• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወላይታ ዞን አፈናና ወከባው ቀጥሏል

April 14, 2014 08:40 am by Editor Leave a Comment

መጋቢት 20/ 2006 ዓ.ም ሶዶ ውስጥ ስብሰባ ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ በነበረበት ወቅት ለእስር የተዳረጉት የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ድብደባና ወከባ እንደተፈጸመባቸው የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ጌታነህ ባልቻ ገለጹ፡፡

በወቅቱ ታስረው ከነበሩት መካከል ወጨፎ ሳዳሞ የወላይታ ዞን ምክትል ሰብሳቢ፣ ታደመ ፍቃዱ የወላይታ ዞን አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ፣ አቶ ጻድቁ ወ/ስላሴ የወላይታ ዞን የፋይናንስ ኃላፊ፣ አቶ ቴዎድሮስ ጌታ የዞኑ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ እና አቶ ቦጋለ የፓርቲው አባል ይገኙበታል፡፡ ጠዋት 4 ሰዓት ላይ የታሰሩት የዞኑ አመራሮች ምግብ፣ ውሃና ልብስ እንዳይገባላቸው ተከልክሎ እንደነበርም የአካባቢው አመራሮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

“ከዚህ በፊት ሁለት የፓርቲው አመራሮች በአራዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ለፓርቲው ስራ የሚገለገሉባቸውን ሰነዶች ተወስዶባቸዋል፡፡ የዞኑን መዋቅር ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ ወደ አካባቢው የተጓዙ ሶስት የፓርቲው አመራሮችና የአካባቢው ተወካዮች ታስረው ስራቸው ከመስተጓጎሉም ባለፈ መገልገያ እቃዎቻቸውን ተቀምተዋል፡፡” ያሉት አቶ ጌታነህ በአሁኑ ወቅት የሚደረገው እስርና ወከባ ከቀደመው የቀጠለ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ቅዳሜ መጋቢት 20 የታሰሩት የወላይታ ዞን የፓርቲው አመራሮች ከምሽቱ 4፡00 አካባቢ ከእስር ቢለቀቁም ሲም ካርዳቸውን በመስበር ከጥቅም ውጭ እንዳደረጉባቸው እና በራሪ ወረቀቶችን፣ ሰነዶችንና ሌሎች የመገልገያ መሳሪያዎችንም እንደቀሟቸው ታውቋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በምሽት የተፈቱት ታሳሪዎች ወደ ቤታቸው በሚያቀኑበት ወቅት የአራዳ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ታጠቅ፣ በሶዶ ከተማ የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር አቶ ጌታቸው መኮንን፣ የአራዳ ክ/ከተማ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዝናቡ ተክሌ፣ የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ አስተባባሪ አቶ መስከረም፣ እንዲሁም አቶ ተሾመ፣ አቶ ደጉና ሌሎች ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች የሰማያዊ ፓርቲ ወላይታ ዞን አደረጃጀት ኃላፊ የሆነውን አቶ ታደመ ፍቃዱ እና የዞኑ ም/ሰብሳቢ የሆነውን አቶ ወጨፎ ሳዳሞ በመደብደብ ጉዳት እንዳደረሱባቸው ከአካባቢው መዋቅር የተገኘውን መረጃ በመጥቀስ አቶ ጌታነህ ባልቻ ለዝግጅት ክፍላችን አስረድተዋል፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule