• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን (አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን)”

February 24, 2015 05:28 am by Editor Leave a Comment

በተለያየ ጊዜ በተለያየ የክህደት አስተምህሮ በመሰናከል በመውደቅ ከዚህች ሐዋርያዊት አንዲት ቤተክርስቲያ እየተለዩ በኑፋቄያዊ አስተምህሮ ጸንተው በመቀጠል ለዚህች አንዲት ሃይማኖት አንዲት ቤተክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ዲያብሎስን የሚያገለግሉ ከ40 ሽህ በላይ ይቆጠራሉ፡፡ ሃይማኖት ነንም ይላሉ፡፡ ክርስቶስ በወንጌሉ ሐዋርያትም በመልእክቶቻቸው እንደተናገሩት ግን ከአንዲቷ በስተቀር ይሄ ሁሉ ሃይማኖት ነኝ ባይ ዝግንትል ሐሰተኛና ዲያብሎሳዊ የክህደትና የጥፋት መንገዶች ናቸው፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ ሲቃረብ ብዙዎች ሐሰተኞች መምህራን በየ እልፍኙ የሚሰብኩላቸው ሐሰተኞች ኢየሱሶች ሐሰተኞች ክርስቶሶች ይመጡ ዘንድ እንዳላቸውና ከእነሱም እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡ ማቴ. 24፤1-28 “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 “መንፈስ ግን በግልጥ በኋለኞቹ ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንት ትምህርት እያዳመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ” ብሏል 1ኛ ጢሞ. 4፤1-2 “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ በእርሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳቹህም ዕረፍትን ታገኛላቹህ እነሱ ግን አንሄድባትም አሉ” ኤር. 6፤16 “የመጀመሪያዋን እምነት እስከመጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና” ዕብ. 3፤14 “ነገር ግን ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራቹህትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና መሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንዳትመለከቱ እለምናቹሀለሁ፡፡ ከእነሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ እንደነዚህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ያታልላሉ” ሮሜ 16፤15-23 “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯቹህን ዋኖቻቹህን አስቡ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹህ በእምነት ምሰሏቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘለዓለምም ያው ነው ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፡፡ ልባቹህ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና ” ዕብ. 13፤7-9  “በጠበበው ደጅ ግቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይዎት የሚወስደው ደጁ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው” ማቴ. 7፤13-14

ቤተክርስቲያን ካቶሊካዊያኑ በክህደት ውስጥ እንዳሉና ሰሐትያን እንደሆኑ አረጋግጣ አውግዛ የለየቻቸው ገና ከመለየታቸው 451ዓ.ም. ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ካቶሊካዊያኑ ለኢትዮጵያዊው ካቶሊካዊ መነኩሴ ብርሃነ ኢየሱስ በቅርቡ በየካቲት 7 2007ዓ.ም. የካርዲናልነት ማዕረግ ሰጥተዋል፡፡ ይንን ሹመት ተከትሎ አቦይ ማትያስ (የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ነኝ ባይ) የእንኳን ደስ አለዎት የደስታ መግለጫ መልእክትን በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም  “…አሁን የተሰጥዎት ከፍተኛ ሐዋርያዊ ሥልጣን በቤተክርስቲያን ለፈጸሙት የረጅም ዘመን አገልግሎት ሁነኛ ማረጋገጫ ነው” በማለት አስተላልፈዋል፡፡

እንግዲህ ይታያቹህ! አቦይ ማትያስ ይሄንን የሚሉት በካቶሊካዊያኑ ክፉኛ የተደቆሰችን የተሰበረችን መራራና አረማዊ ግፍ የተፈጸመባትን ቤተክርስቲያን እመራለሁ እኔም የዚህች ቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና አማኝ ተከታይ ነኝ እያሉና በካቶሊካዊያኑ ላይ ያስተላለፈችውን ግዝት በመተላለፍ ነው ይሄንን እያሉ ያሉት፡፡ ካቶሊካዊያኑ በዚህች ሀገርና ሕዝብ ቁሳዊ መንፈሳዊ ጥበባዊ ሥልጣኔና ሰብአዊ ሀብቶቿ ላይ እስከዛሬ ያልተጠገነ ወደፊትም የማይጠገን ከባድ ስብራትና ኪሳራ ያደረሱ ከንቀታቸው የተነሣም ለዚህ አረመኔያዊ ድርጊታቸውም እስከዛሬ ድረስ ተገቢውን ይቅርታ እንኳን ለመጠየቅ ያልቻሉና ያልፈለጉ መሆናቸውን እያወቁ ነው እንግዲህ አቦይ ማትያስ ይሄንን ያደረጉት፡፡ እንደቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ አስተምህሮ ቀኖናና ሥርዓት አቦይ ማትያስ በግልም ይሁን በቤተክርስቲያን ስም እንዲህ ዓይነት ቃል ከቤተክርስቲያን ለተለዩ ወገኖች ማስተላለፍ አይችሉም የተከለከለና የተወገዘ ነው፡፡ አድርጎት ለተገኘም በግዝት የታሰረና የኑፋቄ የክህደት ተባባሪ በመሆኑ ተወግዞ እስከመለየት የሚያደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እዚህ ላይ አቦይ ማትያስን ልጠይቃቸው የምፈልገው ጉዳይ ቢኖር፡- አቦይ ማትያስ ሆይ! የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ምእመናን ከዚህ ንግግርዎ ምን እንዲረዳ ምን እንዲማር ነው ምን እንዲወስድ ነው የሚፈልጉት? እርስዎ እንዳሉት ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያ መሆናቸውንና ካቶሊካዊያኑም ሐዋርያዊ መሆናቸውን ነው? እናም እነሱን ተከተሉ ነው እያሉን ያሉት? ምእመናን በረታችንን ጥለን እንድንወጣና ወደ ተኩላት በረት ጥርግ ብለን እንድንገባ ነው? አየ አቦይ ማትያስ! ለካም ወያኔ ብቻ አይደሉም ካቶሊካዊ ተኩላም ነዎትና! ባለ ሁለት አፍ የጥፋት ሰይፍ ሆነው ነዋ የቤተክርስቲያንን አንገት ለመቁረጥ ተስለው የገቡት?

ቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ካላት ሕግና ሥርዓቷን ከማስጠበቅ መንጋዋን ከመጠበቅ አንጻር በዚህ በተፈጸመባት ክህደት የሚጠበቅበትን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule