• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወላይታ ዞን አፈናና ወከባው ቀጥሏል

April 14, 2014 08:40 am by Editor Leave a Comment

መጋቢት 20/ 2006 ዓ.ም ሶዶ ውስጥ ስብሰባ ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ በነበረበት ወቅት ለእስር የተዳረጉት የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ድብደባና ወከባ እንደተፈጸመባቸው የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ጌታነህ ባልቻ ገለጹ፡፡

በወቅቱ ታስረው ከነበሩት መካከል ወጨፎ ሳዳሞ የወላይታ ዞን ምክትል ሰብሳቢ፣ ታደመ ፍቃዱ የወላይታ ዞን አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ፣ አቶ ጻድቁ ወ/ስላሴ የወላይታ ዞን የፋይናንስ ኃላፊ፣ አቶ ቴዎድሮስ ጌታ የዞኑ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ እና አቶ ቦጋለ የፓርቲው አባል ይገኙበታል፡፡ ጠዋት 4 ሰዓት ላይ የታሰሩት የዞኑ አመራሮች ምግብ፣ ውሃና ልብስ እንዳይገባላቸው ተከልክሎ እንደነበርም የአካባቢው አመራሮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

“ከዚህ በፊት ሁለት የፓርቲው አመራሮች በአራዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ለፓርቲው ስራ የሚገለገሉባቸውን ሰነዶች ተወስዶባቸዋል፡፡ የዞኑን መዋቅር ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ ወደ አካባቢው የተጓዙ ሶስት የፓርቲው አመራሮችና የአካባቢው ተወካዮች ታስረው ስራቸው ከመስተጓጎሉም ባለፈ መገልገያ እቃዎቻቸውን ተቀምተዋል፡፡” ያሉት አቶ ጌታነህ በአሁኑ ወቅት የሚደረገው እስርና ወከባ ከቀደመው የቀጠለ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ቅዳሜ መጋቢት 20 የታሰሩት የወላይታ ዞን የፓርቲው አመራሮች ከምሽቱ 4፡00 አካባቢ ከእስር ቢለቀቁም ሲም ካርዳቸውን በመስበር ከጥቅም ውጭ እንዳደረጉባቸው እና በራሪ ወረቀቶችን፣ ሰነዶችንና ሌሎች የመገልገያ መሳሪያዎችንም እንደቀሟቸው ታውቋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በምሽት የተፈቱት ታሳሪዎች ወደ ቤታቸው በሚያቀኑበት ወቅት የአራዳ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ታጠቅ፣ በሶዶ ከተማ የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር አቶ ጌታቸው መኮንን፣ የአራዳ ክ/ከተማ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዝናቡ ተክሌ፣ የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ አስተባባሪ አቶ መስከረም፣ እንዲሁም አቶ ተሾመ፣ አቶ ደጉና ሌሎች ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች የሰማያዊ ፓርቲ ወላይታ ዞን አደረጃጀት ኃላፊ የሆነውን አቶ ታደመ ፍቃዱ እና የዞኑ ም/ሰብሳቢ የሆነውን አቶ ወጨፎ ሳዳሞ በመደብደብ ጉዳት እንዳደረሱባቸው ከአካባቢው መዋቅር የተገኘውን መረጃ በመጥቀስ አቶ ጌታነህ ባልቻ ለዝግጅት ክፍላችን አስረድተዋል፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule