• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፕሮፌሰር፣ ጄኔራል” ሳሞራ

December 17, 2015 09:16 am by Editor 1 Comment

ረቡዕ በተሰማው ዜና መሠረት የቻይናው ቲያንጂን የቴክኖሎጂና ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለሳሞራ የኑስ የክብር ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡

ሚያዚያ 1999 የዖጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግምባር በክልሉ በሚገኝ የነዳጅ ፍለጋ ቦታ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከ70 በላይ ንጹሃንን በገደለበት ወቅት ዘጠኝ ቻይናውያን ከሞቱት መካከል ነበሩ፡፡

በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር አዛዥነት በየጊዜው በዖጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሲቃወም የነበረው ኦብነግ ለወሰደው ድንገተኛ እርምጃ በሟቹ መለስ የሚመራው ህወሃት በክልሉ አምስት ቦታዎች ማለትም በፊቅ፣ ቆራሄ፣ ጎዴ፣ ዋርድሄር እና ደጋሃቡር ዘግናኝ የሆነ የመልሶ ማጥቃት ጭፍጨፋ በነዋሪው ሕዝብ ላይ አድርሷል፡፡

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ባወጣው ዘገባ መሠረት ኦብነግ ላደረሰው የአጸፋ መልስ እና ታጣቂዎችን ለመደምሰስ በሚል ህወሃት ያዘመተው ጦር በተደጋጋሚ በሰላማዊው ሕዝብ ላይ ፍጹም ጨካኝና ዘግናኝ ዕልቂት ፈጽሟል፡፡

samorayየመልሶ ማጥቃቱን ዘመቻ ለማካሄድ ጂጂጋ ላይ የክልሉ የደኅንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ባደረጉበት ወቅት የመለስ የጸጥታ አማካሪ አባይ ጸሃዬ እና ሳሞራ የኑስ በጥቃቱ ዕቅድ አወጣጥ ላይ ተገኝተው እንደነበር ታማኝ ምንጮቹን ጠቅሶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ያስረዳል፡፡

ከዚያም በ1999 ሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ አቶ መለስ መጠነ ሰፊ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ እንዲካሄድ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ የዖጋዴን ሕዝብ ፍዳውን በላ፤ እንደ ቅጠል ረገፈ፤ ዕድሜያቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጃገረዶች፣ ሴቶች አዛውንቶችንም ጨምሮ ተደፈሩ፡፡ ህጻናት ወንዶችም ሳይቀሩ የዚህ ሰለባ ሆነዋል፡፡

የቀድሞው የቻይና መሪ ማዖ ሴቱንግ ሽምቅ ተዋጊዎችን ስለማጥፋት የተናገሩት ቃል በመለስ ፊት አውራሪነት ተፈጸመ፡፡ “ዓሣ በባህር እንደሚዋኝ ሽምቅ ተዋጊም በሕዝቡ መካከል መንቀሳቀስ አለበት፤ (ሽምቅ ተዋጊን ለማጥፋት ካስፈለገ ዓሣው ያለበትን ባህር ማድረቅ ነው)” ያሉት የማዖ ቃል በመለስ ትዕዛዝ በሳሞራ የኑስና ሌሎች የህወሃት አጋፋሪዎች ተፈጸመ፡፡

ውለታ የማይረሱት ቻይናውያን የትምህርት ደረጃው በውል የማይታወቀውን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አሉ ከሚባሉት የጦር አካዳሚዎች ሥልጠና ስለመውሰዱ ምንም ማስረጃ ላልተገኘለት “ቻይናዊ ጄኔራል ደምመላሽ” ባቋራጭ “የላቀ ምሁርነት” አጎናጸፉት፡፡

ውለታን መመለስ ከሆነ አይቀር እንዲህ ነው፡፡

ማዖ ነኝ ከቲያንጂን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ffinilla says

    December 21, 2015 07:55 am at 7:55 am

    It is unfair; however, it is totally unjust an insult on human beings. This man known for his brutality and illiterate a person never deserves such accolade at all. Well, Chinese goods are this days cheap any wealthy blood robber like Samura can afford goods from Chinese diploma mill.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule