• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ 97ና ትውስታዬ

May 21, 2014 12:09 am by Editor Leave a Comment

የምርጫ ነገር ሲታሰብ ሲነሣ በሁላችንም ልቡና የሚታሰበን ከፊታችን ድንቅ የሚልብን ምርጫ 97ዓ.ም. ነው፡፡ በምርጫ 97ቱ ወቅት መቸም የማይረሱን ጉልህ ጉልህ ጉዳዮች አሉ፡- ያ ምርጫ የወያኔ “ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲ አላደለንም” የሚለው የምጸት ጸሎቱ ተሰምቶለት ተአምር ሊባል በሚችል መልኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወያኔ የመቋቋም አቅም በላይ መልስ ያገኘበት፣ በዓለም ውስጥ ከታዩት ጥቂት ታላላቅ የሕዝብ ማዕበል ከታየባቸው ሰላማዊ ሰልፎች አንዱ የተደረገበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በላቀ መልኩ (ይሄንን ስል በድፍረት ነው) ያለውን የበሰለ ፖለቲካዊ (እምነተ-አሥተዳደራዊ) አስተሳሰብና አስደናቂ ሥነ-ሥርዓት (ዲሲፒሊን) ያሳየበት፣ የወያኔን ሲጀመር ጀምሮ ይዞት የነበረውን የውሸት የማስመሰል ዲሞክራሲ (በይነ ሕዝብ) ካባ አስወልቆ እርቃሉን በማስቀረት ትክክለኛ አንባገነናዊ ማንነቱት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያጋለጠበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ያለውን ጠንካራ አንድነት ያሳየበት፣ ተጨባጭ የኢትዮጵያ ተስፋ ለአፍታም ቢሆን የታየበት፣ በሕዝቡ ልቡና ውስጥ ሀገርን ከወደቀችበት ለማንሣት ያለውን የጋለ የተነቃቃ ስሜትና ቁርጠኛ ፍላጎት ያየንበት፣ ወዲያው ተመትቶ ወደቀ እንጅ የንባብ ባሕል የተቀጣጠለበት (እናቶች ሳይቀሩ ጋዜጣ ገዝተው “እባካቹህ አንብቡልኝ?” እስከማሰኘት የደረሰ)፣ ከረጅም ጊዜ ጨፍጋጋና ኃዘን የተሞላ ገጽታ በኋላ በሕዝቡ ገጽታ ላይ ተስፋን የሰነቀ የሞቀ ስሜትና ፈገግታ ደምቆ የታየበት ወዘተ.

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እኔ ደግሞ በግሌ አንድ ልዩ ትዝታ አለኝ በዚያ አይረሴ የምርጫ ሂደት ውስጥ ጎልቶ ይታይ የነበረው በየ የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳና የክርክር መድረኮች ላይ ይገለጽ የነበረው የየፓርቲው መሪ ቃል (slogan) ነበር፡፡ ከእነዚህ መሪ ቃሎች ውስጥ የቅንጅትና የኢሕአዴግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በዓለም አቀፍ የብዙኃን መገናኛዎች ሳይቀር ልዩነታቸውን በማንሣትም ጭምር ተደጋጋሚ ሽፋን ተሰጥቶት ነበር፡፡ እነዚህ መሪ ቃሎች የየፓርቲውን የብስለት፣ የአስተሳሰብ፣ የንቃተ ሕሊና ልዩነቶች አጉልተው ያሳዩ ነበሩ፡፡ የቅንጅትንና የኢሕአዴግን ብናይ የነበራቸው ልዩነት የኋላ ቀርና የዘመናዊ (የአናሎግና የዲጂታል) የዛሬና የነገ፣ የገጠርና የከተማ ያልሠለጠነና የሠለጠነ ያህል ዓይነት ነበር፡፡ የኢሕአዴግ የምርጫ ቅስቀሳ መሪቃል “ ንብን ይምረጡ! ንብ ታታሪ ሠራተኛ ናት፤ ንብ ማር ትሰጣለች ንብን ይምረጡ!” የሚል ነበር የቅንጅት ደግሞ “ ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ የመከራ የችጋር የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው ” የሚል ነበር፡፡ ይሄንን በሚገባ የተረዳው የኢትዮጵያ ሕዝብም በምርጫ ካርዱ ንቃቱን፣ ብስለቱን፣ ፍላጎቱን፣ ምኞቱን፣ ማንነቱን፣ አቋሙን ባረጋገጠ መልኩ ተናገረ ጮኸ አሰማ አስደመጠ፡፡ በሚያሳዝን መልኩ ወያኔም ይሁን የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በእሱ የንቃተ ሕሊናና የብስለት ደረጃ ያሉ ስላልነበሩ ምላሻቸው የሚያሳዝን ሆነ፡፡

“ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ፣ የመከራ፣ የችጋር፣ የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው” ይህ መሪ ቃል የእኔ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule