• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋርና ግብረአበሮቹ 10 ተደራራቢ ክሶች ተከፈተባቸው

September 19, 2020 10:33 pm by Editor 1 Comment

አቃቤ ሕግ በእነ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ ላይ ክስ የሚመሰርትበት ቀን አርብ መስከረም 8፤ 2013ዓም ነበር። ሆኖም በዚህ ክስ ይመሰረታል ተብሎ በሚጠበቅበት የመጨረሻው ቀን ተጠርጣሪዎቹ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

በዚህም አካልን ነጻ የማውጣት አቤቱታ ለፍርድ ቤት እንደሚያቀርቡ የነ ጃዋር መሐመድ ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ተናግረው ነበር።

ሆኖም ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ መሠረት ጃዋርና ሲራጅ መሐመድና ግብረአበሮቹ በ10 ተደራራቢ ክሶች ፋይል እንደከፈተባቸውና የክስ ቻርጁም መስከረም 11፤2013ዓም ፍርድ ቤት ሲቀርቡ እንደሚደርሳቸው አስታውቋል። ዐቃቤ ሕግ ያወጣው ጽሁፍ ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፤

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ

  • አቶ ጃዋር መሀመድ፤
  • አቶ በቀለ ገርባ፤
  • አቶ ሀምዛ አድናን

እንዲሁም በሌሉበት የተከሰሱትን

  • የኦሮሚያ ሜዲያ ኔትወርክ (OMN) ደጀኔ ጉተማ፤
  • ዶ/ር ብርሃነመስቀል አበበ እና
  • ፀጋዬ ረጋሳን

ጨምሮ በአጠቃላይ በ24 ሰዎች ላይ እንደየተሳትፏቸው፦

  • በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 240 በመተላለፍ ብሔርን እና ሐይማኖትን መሰረት ያደረገ የእርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ እንዲነሳሳ በማድረግ፤
  • የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/2012 በመተላለፍ፤
  • የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 761/2004 በመተላለፍ፤
  • የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1177/2012 በመተላለፍ በፈፀሙት ወንጀል

መስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በመዝገብ ቁጥር 260215 አስር ተደራራቢ ክሶችን መክፈቱን ገልጿል።

ተከሳሾቹ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ይደርሳቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዐቃቤ ህግ በታገደው የእነ ጃዋር መሐመድ ንብረት ላይ የሰጠው ምላሽ መስጠቱ ታውቋል።

አቶ ጃዋር መሐመድ “ለግል ፍጆታዬ ቤት ያስቀመጥኩት ጥሬ ገንዘብ እና ውድ ዋጋ ያላቸው ዕቃዎች ከቤቴ ተወስደውብኛል” በማለት በጠበቆቻቸው በኩል ላቀረቡት አቤቱታ አቃቤ ህግ በሰጠው ምላሽ፤“የፌደራል ፖሊስ ለወንጀል ምርመራው ይጠቅመኛል በማለት በብርበራ ከቤቱ ውስጥ በኢግዚቢትነት የተወሰደ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ ምላሽ ሊሰጥ አይገባም” ብሏል።

ሁለተኛው የአቃቤ ህግ ምላሽ የተመለከተው በአቶ በቀለ ገርባ፣ ሀምዛ አዳነ፣ ቦና ትቢሌ በተባሉ ሶስት ተጠርጣሪዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ስም የተመዘገቡ ስድስት መኪኖች ላይ የቀረበ አቤቱታን ነው።

አምስቱ መኪኖች የወንጀል ድርጊት የተገኙ እና ለወንጀል መፈጸሚያ የዋሉ በመሆናቸው የተያዘው ንብረት ይመለስልኝ በሚል የቀረበው አቤቱታ “ውድቅ ሊሆን ይገባል” ሲል አቃቤ ህግ ምላሽ ሰጥቷል።

አቃቤ ህግ ክርክሩን ያቀረበው አቶ ጃዋርን ጨምሮ 15 ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን የንብረት እገዳ ይነሳልን አቤቱታ በመቃወም ለፍርድ ቤት ዛሬ አርብ መስከረም 8፤ 2013 በጹሁፍ በሰጠው ምላሽ ነው። ጉዳዩን የሚመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ምላሹን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለመስከረም 19 ቀጠሮ ሰጥቷል።

በሌላ በኩል የአሥራት ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ በተወሰነው መሠረት ጋዜጠኞቹ ተፈትተዋል።

አቶ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር እና ምስጋናው ከፈለኝ ዛሬ መስከረም 9/2013 ዓ/ም ከእስር መፈታታቸውን ቴሌቪዥን ጣቢያው አሳውቋል።

የአሥራት ሚዲያ ጋዜጠኞች ዋስትና ከተፈቀደላቸው በኋላ እንደገና ታስረው የተከፈተባቸውን መዝገብ ፍርድ ቤት ውድቅ ይታወሳል።

ጋዜጠኞቹ 2ኛው መዝገብ ውድቅ በመደረጉ ባለፈው ጊዜ በተወሰነው መሰረት አዲስ ዋስትና ማስያዝ ሳያስፈልጋቸው ነበር ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ የወሰነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Middle Column, News Tagged With: chilot, jawar, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. picture-man says

    September 19, 2020 12:51 pm at 12:51 pm

    who is the picture?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule