• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋርና ግብረአበሮቹ 10 ተደራራቢ ክሶች ተከፈተባቸው

September 19, 2020 10:33 pm by Editor 1 Comment

አቃቤ ሕግ በእነ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ ላይ ክስ የሚመሰርትበት ቀን አርብ መስከረም 8፤ 2013ዓም ነበር። ሆኖም በዚህ ክስ ይመሰረታል ተብሎ በሚጠበቅበት የመጨረሻው ቀን ተጠርጣሪዎቹ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

በዚህም አካልን ነጻ የማውጣት አቤቱታ ለፍርድ ቤት እንደሚያቀርቡ የነ ጃዋር መሐመድ ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ተናግረው ነበር።

ሆኖም ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ መሠረት ጃዋርና ሲራጅ መሐመድና ግብረአበሮቹ በ10 ተደራራቢ ክሶች ፋይል እንደከፈተባቸውና የክስ ቻርጁም መስከረም 11፤2013ዓም ፍርድ ቤት ሲቀርቡ እንደሚደርሳቸው አስታውቋል። ዐቃቤ ሕግ ያወጣው ጽሁፍ ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፤

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ

  • አቶ ጃዋር መሀመድ፤
  • አቶ በቀለ ገርባ፤
  • አቶ ሀምዛ አድናን

እንዲሁም በሌሉበት የተከሰሱትን

  • የኦሮሚያ ሜዲያ ኔትወርክ (OMN) ደጀኔ ጉተማ፤
  • ዶ/ር ብርሃነመስቀል አበበ እና
  • ፀጋዬ ረጋሳን

ጨምሮ በአጠቃላይ በ24 ሰዎች ላይ እንደየተሳትፏቸው፦

  • በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 240 በመተላለፍ ብሔርን እና ሐይማኖትን መሰረት ያደረገ የእርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ እንዲነሳሳ በማድረግ፤
  • የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/2012 በመተላለፍ፤
  • የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 761/2004 በመተላለፍ፤
  • የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1177/2012 በመተላለፍ በፈፀሙት ወንጀል

መስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በመዝገብ ቁጥር 260215 አስር ተደራራቢ ክሶችን መክፈቱን ገልጿል።

ተከሳሾቹ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ይደርሳቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዐቃቤ ህግ በታገደው የእነ ጃዋር መሐመድ ንብረት ላይ የሰጠው ምላሽ መስጠቱ ታውቋል።

አቶ ጃዋር መሐመድ “ለግል ፍጆታዬ ቤት ያስቀመጥኩት ጥሬ ገንዘብ እና ውድ ዋጋ ያላቸው ዕቃዎች ከቤቴ ተወስደውብኛል” በማለት በጠበቆቻቸው በኩል ላቀረቡት አቤቱታ አቃቤ ህግ በሰጠው ምላሽ፤“የፌደራል ፖሊስ ለወንጀል ምርመራው ይጠቅመኛል በማለት በብርበራ ከቤቱ ውስጥ በኢግዚቢትነት የተወሰደ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ ምላሽ ሊሰጥ አይገባም” ብሏል።

ሁለተኛው የአቃቤ ህግ ምላሽ የተመለከተው በአቶ በቀለ ገርባ፣ ሀምዛ አዳነ፣ ቦና ትቢሌ በተባሉ ሶስት ተጠርጣሪዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ስም የተመዘገቡ ስድስት መኪኖች ላይ የቀረበ አቤቱታን ነው።

አምስቱ መኪኖች የወንጀል ድርጊት የተገኙ እና ለወንጀል መፈጸሚያ የዋሉ በመሆናቸው የተያዘው ንብረት ይመለስልኝ በሚል የቀረበው አቤቱታ “ውድቅ ሊሆን ይገባል” ሲል አቃቤ ህግ ምላሽ ሰጥቷል።

አቃቤ ህግ ክርክሩን ያቀረበው አቶ ጃዋርን ጨምሮ 15 ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን የንብረት እገዳ ይነሳልን አቤቱታ በመቃወም ለፍርድ ቤት ዛሬ አርብ መስከረም 8፤ 2013 በጹሁፍ በሰጠው ምላሽ ነው። ጉዳዩን የሚመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ምላሹን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለመስከረም 19 ቀጠሮ ሰጥቷል።

በሌላ በኩል የአሥራት ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ በተወሰነው መሠረት ጋዜጠኞቹ ተፈትተዋል።

አቶ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር እና ምስጋናው ከፈለኝ ዛሬ መስከረም 9/2013 ዓ/ም ከእስር መፈታታቸውን ቴሌቪዥን ጣቢያው አሳውቋል።

የአሥራት ሚዲያ ጋዜጠኞች ዋስትና ከተፈቀደላቸው በኋላ እንደገና ታስረው የተከፈተባቸውን መዝገብ ፍርድ ቤት ውድቅ ይታወሳል።

ጋዜጠኞቹ 2ኛው መዝገብ ውድቅ በመደረጉ ባለፈው ጊዜ በተወሰነው መሰረት አዲስ ዋስትና ማስያዝ ሳያስፈልጋቸው ነበር ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ የወሰነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Middle Column, News Tagged With: chilot, jawar, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. picture-man says

    September 19, 2020 12:51 pm at 12:51 pm

    who is the picture?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule