• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጥቂት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ

September 16, 2015 12:41 am by Editor Leave a Comment

 ተግባቢና በሳል ነው፤ ረጋ ባለ አንደበቱ የሚሰማውን በጥሞና መናገር ልዩ ያደርገዋል ፡፡ እምነቱን አጥበቆ ይወዳል፤ የእስልምና ሃይማኖት የሚያዛቸውን ተግባራት (ሶላት መስገድ፣ መጾም…) ፈጽሞ ሌሎች መሰሎቹ እንዲፈጽሙ ማድረግን ያውቅበታል፡፡ ከሌሎች የእምነት ተከታዮች ጋር የመግባባቱና ከሁሉም ጋር በአብሮነት መኖሩ ባጠቃላይ ማህበራዊ ኑሮ የሚጠይቀውን ግዴታ የመወጣት ልዩ ችሎታ አለው፡፡ ከማንም ሰው ጋር የመግባባት፣ ተጫውቶ የማጫወት ክህሎት አለው፡፡ ከቀለሙ በተጓዳኝ ሀይማኖታዊ እውቀቱም የተመሰከረለት ነው፡፡ ሙስሊም ተማሪዎችን በመሰብሰብ በስነ ምግባር እንዲታነጹና ለሀገራቸው ተቆርቋሪ እንዲሆኑ ያስተምራል፡፡ በግቢው ውሰጥ ተሰሚነት ካላቸው የሀይማኖት ሰዎች አንዱ ነበር፡፡

ካሚል ሽምሱን መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ሳለ አውቀው ነበር፤ አንድ ባችም ነበርን፤ በህግ ፋከልቲ ተደልድለን ለአምስት አመታት በቆየንባቸው ወራት ደጉንም ከፉንም አብረን አሳልፈናል፡፡ ካሚል ሸምሱ ጽንፈኛ የሆነ አመለካከት ሲያራምድ ለአንዲት ቀናት እንኳን አላየነውም፣ አልሰማነውም፤ በግቢው ውሰጥ ከነበረው ተወዳጅነት ተነስቶም እንዲህ አይነት ሀሳብ የነበራቸውን ተማሪዎች ሊገስጽ ይችል ይሆናል እንጂ አንዲትም ቀን ክፉ ሲወጣው አልሰማንም፡፡ ከዚህ ይልቅ በሳል አስተሳሰቦችንና አንድ የሚያደርጉ ስራዎችን ማከናውን ይቀናዋል – ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ፡፡ እንደውም እኛም ክርስትያንነታችን እርሱም ሙስሊምነቱ ሳይገድበን እንደ አንድ የአዳም ልጆች እንጨዋወታለን ቀልዶችን እያነሳን እንሳሳቃለን እንጂ ላንዲትም ቀን እርሱ የኛን እኛም የርሱን እምነት የተንተራሰ እሰጥ አገባ ወይንም መከፋፈል መሰረት ያደረግ ጉዳይ አንስተን አናውቅም፡፡ እንደውም አንተ የዚህ እኔ የዛ ነኝ የሚለው አስተሳሰብ ትዝም ብሎን አያውቅም፡፡ በዚህ መልኩ የህግን ሀ ሁ፣ ሰብአዊ መብቶችን፣ የህግ ሙያን ተምረን ወጣን፡፡ አገቱኒ፡፡

ሰብአዊ መብት ማለት የማይሸራረፍ አንድ ሰው ሰው ስለሆነ ብቻ የሚያገኘው መብት ማለት ነው፡፡ ሰብአዊ መብት አንዱ ባንዱ ካልተደገፈ፣ አንዱን አክብሮ ሌላዉን ቸል ያሉት እንደሆነ፣ አንዱን በአደባባይ አውሎ ሌላውን ጓዳ ውስጥ ከቆለፉበት ምንም ትርጉም አይኖረውም፣ ግንጥል ጌጥ የሚሉት አይነት ይሆናል፡፡ በአገራችን ዛሬ ዛሬ እየደመቀ የመጣው ሰብአዊ መብቶችን መቆራረጥና መሸራረፍ ችግር አንዱ አንዱን እየወለደ አገሪቷን ልትወጣው የማትችለው አዘቅት ውስጥ እየከታት እየመጣ እንደሆነ በሂደት ክስተቶች እያሳዩን መጥተዋል፡፡

መንግስት የእምነት ነጻነት ተረጋጧል እንደፈለግክ እምነትህን ማራመድ ትችላለህ ይልና በሌላ በኩል ደግሞ የእምነት መሮዎችህን የምመርጥልህ ግን እኔ ነኝ ይላል፡፡ የህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞው ከዚህ ይጀምራል፤ በታህሳስ 21 ቀን 2004 አ.ም. ጀማል መሀመድ የተባለው የመጅሊስ አመራር አወሊያ ትምህርት ቤት አንድ ደብዳቤ ይጽፋል፤ ደብዳቤው በርካታ የመስጂድ ኢማሞች፣ የትምህርት ቤቱ መምህራን እና የአረብኛ ተማሪዎች ከተቋሙ እንደተባረሩ ይገልጻል፤ ይህ ደብዳቤ መጅሊሱ ሙሉ በሙሉ ፓለቲካዊ ማስፈጸሚያ ወደ መሆን እንደተሸጋገረ ግልጽ ማሳያ ሆነ፡፡ ሀይማኖታቸው እንዲህ የካድሬ ማላገጫ መሆኗ ያበገናቸው ሰዎችም ተሰበሰቡ፣ አስራ ሰባት አባላትን ያቀፈ ኮሚቴ ሰየሙ፡፡ “የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ” በተሰኘው በዚህ ኮሚቴ አባል ለመሆን ከተመረጡት አንዱ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ነበር፡፡ ስራ ድልድል ላይም የኮሚቴው የህግ ተጠሪ ሆኖ ተመረጠ፡፡

ከዚህ በኋላ ኮሚቴው ስብሰባዎችን በሚያካሄድበት ቦታ ሁሉ የኮሚቴው አካሄድ ፍጹም ሰላማዊ እንደሆነ ህገ መንግስቱ ላይ የተካተቱ መብቶቻችን ይከበሩ ሲል ካሚል ሸምሱ ይናገር ነበር፡፡ ጥያቄያቸውም ሀይማኖታዊ ብቻ እንደሆነ ሳያሰልስ ለማስረዳት ሞክሯል፡፡ ባንዳንድ መስጊዶች ስብሰባ ላይም (ለምሳሌ በሻሸመኔ እንዲህ ማድረጉን ከአሌክስ አብርሀም የፌስቡክ ገጽ ላይ የተያያዘውን ፎቶ ማየት ይቻላል፡፡) የህገ መንግስቱን አንቀጾች እየጠቀሰ ጥያቄያቸው ህግንና ህግን የተከተለ መንገድ እንደሆነ አንደበተ ርትኡ የሆነው ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ተናግሯል፡፡

በግንቦት 8 ቀን 2004 አ.ም ኮሚቴው ስለተቋቋመበት አላማና የህዝበ ሙስሊሙ ወቅታዊ ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በዚህ ቃለ ምልልሱም ህዝበ ሙሲሊሙ ያነሳው ህገ መንግስታዊ ጥያቄዎች መሆናቸውንና ባእድ የሆነው የአህባሽ አስተምሮም በግድ ላያቸው ላይ ሊጫን በመሞከሩ መቃወማቸውን ተናግሯል፡፡ አያይዞም አህባሽ ለሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን፣ ለክርስትያኑ ባጠቃላይ ለሀገር ጸር የሆነ ሙስናን የሚያበረታታ አስተምህሮ ነው ሲልም ተናግሯል፡፡ በሌላ አነጋገር አህባሽ ጸረ ኢትዮጵያ አስተምህሮ ከሆነ የነካሚል ሸምሱ ትግልም ይህንን ባጭሩ ለመቅጨት ከሆነ ትግላቸው አገርን ማዳንም ጭምር ነበር ማለት ነው፤ በመሆኑም ለመስዋእትነታችሁ ታላቅ ዋጋ መስጠት ብቻ ሳይሆን እዳም እንዳለብን ተገንዝበናል፡፡ ነገሩ አስቀድሞ የገባቸው የሚመስሉ እንዳንድ ክርስትያኖች ኮሚቴው በሚጠራው ስብሰባ ላይ ይገኙ ነበር፡፡Kamil(1)

መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው ለጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ድረስ ደብዳቤ በመጻፍ ጥያቄያቸው ገለልተኛ መጅሊስ እንዲቋቋም፣ የአወሊያ ትምህርት ቤት አስተዳደር እንዲከለስ፣ የሀይማኖት ነጻነታቸው እንዲጠበቅ የሚያሳስብ ብቻ እንደሆነ ገልጧል፡፡ ይህ ቢሆንም ቅሉ በጥር የተቋቋመው ኮሚቴ አባላት በሀምሌ ወር 2004 አ.ም ለእስር ተዳረጉ፡፡ ለአገሩም ለእምነቱም ብዙ መስራት የሚችለው ካሚል ሸምሱ ከልጆቹና ከባለቤቱ ተነጥሎ ወደ እስር ቤት ተጋዘ፡፡ ለአራት ወራትም ያለ ፍርድ በማእከላዊ ታሰሮም ስቃየ ስቃያትን ተቀበለ፡፡ ጂሀዳዊ ሀረካት ተብሎ በወያኔ የተቀነባበረው ዶክመንተሪ ፊልም ላይም ካሚል ሸምሱን ሲያቀርብ መከራ እየደረሰበት መሆኑን ከገጽታው ማንበብ ይቻል ነበር፡፡ ማእከላዊ እንዲታሰሩ የተደረጉበት ቦታም ሳይቤሪያ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በበጋም በክረምትም እጅግ ቀዛቃዛ በመሆኑ እችክእችክ ያስብላል፡፡በማእከላዊ ቆይታቸውም አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጥቃቶችን ለማስተናገድ ተገደዋል፡፡ ከመርማሪዎቹ አንዱም‹‹ዓለም ላይ ያለን ጠበቃ ብታመጣ አታሸንፈንም ፖሊሱም የእኛ! አቃቤ ህጉም የእኛ! ዳኛውም የእኛ!›› ሲል እንደደነፋ ካሚል ሸምሱ ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል፡፡ ከዚህ ባለፈም በፍርድ ሂደቱ ጊዜ ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን ለአቃቤ በማቅረብ ሀሰት ራቁቱን እንዲቀር አድርጓል፡፡

ደፋር የሆነውና በመንግስት የሚደገፈው መጅሊስ ግን የህዝበ ሙስሊሙን መሪዎች አሳስሮ ሲያበቃ ምርጫ አካሂዳለሁና ተሳተፉ ሲል ቱሪናፋነቱን ሊያስመሰክር በቅቷል፡፡ መስከረም 27፤ 2005 በማደርገው ምርጫም ተሳተፉ ሲልም መለፈፍ ጀመረ፡፡ ካሚል ሸምሱም በጠበቃው አማካይነት መጅሊሱን በመክሰስ ምርጫውን እንዳያካሂዱ እግድ ይተላለፍ ዘንድ ጠይቆ ነበር፡፡ ወደ ቂሊንጦ እስር ቤት ከተዛወረ ወዲህ በእስረኞቹ ከፍተኛ ተወዳጅነትን በማትረፉ በከፍተኛ ድምጽ የታሳሪዎች ተወካይ ተደርጎ ተመርጧል፡፡ የሙስሊሞች ድምጽ፤ የቂሊንጦ ድምጽ፤ የድምጽ አልባዎች ድምጽ – ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ፡፡ በቂሊንጦ አስሩ በዞን 1 ታሰሮ የነበረ ሲሆን ወደ ዞን ሶስት እንዲዛወር ተደርጓል፤ የእስር ቤቱ ምክንያትም ሰዎችን እየሰበሰብክ ቁራን እንዲቀሩ ታደርጋለህ የሚል ነበር፡፡

እንደ ማራቶን በረዘመው የሶስት አመታት የፍርድ ቤት ምልልስና እንግልት በኋላ ካንጋሮው ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ናቸሁ ሲል በየነ፡፡ የሙስሊሙ ህጋዊ ተወካይ የሆኑትን ኮሚቴዎችም ከ 7 እስከ 22 አመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ ወሰነ፡፡ ከኮሚቴው አባላት መሀል 22 አመት የተፈረደባቸው አራት ሲሆኑ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ አንዱ ነው፡፡ እውነትና ፍትህ አገራቸው የት ይሆን ፍርዱን ተከትሎም ባንድ ክፍል አብረው ይማሩ ከነበሩ ጓደኞቹ ሁለቱ እንዲህ ብለዋል፣

  • Law school friend, Kamil Shemsu, fall prey to the constitution he studied! 22 yrs of sentencing for simply demanding constitutional rights?
  • Kamil was the most mature, intelligent, down to earth classmates I’ve ever had. As far as I am considered one cannot get as far from being a religious terrorist as Kamil. He was a good man.

ዛሬ የሙስሊሙ ማህበረሰብ በሀገርም በውጭም ያለው ካሚል ሸምሱን አንተ ብሎ አይጠራውም፤ ሰውን የሚያስከብረውም ሆነ የሚያወርደው ስራው ነውና ላመነበት ጉዳይ እስከ መጨረሻው በጽናት በመጓዙ አንቱ ተብሏል፡፡ እንዲህ አንቱታን ካተረፈ፣ ቃሉን ጠባቂ፣ ስለ እውነት እስከመጨረሻው ድረስ መስዋእት ከሆነ ሰው ጋር ባንድ ወንበር ቁጭ ብዬ መማሬ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል፤ በሌላ በኩል ደግሞ 22 አመታትን ያለ ሀጥያቱ እንዲታሰር በዝንጀሮው ፍርድ ቤት የተበየነበትን ወንድም ኡስታዝ ካሚል ሸምሱን ሳስበው እንባ ይተናነቀኛል፡፡

ህግን አሳምሮ ለሚያውቅ ግለሰብ ህጋዊ መብቶቹ ሲጣሱ መመልከት እጅግ የሚያደማ እንደሆነ እንገነዘባለን፤ ቢሆንም የዛሬ መስዋእትህ ለሀገርህ፣ ለልጆችህ፣ ከታሪክ ተጠያቂነት ለመዳን ያደረግው መሆኑ ያጽናናኛል፤ እውነት ግን መቼም ተሸፍና አትቀርም፣ ዋጋ የከፈላችሁለት አላማችሁም ጠብ አይልም፤ እውነት ነጻ ታወጣችኋለች፤ ወንድም ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ አንተም ሆንክ ፍትህ የተጠማው መላው ህዛባችን ከእውነተኛ ዳኛ ፍትህ የሚያገኙበት ቀን እጅግ ቅርብ ናት፡፡

አዲሱ አመት በጎ በጎውን የምንሰማበት ያድርግልን!

በሱፍቃድ ደረጄ

(besufekadereje@gmail.com)

ተጻፈ፤ መስከረም 02 2008 አ.ም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule