• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ የጎሣ ፌደራሊዝም ሲፈተሽ

April 5, 2016 12:03 am by Editor Leave a Comment

የወያኔ አስተዳደር የማዕከላዊውን የመንግሥት ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ በሀገሪቱ ተግባራዊ ያደረገው የፌደራል ሥርዓት ጎሣን መሠረት ማድረጉ የሚታወቅ ነው። እንደ ወያኔ አገላለጽ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ደም መፋሰስን ያስቀረና ሀገሪቱንም ከመበታተን አደጋ የሚታደግ ነው ይላል። ይሁን እንጂ በተግባር እየተፈፀመ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ስንፈትሽ ይህ ወያኔ-ሰራሽ የሆነው የጎሣ ፌደራሊዝም ዓላማም ሆነ እያስከተለ ያለው ውጤት ከዚህ በተቃራኒ ሆኖ እናገኘዋለን።

በመጀመሪያ ምንም እንኳን በሕገ መንግሥቱ ላይ “ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብት አላቸው” ቢልም በተግባር ግን አምስት ብሔሮች ብቻ የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው አድርጓል። ሌሎች ከሰባ አምስት በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች ወይ ባለብዙ ብሔር ክልል በመፍጠር በዚያ እንዲታቀፉ ሲያደርግ፤ አልያም በሌሎች አምስቱ ክልሎች ውስጥ ህዳጣን /Minority/ ሆነው እንዲኖሩ ተደርጓል።

ከዚህም መገንዘብ የሚቻለው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ከሰማንያ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች በሚኖሩበት ሀገር ውስጥ ጎሣን ብቻ መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝምን ተግባራዊ ማድረግ እንደማይቻል ነው። በመሆኑም የሚከተለውን ጥያቄ እንድናነሳ እንገደዳለን፡- ወያኔ ይህን የጎሣ ፌደራሊዝም የሙጥኝ ብሎ ሩብ ምዕተ-ዓመት ለምን መጓዝ ፈለገ? በእኔ እምነት ይህን ያደረገው በሁለት ምክንያት ይመስለኛል።

ሀ. የራሳቸው ክልል እንዲኖራቸው በተደረጉ አምስቱ ክልሎች ተቀባይነትን /Internal Legitimacy/ ለማግኘት።

ለ. የወያኔን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የበላይነትን የሚቃወም ሕብረ-ብሔራዊነቱ የተጠናከረና በአንድነት የሚቆም ማኅበረሰብ እንዳይፈጠር ለመከላከል። ለምሣሌ በተለያዩ ወቅቶች በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ፣ በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ ቢሆንም በአንዱ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ በሌላ ክልል የሚኖረው ህዝብ በአይመለከተኝም ስሜት ጉዳዩን እንዲያየው ተደርጓል፤ እየተደረገም ነው።

በሌላ በኩል ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ህዝብና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላይ እያሳደረ ያለው ተፅዕኖና እያስከተለ ያለው ችግር የሚከተለውን ይመስላል።

ሀ. ባለብዙ ብሔር በሆኑ ክልሎች ውስጥ በየጊዜው የሚያገረሽ ማንነትን መሰረት ያደረገ ግጭት መከሰት።

ለ. በነዚህ ባለብዙ ብሔር ክልሎች ውስጥ የተፈጥሮ ሀብት ክፍፍልን፣ የድንበር ወሰንን እንዲሁም በክልልና በወረዳ ምክር ቤቶች ውስጥ በሚኖር የውክልና ጥያቄን መሰረት ያደረገ ውጥረት እና ግጭት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል።

ሐ. ዜጎች በሀገሪቱ በየትኛውም ክልል ተንቀሳቅሰው የመሥራት፣ የመኖርና ሀብት የማፍራት መብታቸው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንዲገታ ተደርጓል።

መ. ዜጎች በችሎታቸው ሳይሆን በብሔር ማንነታቸው በመመዘናቸው፤ የሀገሪቱ ቢሮክራሲ የተንዛዛና መልካም አስተዳደር የጎደለው እንዲሁም ለከፍተኛ ሙስናና ምዝበራ የተጋለጠ እንዲሆን አድርጓል።

ሠ. ሀገራዊ ራዕይ ያላቸውና የወያኔን መንግሥት መገዳደር የሚችሉ ሕብረ ብሔራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይፈጠሩ፤ ይልቁንም ብሔር ተኮር የሆኑ ድንክ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ አሸን እንዲፈሉ በማድረጉ፤ ወያኔን በሠላማዊ የፖለቲካ ትግል ማስወገድ እንዳይቻል አድርጓል።

ረ. ወያኔ ሆን ብሎ በሚያሰረጨው ታሪካዊ-ቅሰጣ /Historical Revisionism/ መሰረት በተለያዩ ክልሎች መካከል ከፍተኛ የሚባል ጥላቻ እንዲነግሥ ከማድረጉ ባሻገር፤ ነገን በደም እንዲፈላለጉ እያደረገ ይገኛል።

በአጠቃላይ ይህ የጎሣ ፌደራሊዝም ወያኔ እንደሚለው በሀገሪቱ ደም መፋሰስን የሚያስቆም ሳይሆን፤ ይልቁን እንደ ባልከን ሀገሮች ከፍተኛ ለሚባል ደም መፋሰስና መበታተን የሚዳርግ ትልቅ አደጋን ያዘለ ነው። በመሆኑም በዜጎች መካከል ግንዛቤን ከመፍጠር ጀምሮ በሀገራችንና በህዝባችን ላይ ያንዣበበውን አደጋ ከወዲሁ ለማስቀረት ወያኔን በጋራ ልናስወግደው ይገባል።

ተስፋዬ ገብረዮሐንስ (ከጀርመን)

tesfayejohn@hotmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule