ፣ በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ ቢሆንም በአንዱ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ በሌላ ክልል የሚኖረው ህዝብ በአይመለከተኝም ስሜት ጉዳዩን እንዲያየው ተደርጓል፤ እየተደረገም ነው።

በሌላ በኩል ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ህዝብና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላይ እያሳደረ ያለው ተፅዕኖና እያስከተለ ያለው ችግር የሚከተለውን ይመስላል።

ሀ. ባለብዙ ብሔር በሆኑ ክልሎች ውስጥ በየጊዜው የሚያገረሽ ማንነትን መሰረት ያደረገ ግጭት መከሰት።

ለ. በነዚህ ባለብዙ ብሔር ክልሎች ውስጥ የተፈጥሮ ሀብት ክፍፍልን፣ የድንበር ወሰንን እንዲሁም በክልልና በወረዳ ምክር ቤቶች ውስጥ በሚኖር የውክልና ጥያቄን መሰረት ያደረገ ውጥረት እና ግጭት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል።

ሐ. ዜጎች በሀገሪቱ በየትኛውም ክልል ተንቀሳቅሰው የመሥራት፣ የመኖርና ሀብት የማፍራት መብታቸው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንዲገታ ተደርጓል።

መ. ዜጎች በችሎታቸው ሳይሆን በብሔር ማንነታቸው በመመዘናቸው፤ የሀገሪቱ ቢሮክራሲ የተንዛዛና መልካም አስተዳደር የጎደለው እንዲሁም ለከፍተኛ ሙስናና ምዝበራ የተጋለጠ እንዲሆን አድርጓል።

ሠ. ሀገራዊ ራዕይ ያላቸውና የወያኔን መንግሥት መገዳደር የሚችሉ ሕብረ ብሔራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይፈጠሩ፤ ይልቁንም ብሔር ተኮር የሆኑ ድንክ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ አሸን እንዲፈሉ በማድረጉ፤ ወያኔን በሠላማዊ የፖለቲካ ትግል ማስወገድ እንዳይቻል አድርጓል።

ረ. ወያኔ ሆን ብሎ በሚያሰረጨው ታሪካዊ-ቅሰጣ /Historical Revisionism/ መሰረት በተለያዩ ክልሎች መካከል ከፍተኛ የሚባል ጥላቻ እንዲነግሥ ከማድረጉ ባሻገር፤ ነገን በደም እንዲፈላለጉ እያደረገ ይገኛል።

በአጠቃላይ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም ወያኔ እንደሚለው በሀገሪቱ ደም መፋሰስን የሚያስቆም ሳይሆን፤ ይልቁን እንደ ባልከን ሀገሮች ከፍተኛ ለሚባል ደም መፋሰስና መበታተን የሚዳርግ ትልቅ አደጋን ያዘለ ነው። በመሆኑም በዜጎች መካከል ግንዛቤን ከመፍጠር ጀምሮ በሀገራችንና በህዝባችን ላይ ያንዣበበውን አደጋ ከወዲሁ ለማስቀረት ወያኔን በጋራ ልናስወግደው ይገባል።

ተስፋዬ ገብረዮሐንስ (ከጀርመን)

tesfayejohn@hotmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule