• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን (አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን)”

February 24, 2015 05:28 am by Editor Leave a Comment

በተለያየ ጊዜ በተለያየ የክህደት አስተምህሮ በመሰናከል በመውደቅ ከዚህች ሐዋርያዊት አንዲት ቤተክርስቲያ እየተለዩ በኑፋቄያዊ አስተምህሮ ጸንተው በመቀጠል ለዚህች አንዲት ሃይማኖት አንዲት ቤተክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ዲያብሎስን የሚያገለግሉ ከ40 ሽህ በላይ ይቆጠራሉ፡፡ ሃይማኖት ነንም ይላሉ፡፡ ክርስቶስ በወንጌሉ ሐዋርያትም በመልእክቶቻቸው እንደተናገሩት ግን ከአንዲቷ በስተቀር ይሄ ሁሉ ሃይማኖት ነኝ ባይ ዝግንትል ሐሰተኛና ዲያብሎሳዊ የክህደትና የጥፋት መንገዶች ናቸው፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ ሲቃረብ ብዙዎች ሐሰተኞች መምህራን በየ እልፍኙ የሚሰብኩላቸው ሐሰተኞች ኢየሱሶች ሐሰተኞች ክርስቶሶች ይመጡ ዘንድ እንዳላቸውና ከእነሱም እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡ ማቴ. 24፤1-28 “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 “መንፈስ ግን በግልጥ በኋለኞቹ ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንት ትምህርት እያዳመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ” ብሏል 1ኛ ጢሞ. 4፤1-2 “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ በእርሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳቹህም ዕረፍትን ታገኛላቹህ እነሱ ግን አንሄድባትም አሉ” ኤር. 6፤16 “የመጀመሪያዋን እምነት እስከመጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና” ዕብ. 3፤14 “ነገር ግን ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራቹህትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና መሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንዳትመለከቱ እለምናቹሀለሁ፡፡ ከእነሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ እንደነዚህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ያታልላሉ” ሮሜ 16፤15-23 “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯቹህን ዋኖቻቹህን አስቡ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹህ በእምነት ምሰሏቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘለዓለምም ያው ነው ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፡፡ ልባቹህ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና ” ዕብ. 13፤7-9  “በጠበበው ደጅ ግቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይዎት የሚወስደው ደጁ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው” ማቴ. 7፤13-14

ቤተክርስቲያን ካቶሊካዊያኑ በክህደት ውስጥ እንዳሉና ሰሐትያን እንደሆኑ አረጋግጣ አውግዛ የለየቻቸው ገና ከመለየታቸው 451ዓ.ም. ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ካቶሊካዊያኑ ለኢትዮጵያዊው ካቶሊካዊ መነኩሴ ብርሃነ ኢየሱስ በቅርቡ በየካቲት 7 2007ዓ.ም. የካርዲናልነት ማዕረግ ሰጥተዋል፡፡ ይንን ሹመት ተከትሎ አቦይ ማትያስ (የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ነኝ ባይ) የእንኳን ደስ አለዎት የደስታ መግለጫ መልእክትን በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም  “…አሁን የተሰጥዎት ከፍተኛ ሐዋርያዊ ሥልጣን በቤተክርስቲያን ለፈጸሙት የረጅም ዘመን አገልግሎት ሁነኛ ማረጋገጫ ነው” በማለት አስተላልፈዋል፡፡

እንግዲህ ይታያቹህ! አቦይ ማትያስ ይሄንን የሚሉት በካቶሊካዊያኑ ክፉኛ የተደቆሰችን የተሰበረችን መራራና አረማዊ ግፍ የተፈጸመባትን ቤተክርስቲያን እመራለሁ እኔም የዚህች ቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና አማኝ ተከታይ ነኝ እያሉና በካቶሊካዊያኑ ላይ ያስተላለፈችውን ግዝት በመተላለፍ ነው ይሄንን እያሉ ያሉት፡፡ ካቶሊካዊያኑ በዚህች ሀገርና ሕዝብ ቁሳዊ መንፈሳዊ ጥበባዊ ሥልጣኔና ሰብአዊ ሀብቶቿ ላይ እስከዛሬ ያልተጠገነ ወደፊትም የማይጠገን ከባድ ስብራትና ኪሳራ ያደረሱ ከንቀታቸው የተነሣም ለዚህ አረመኔያዊ ድርጊታቸውም እስከዛሬ ድረስ ተገቢውን ይቅርታ እንኳን ለመጠየቅ ያልቻሉና ያልፈለጉ መሆናቸውን እያወቁ ነው እንግዲህ አቦይ ማትያስ ይሄንን ያደረጉት፡፡ እንደቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ አስተምህሮ ቀኖናና ሥርዓት አቦይ ማትያስ በግልም ይሁን በቤተክርስቲያን ስም እንዲህ ዓይነት ቃል ከቤተክርስቲያን ለተለዩ ወገኖች ማስተላለፍ አይችሉም የተከለከለና የተወገዘ ነው፡፡ አድርጎት ለተገኘም በግዝት የታሰረና የኑፋቄ የክህደት ተባባሪ በመሆኑ ተወግዞ እስከመለየት የሚያደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እዚህ ላይ አቦይ ማትያስን ልጠይቃቸው የምፈልገው ጉዳይ ቢኖር፡- አቦይ ማትያስ ሆይ! የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ምእመናን ከዚህ ንግግርዎ ምን እንዲረዳ ምን እንዲማር ነው ምን እንዲወስድ ነው የሚፈልጉት? እርስዎ እንዳሉት ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያ መሆናቸውንና ካቶሊካዊያኑም ሐዋርያዊ መሆናቸውን ነው? እናም እነሱን ተከተሉ ነው እያሉን ያሉት? ምእመናን በረታችንን ጥለን እንድንወጣና ወደ ተኩላት በረት ጥርግ ብለን እንድንገባ ነው? አየ አቦይ ማትያስ! ለካም ወያኔ ብቻ አይደሉም ካቶሊካዊ ተኩላም ነዎትና! ባለ ሁለት አፍ የጥፋት ሰይፍ ሆነው ነዋ የቤተክርስቲያንን አንገት ለመቁረጥ ተስለው የገቡት?

ቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ካላት ሕግና ሥርዓቷን ከማስጠበቅ መንጋዋን ከመጠበቅ አንጻር በዚህ በተፈጸመባት ክህደት የሚጠበቅበትን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule