• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ 97ና ትውስታዬ

May 21, 2014 12:09 am by Editor Leave a Comment

የምርጫ ነገር ሲታሰብ ሲነሣ በሁላችንም ልቡና የሚታሰበን ከፊታችን ድንቅ የሚልብን ምርጫ 97ዓ.ም. ነው፡፡ በምርጫ 97ቱ ወቅት መቸም የማይረሱን ጉልህ ጉልህ ጉዳዮች አሉ፡- ያ ምርጫ የወያኔ “ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲ አላደለንም” የሚለው የምጸት ጸሎቱ ተሰምቶለት ተአምር ሊባል በሚችል መልኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወያኔ የመቋቋም አቅም በላይ መልስ ያገኘበት፣ በዓለም ውስጥ ከታዩት ጥቂት ታላላቅ የሕዝብ ማዕበል ከታየባቸው ሰላማዊ ሰልፎች አንዱ የተደረገበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በላቀ መልኩ (ይሄንን ስል በድፍረት ነው) ያለውን የበሰለ ፖለቲካዊ (እምነተ-አሥተዳደራዊ) አስተሳሰብና አስደናቂ ሥነ-ሥርዓት (ዲሲፒሊን) ያሳየበት፣ የወያኔን ሲጀመር ጀምሮ ይዞት የነበረውን የውሸት የማስመሰል ዲሞክራሲ (በይነ ሕዝብ) ካባ አስወልቆ እርቃሉን በማስቀረት ትክክለኛ አንባገነናዊ ማንነቱት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያጋለጠበት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ያለውን ጠንካራ አንድነት ያሳየበት፣ ተጨባጭ የኢትዮጵያ ተስፋ ለአፍታም ቢሆን የታየበት፣ በሕዝቡ ልቡና ውስጥ ሀገርን ከወደቀችበት ለማንሣት ያለውን የጋለ የተነቃቃ ስሜትና ቁርጠኛ ፍላጎት ያየንበት፣ ወዲያው ተመትቶ ወደቀ እንጅ የንባብ ባሕል የተቀጣጠለበት (እናቶች ሳይቀሩ ጋዜጣ ገዝተው “እባካቹህ አንብቡልኝ?” እስከማሰኘት የደረሰ)፣ ከረጅም ጊዜ ጨፍጋጋና ኃዘን የተሞላ ገጽታ በኋላ በሕዝቡ ገጽታ ላይ ተስፋን የሰነቀ የሞቀ ስሜትና ፈገግታ ደምቆ የታየበት ወዘተ.

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እኔ ደግሞ በግሌ አንድ ልዩ ትዝታ አለኝ በዚያ አይረሴ የምርጫ ሂደት ውስጥ ጎልቶ ይታይ የነበረው በየ የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳና የክርክር መድረኮች ላይ ይገለጽ የነበረው የየፓርቲው መሪ ቃል (slogan) ነበር፡፡ ከእነዚህ መሪ ቃሎች ውስጥ የቅንጅትና የኢሕአዴግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በዓለም አቀፍ የብዙኃን መገናኛዎች ሳይቀር ልዩነታቸውን በማንሣትም ጭምር ተደጋጋሚ ሽፋን ተሰጥቶት ነበር፡፡ እነዚህ መሪ ቃሎች የየፓርቲውን የብስለት፣ የአስተሳሰብ፣ የንቃተ ሕሊና ልዩነቶች አጉልተው ያሳዩ ነበሩ፡፡ የቅንጅትንና የኢሕአዴግን ብናይ የነበራቸው ልዩነት የኋላ ቀርና የዘመናዊ (የአናሎግና የዲጂታል) የዛሬና የነገ፣ የገጠርና የከተማ ያልሠለጠነና የሠለጠነ ያህል ዓይነት ነበር፡፡ የኢሕአዴግ የምርጫ ቅስቀሳ መሪቃል “ ንብን ይምረጡ! ንብ ታታሪ ሠራተኛ ናት፤ ንብ ማር ትሰጣለች ንብን ይምረጡ!” የሚል ነበር የቅንጅት ደግሞ “ ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ የመከራ የችጋር የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው ” የሚል ነበር፡፡ ይሄንን በሚገባ የተረዳው የኢትዮጵያ ሕዝብም በምርጫ ካርዱ ንቃቱን፣ ብስለቱን፣ ፍላጎቱን፣ ምኞቱን፣ ማንነቱን፣ አቋሙን ባረጋገጠ መልኩ ተናገረ ጮኸ አሰማ አስደመጠ፡፡ በሚያሳዝን መልኩ ወያኔም ይሁን የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በእሱ የንቃተ ሕሊናና የብስለት ደረጃ ያሉ ስላልነበሩ ምላሻቸው የሚያሳዝን ሆነ፡፡

“ቅንጅትን አለመምረጥ መብት ነው፤ ግን የሀገርን የስቃይ፣ የመከራ፣ የችጋር፣ የፈተና ዘመንን ማራዘም ነው” ይህ መሪ ቃል የእኔ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule