• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዘመድነህ ንጋቱ የኩባንያው ሳይሆን የህወሃት አገልጋይ ናቸው”

October 24, 2015 03:33 am by Editor 2 Comments

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ስም የኧርነስትና ያንግ የተሰኘውን የንግድ ሒሳብና ኦዲት ሥራ የሚያከናውን ኩባንያ ከፍተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ዘመድነህ ንጋቱ በኦባንግ ሜቶ ለዓምአቀፉ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች አቤቱታ ቀረበባቸው፡፡

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለዓለምአቀፉ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ ዋና የሥራ ኃላፊዎች ማርክ ዋይንበርገር እና ሮጀር ደንባር ጥቅምት 9፤2008 ዓም (October 20, 2015) በጻፉት ደብዳቤ የኩባንያው ሸሪክ አስተዳዳሪ አቶ ዘመድነህ ንጋቱ ኩባንያው ከቆመለት ዓላማ ውጪ በመንቀሳቀስ ከህወሃት ጋር በማበር ከሙያው ሥነምግባር ያፈነገጠ አካሄድ በመሄድ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየበደሉ መሆናቸውን አውስተዋል፡፡

“ላለፉት 14 ዓመታት” ይላል ደብዳቤው “በገሃድ ከሚታየው እውነታ በራቀ መልኩ አቶ ዘመድነህ ሚዛኑን ያልጠበቀና የሃሰት መረጃ በማቅረብ በኢትዮጵያ ውስጥ ጥሩ የኢንቨስትመንት ሁኔታ እንዳለ ሲሰብኩ ቆይተዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የፖለቲካና የገበያ አደጋ ዝቅ አድርጎ እንዲታይ አድርገዋል ብለን እናምናለን፡፡ ስለሆነም አቶ ዘመድነህ የዓለምአቀፉን ኩባንያ የሥነምግባር መመሪያ በመጣስ የድርጅቱን ስም በማጉደፍ ኩባንያውንና የኩባንያውን ደምበኞች ፍላጎት አደጋ ላይ ጥለዋል ብለን እናምናለን” ብሏል፡፡

ደብዳቤው ሲቀጥልም አቶ ዘመድነህ ህወሃት የሚገዛትን ኢትዮጵያ በመወከል በተለያዩ መድረኮች በመገኘት በኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስትመንት እንዲካሄድ የሚያደርጉትን ቅስቀሳ ወቅሷል፡፡ እጅግ በርካታ የሆኑ ህወሃት በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ የተቆጣጠራቸውን ኩባንያዎች በመወከል እንዲሁም በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ በመቀስቀስ አቶ ዘመድነህ የሚያደርጉት ተግባር ከኩባንያው የሥነምግባር አሠራር ጋር የሚጋጭና ኩባንያውንም አደጋ ላይ የሚጥል ብቻ ሳይሆን ሕገወጥ አሠራርም መሆኑን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ ለበላይ ኃላፊዎቹ አስረድተዋል፡፡

በተለያዩ ዓምአቀፋዊ የሙስና መለኪያዎች መሠረት በኢትዮጵያ የሚገኘው የሙስና አሠራር አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ያለ መሆኑ እየታወቀ እንደ ባለሙያ ይህንን እውነታ በማሳየት ኢንቨስት የሚያደርጉ ሁሉ ጥንቃቄ እንዲወስዱ ከመምከር ይልቅ ዘመድነህ ንጋቱ ህወሃት በሚገዛት ኢትዮጵያ ሁሉም ነገር ለኢንቨስትመንት የተመቻቸ መሆኑን በየመድረኩ መስበካቸው ከሥርዓቱ ጋር የተቆራኙ ከመሆናቸው ጋር የተያያዘ ለመሆኑ ደብዳቤው ማስረጃዎችን ጠቅሷል፡፡ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ ከመመሥረቱ አንስቶ ቢሮውን በአዲስ አበባ ቦሌ መንገድ ላይ በሚገኘው ሜጋ ሕንጻ ላይ ማድረጉ ከህወሃት ጋር ያለውን ትስስር ገና ከጅምሩ ያደረገ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡

በመሆኑም ደብዳቤው ለዓለምአቀፉ የበላይ ኃላፊዎች የሚከተሉትን ጥያቄዎች አቅርቧል፡-

  • To conduct a thorough assessment/investigation of these concerns in regards to Mr. Zemedeneh Negatu and EY’s East Africa Managing Office, currently under his leadership
  • To appoint an independent body to examine East African Managing Partner’s books and Mr. Negatu’s business activities on the ground in Ethiopia, in the Middle East, Asia and in the US
  • To also require a disclosure of his associations with all the ruling party-owned and regime-affiliated corporations on the ground in Ethiopia, as well as in the US, Europe, Middle East, Asia and other locations.
  • To require that Mr. Negatu and/or his emissaries cease from promoting all FDI in Ethiopia where such promotion favors or is in collusion with the ruling party-owned and affiliated corporations, although few other options exist.
  • To stop Mr. Negatu from using EY’s brand in association with his role as a representative of the Ethiopian government’s foreign investment promotion effort; in particular, where it is used to mislead investors to the reality of the economy. The Video presentation at the Turkey-Ethiopia Business Forum on 27 April 2015, in Istanbul, Turkey is the latest example.
  • To require that Mr. Negatu disclose his personal business activities and his association with Fairfax Africa Fund LLC, established in McLean, Virginia and led by the former EY East Africa Managing Partner employee in Addis Ababa, Yared Berhane, regarding the investment of millions of dollars in Ethiopia and East African countries.
  • According to the news, the latest investment offer of Fairfax Africa Fund was the Ethiopian Crown Cork & Can Manufacturing Industry S.C. (ECCCMI), from the government’s Privatization & Public Enterprise Supervising Agency. David Johns, Director of Fairfax is a newly hired US national who may be a front to make it appear that the fund is an American investment, when in actuality; it is believed to be a ruling party-affiliated business. The website, All Africa, reported that Mr. Negatu was the principle representative of the fund in the purchases of ECCCMI. Interestingly, he was invited to speak at the Fairfax Africa Fund’s organized event: “Collaborative Investing by the Ethiopian Diaspora in the U.S” on at least two occasions in California in February of 2012.

በተለይ በመጨረሻው ላይ ዘመድነህ ንጋቱ እና በአሜሪካ አገር በቨርጂኒያ ጠቅላይ ግዛት የሚገኘው Fairfax Africa Fund LLC የተባለው ድርጅት ያላቸው ግንኙነት እንዲመረመር የተጠየቀው የአቶ ዘመድነህን ከህወሃት ጋር ያላቸውን ድብቅ ግንኙነት የሚያጋልጥ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ Fairfax Africa Fund LLC ዴቪድ ጆንስ የተባለ አሜሪካዊ የሚመራው ድርጅት ሆኖ ለይስሙላ በግምባር የተቀመጠ ቢሆንም ድርጅቱን ከኋላ የሚመራው የቀድሞ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያው ሠራተኛ የሆነው ያሬድ ብርሃኔ መሆኑ አቶ ዘመድነህ ከህወሃት ጋር የተጠላለፈ ንግድ የሚፈጽሙ የሥርዓቱ ደጋፊ መሆናቸውን ያጎላ ሆኗል፡፡ ያሬድ ብርሃኔ የሚመራው የውጭ ኩባንያ ተብሎ የተሰጠቀሰው ድርጅት የፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ለሽያጭ የሚያቀርባቸውን ድርጅቶች እያመቻቸ እና እያስማማ የሚያሸጥ የህወሃት ውክልና ያለው እንደሆነ ተግባሩ እንደሚመሰክር ከደብዳቤው ላይ የተገኘው መረጃ አስረድቷል፡፡ በመሆኑም ይህንን መሰል አሠራር ውስጥ የሚገኙት ዘመድነህ ንጋቱ በአለቆቻቸው እንዲጠየቁና ሕገወጥ ከሆነው እና በግፍ ኢትዮጵያን እየገዛ ካለው ሥርዓት ጋር ያላቸው ግንኙነት እንዲመረመር አቶ ኦባንግ በደብዳቤያቸው ጠይቀዋል፡፡

ይህ ደብዳቤ ለዓለምአቀፉ ድርጅት የሥራ አመራሮች መድረሱን በተመለከተ ጎልጉል መረጃ የደረሰው ሲሆን ጉዳዩ በይፋ የወጣና ለዓለምአቀፍ ሚዲያዎች ላይ እንዲያውቁት የተላከ በመሆኑ የኩባንያው አመራሮች ይፋዊ ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አቶ ኦባንግ የጻፉት ደብዳቤ ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡-


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. yeshambel says

    November 10, 2015 10:14 am at 10:14 am

    Dear
    Zemedenh is one of the the best influential man not in Ethiopia but also in Africa. I can not agree by your worthless comments and suggestions. This man has left up the name and image of Ethiopia. He might have good relations with the government. Those leaders and VIP people in America do they work with opposition partyllike you who is out side the country.
    I am not the supporter of EPRDF but you can not complain every man does not agree with you.
    Please encourage those who work for Ethiopia.
    I did not agree with your worthless complaints.

    Reply
  2. Solomon Dagnachew says

    November 19, 2015 10:16 am at 10:16 am

    Why didn’t the person in question come out and challenge? his silence speaks louder. There are many other under the blanket of ‘Investor’ robbed our people in collaboration of TPLF’s nexus-of-evils and bled our country dry.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule