• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን (አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን)”

February 24, 2015 05:28 am by Editor Leave a Comment

በተለያየ ጊዜ በተለያየ የክህደት አስተምህሮ በመሰናከል በመውደቅ ከዚህች ሐዋርያዊት አንዲት ቤተክርስቲያ እየተለዩ በኑፋቄያዊ አስተምህሮ ጸንተው በመቀጠል ለዚህች አንዲት ሃይማኖት አንዲት ቤተክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ዲያብሎስን የሚያገለግሉ ከ40 ሽህ በላይ ይቆጠራሉ፡፡ ሃይማኖት ነንም ይላሉ፡፡ ክርስቶስ በወንጌሉ ሐዋርያትም በመልእክቶቻቸው እንደተናገሩት ግን ከአንዲቷ በስተቀር ይሄ ሁሉ ሃይማኖት ነኝ ባይ ዝግንትል ሐሰተኛና ዲያብሎሳዊ የክህደትና የጥፋት መንገዶች ናቸው፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ ሲቃረብ ብዙዎች ሐሰተኞች መምህራን በየ እልፍኙ የሚሰብኩላቸው ሐሰተኞች ኢየሱሶች ሐሰተኞች ክርስቶሶች ይመጡ ዘንድ እንዳላቸውና ከእነሱም እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡ ማቴ. 24፤1-28 “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 “መንፈስ ግን በግልጥ በኋለኞቹ ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንት ትምህርት እያዳመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ” ብሏል 1ኛ ጢሞ. 4፤1-2 “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ በእርሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳቹህም ዕረፍትን ታገኛላቹህ እነሱ ግን አንሄድባትም አሉ” ኤር. 6፤16 “የመጀመሪያዋን እምነት እስከመጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና” ዕብ. 3፤14 “ነገር ግን ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራቹህትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና መሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንዳትመለከቱ እለምናቹሀለሁ፡፡ ከእነሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ እንደነዚህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ያታልላሉ” ሮሜ 16፤15-23 “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯቹህን ዋኖቻቹህን አስቡ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹህ በእምነት ምሰሏቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘለዓለምም ያው ነው ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፡፡ ልባቹህ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና ” ዕብ. 13፤7-9  “በጠበበው ደጅ ግቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይዎት የሚወስደው ደጁ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው” ማቴ. 7፤13-14

ቤተክርስቲያን ካቶሊካዊያኑ በክህደት ውስጥ እንዳሉና ሰሐትያን እንደሆኑ አረጋግጣ አውግዛ የለየቻቸው ገና ከመለየታቸው 451ዓ.ም. ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ካቶሊካዊያኑ ለኢትዮጵያዊው ካቶሊካዊ መነኩሴ ብርሃነ ኢየሱስ በቅርቡ በየካቲት 7 2007ዓ.ም. የካርዲናልነት ማዕረግ ሰጥተዋል፡፡ ይንን ሹመት ተከትሎ አቦይ ማትያስ (የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ነኝ ባይ) የእንኳን ደስ አለዎት የደስታ መግለጫ መልእክትን በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም  “…አሁን የተሰጥዎት ከፍተኛ ሐዋርያዊ ሥልጣን በቤተክርስቲያን ለፈጸሙት የረጅም ዘመን አገልግሎት ሁነኛ ማረጋገጫ ነው” በማለት አስተላልፈዋል፡፡

እንግዲህ ይታያቹህ! አቦይ ማትያስ ይሄንን የሚሉት በካቶሊካዊያኑ ክፉኛ የተደቆሰችን የተሰበረችን መራራና አረማዊ ግፍ የተፈጸመባትን ቤተክርስቲያን እመራለሁ እኔም የዚህች ቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና አማኝ ተከታይ ነኝ እያሉና በካቶሊካዊያኑ ላይ ያስተላለፈችውን ግዝት በመተላለፍ ነው ይሄንን እያሉ ያሉት፡፡ ካቶሊካዊያኑ በዚህች ሀገርና ሕዝብ ቁሳዊ መንፈሳዊ ጥበባዊ ሥልጣኔና ሰብአዊ ሀብቶቿ ላይ እስከዛሬ ያልተጠገነ ወደፊትም የማይጠገን ከባድ ስብራትና ኪሳራ ያደረሱ ከንቀታቸው የተነሣም ለዚህ አረመኔያዊ ድርጊታቸውም እስከዛሬ ድረስ ተገቢውን ይቅርታ እንኳን ለመጠየቅ ያልቻሉና ያልፈለጉ መሆናቸውን እያወቁ ነው እንግዲህ አቦይ ማትያስ ይሄንን ያደረጉት፡፡ እንደቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ አስተምህሮ ቀኖናና ሥርዓት አቦይ ማትያስ በግልም ይሁን በቤተክርስቲያን ስም እንዲህ ዓይነት ቃል ከቤተክርስቲያን ለተለዩ ወገኖች ማስተላለፍ አይችሉም የተከለከለና የተወገዘ ነው፡፡ አድርጎት ለተገኘም በግዝት የታሰረና የኑፋቄ የክህደት ተባባሪ በመሆኑ ተወግዞ እስከመለየት የሚያደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እዚህ ላይ አቦይ ማትያስን ልጠይቃቸው የምፈልገው ጉዳይ ቢኖር፡- አቦይ ማትያስ ሆይ! የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ምእመናን ከዚህ ንግግርዎ ምን እንዲረዳ ምን እንዲማር ነው ምን እንዲወስድ ነው የሚፈልጉት? እርስዎ እንዳሉት ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያ መሆናቸውንና ካቶሊካዊያኑም ሐዋርያዊ መሆናቸውን ነው? እናም እነሱን ተከተሉ ነው እያሉን ያሉት? ምእመናን በረታችንን ጥለን እንድንወጣና ወደ ተኩላት በረት ጥርግ ብለን እንድንገባ ነው? አየ አቦይ ማትያስ! ለካም ወያኔ ብቻ አይደሉም ካቶሊካዊ ተኩላም ነዎትና! ባለ ሁለት አፍ የጥፋት ሰይፍ ሆነው ነዋ የቤተክርስቲያንን አንገት ለመቁረጥ ተስለው የገቡት?

ቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ካላት ሕግና ሥርዓቷን ከማስጠበቅ መንጋዋን ከመጠበቅ አንጻር በዚህ በተፈጸመባት ክህደት የሚጠበቅበትን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule