• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ለአውሮጳውያን (ስለ ምርጫው ውጤት) ‘ሌክቸር’ አልፈልግም ብዬ ነግሬአቸኋለሁ”

February 22, 2016 10:10 am by Editor Leave a Comment

በዑጋንዳ በተካሄደው ምርጫ አገሪቱን ለ30 ዓመት የመሩት ዮዌሪ ሙሰቪኒ ለአምስተኛ ጊዜ “አሸንፈዋል”፡፡ ተቀናቃኛቸው ምርጫው መጭበርበሩንና እንደማይቀበሉት ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንና አሜሪካ ምርጫው ዓለምአቀፋዊ ሕግጋትን የጠበቀ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ሙሰቪኒ ዋናው ዓላማቸው እስካሁን ኢትዮጵያን ያላካተተውን የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን መመሥረት እንደሆነና ስለምርጫው ከአውሮጳውያን “ሌክቸር” እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል፡፡

በምዕራባውያን ድለላና ድጋፍ በትጥቅ ትግል ወደ ሥልጣን የመጡት መለስ ዜናዊ፣ ኢሳያስ አፈወርቂ፣ ፖል ካጋሜ እና ዮዌሪ ሙሰቪኒ “አዲስ የአፍሪካ መሪዎች ውልድ (ዘር)” በመባል በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን እንዳልተሞካሹ በአሁኑ ወቅት ሁሉም ፍጹም አምባገነኖች ሆነዋል፡፡ መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድማቸው ኖሮ ከሌሎቹ ጋር በመሆን ማቆሚያ የሌለውን ሥልጣናቸውን ቀጥለው ነበር፡፡ ሌሎቹ ግን ሲያመቻቸው “በምርጫ” ካልሆነም በምርጫና በጠብመንጃ ካልሆነም ምርጫ አልባ በሆነ ስልት አምባገነናዊ አገዛዛቸውን ቀጥለዋል፡፡

uganda museveniቅዳሜ በተደረገው የዑጋንዳ ምርጫ አገሪቱን ለ30 ዓመታት የገዙት የ71ዓመቱ ዮዌሪ ሙሰቪኒ በ61 በመቶ አካባቢ በሆነ ብልጫ “አሸንፈዋል” ተብሎ በአገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን ይፋ ተደርጎላቸዋል፡፡ በአገርዓቀፉ ምርጫ ሙሰቪኒ እንደተመረጡ ቢነገርም ከካቢኔያቸው ውስጥ የመከላከያ ሚኒስትራቸውን እና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉን ጨምሮ 19 ሚኒስትሮቻቸው የፓርላማ መቀመጫቸውን አጥተዋል፡፡ “ለአምስተኛ ጊዜ ተመርጫለሁ” የሚሉት ሙሰቪኒ “በተለይ የገጠሩ ዑጋንዳዊ እኔንና ድርጅቴን ይወዳል” ቢሉም ሕዝቡ በሚደርስበት አፈና እና ጭቆና የምርጫ ትርጉሙንም ሆነ ፍላጎቱን እንዳጣ ይነገራል፡፡

በአገር አቀፍ ደረጃ ለመመምረጥ ከተመዘገበው 63 በመቶ አካባቢ ለምርጫ እንደወጣ ሲነገር በመዲናዋ ካምፓላ 46በመቶ ያህሉ ብቻ በምርጫው እንደተሳተፈ ተዘግቧል፡፡ የካምፓላ ነዋሪ የሆነውና የሞተር ብስክሌት ታክሲ (ቦዳ) የሚነዳው የ40ዓመቱ ስቲቨን የአስርሺህ ሽልንግ (የሦስት ዶላር) ቤንዚን ቀድቶ ወደ ምርጫ ጣቢያ በመሄድ ድምጽ መስጠት አቅሙ ስላልፈቀደለት ሳይመርጥ እንደቀረ ይናገራል፡፡ በመቀጠልም “(በአጠቃላይ ምርጫው ራሱ) ገንዘብ ማባከን ነው” በማለት መናገሩን ዘ ኢኮኖሚስት ዘግቧል፡፡museveni

የሙሰቪኒ የቀድሞ የግል ሃኪም የነበሩትን አሁን ግን ተቀናቃኛቸው በመሆን ለአራተኛ ጊዜ የተወዳደሩት ሐኪም ኪዛ ቤሲግዬ የምርጫውን ውጤት ፈጽሞ እንደማይቀበሉትና ደጋፊዎቻቸውም ይህንኑ አውቀው ተቃውሟቸውን እንዲያሰሙ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

የቀድሞውን መሪ ሚልተን ኦቦቴን ከሥልጣን ለማስወገድ በተደረገው ጦርነት የሙሰቪኒ የትግል አጋር የነበሩት የ59ዓመቱ ቤሲግዬ “እኛ እስካልተባበር ድረስ ይህ አገዛዝ መቆየት አይችልም፤ ስለዚህ ይህንን የምርጫ ሌብነት በአንድነት እናውግዝና ከዚህ አገዛዝ ጋር ያለንን ትብብር እናቋርጥ፤ እውቅናም አንስጠው” በማለት ጥሪ አሰምተዋል፡፡Besigye Arrested

የምርጫ ዘመቻ በሚካሄድበት ወቅት ከፍተኛ እንግልትና ስቃይ የተቀበሉት ሐኪም ባለፈው ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ሦስት ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ሰኞ እለት የምርጫ ዘመቻ እያካሄዱ ሳለ እንዲሁም ሐሙስ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ እንደገና አርብ ለእስር ተዳርገዋል፡፡ የምርጫው ውጤት ቅዳሜ ይፋ ከመሆኑ በፊት “ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ መድረክ – FDC” የተሰኘው የቤሲግዬ ፓርቲ ጽ/ቤት “የምርጫውን ውጤት ለብቻው ይፋ እንዳያደርግ ለመከላከል” በሚል በፖሊስ ከተወረረ በኋላ ነበር እርሳቸው ለእስር የተዳረጉት፡፡ አሁንም በቁም እስር ይገኛሉ፡፡

ምርጫው ዓለምአቀፋዊ መስፈርቶችን ያሟላ አይደለም በማለት አውሮጳውያንና አሜሪካ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ “(የሙሰቪኒ ተግባር) ሃሳብን በነጻ የመግለጽን ነጻነት ይጻረራል፤ በአገሪቷ ውስጥ የዛቻንና የማስፈራራትን አየር ይፈጥራል” በማለት የአውሮጳ ኅብረት ተናግሯል፡፡ አሜሪካ በበኩሏ የቤሲግዬ መታሰር እንዲሁም በምርጫው የተከሰተው ወከባና እንግልት እንዲሁም ድምጽ የመግዛት ተግባር እንደሚያሳስባት ተናግራለች፡፡ የጋራ ብልጽግና ኅብረት የምርጫ ታዛቢን የመሩት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ምርጫው “ወሳኝ የዴሞክራሲያዊ መለኪያዎችን እንዳላሟላ” ተናግረዋል፡፡BesigyeArrested demo002

ሙሰቪኒ ለዚህ ሁሉ መልስ ያጠራቸው አይመስሉም፡፡ “(አውሮጳውያን) ተሳስተዋል፤ እንዲያውም ለነዚህ አውሮጳውያን (ምርጫውን በተመለከተ) ከማንም ሌክቸር አልፈልግም ብዬ ነግሬአቸኋለሁ” በማለት የአጸፋ መልስ ሰጥተዋል፡፡ የአሜሪካ ጉዳይ እንደማያሳስባቸው በአነጋገራቸው እንደምታ የገለጹት ሙሰቪኒ “ሚ/ር ጆን ኬሪ (የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር) ደውለውልኝ ነበር፤ የምርጫን ጉዳይ በተመለከተ ሁሉ ልክ ማስገባቱን እናውቅበታን (ለእኛ ተዉልን) ብያቸዋለሁ” በማለት መናገራቸውን ሬውተር ዘግቧል፡፡

ሙሰቪኒ ለተቀናቃኛቸው የሰጡት ምላሽ ግን ከሁሉም የከረረው ነው፡፡ “ቢሲግዬ ማወቅ የሚኖርበት ነገር ቢኖር ኡጋንዳ ማለት አይቮሪ ኮስት ወይም ኬኒያ ማለት አይደለችም፤ በምርጫ ኮሚሽን ከተካሄደው የድምጽ ቆጠራ ሌላ ትይዩ ቆጠራ እንዲያደርግ አንፈቅድለትም” ካሉ በኋላ ሁኔታው በዚሁ የማያበቃ ከሆነ ቢሲግዬን እስርቤት እንደሚልኩ ዝተዋል፡፡

በቀድሞው የኬኒያ ምርጫ እንደተጭበረበሩ በስፋት የሚነገርላቸው ራይላ ኦዲንጋ በቀጣይ ለሚደረገው አገራዊ የፕሬዚዳንትነት ምርጫ “ትይዩ ቆጠራ” (parallel tallying) ለማድረግ ከጀርመን ኩባንያ ጋር ንግግር እያደረጉ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ በዚህ የትይዩ ቆጠራ አሠራር መሠረት ከሁሉም ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የሚሰጠውን ድምጽ ኩባንያው እየሰበሰበ እና እየቆጠረ ለቀጠረው ተቃዋሚ ፓርቲ መረጃውን ያስተላልፋል፡፡ በዚህም መሠረት ተቃዋሚው ትክክለኛውን ውጤት በሥልጣን ላይ ካለው አገዛዝ እንዳይነጠቅ የሚከላከልበትን በማስረጃ የሚያስደግፍበትን መረጃ የሚያገኝበት ይሆናል፡፡ በአምባገነናዊ አገዛዝ ሕዝባቸውን የሚጨቁኑ ግን “አንድ አገር ሁለት ዳኛ ሊኖራት አይገባም” በማለት አሠራሩን ሲቃወሙ ምርጫ በሕጋዊው የምርጫ ኮሚሽን ብቻ መፈጸም አለበት ይላሉ፡፡eac

እንደ መለስ፣ ኢሳያስ እና ካጋሜ የለውጥ ሃዋሪያ መሆናቸውን አስመስለው በ40ኛው ዕድሜያቸው ወደ ሥልጣን መንበር የመጡት ሙሰቪኒ እንደባልንጀሮቻቸው የተጠናወታቸው አምባገነንነት 30ዓመታት በመግዛት ሊበቃቸው አልቻለም፡፡ በመሆኑም በድጋሚ “በምርጫ” ስም በአምባገነንነቱ ቀጥለውበታል፡፡ ከኡጋንዳ ያለፈ ቀጣናዊ ዕቅድ እንዳላቸው የሚናገሩት ሙሰቪኒ በታኅሳስ 2007ዓም በአዲስ አበባ በተደረገ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ “የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን” የመፍጠር ዕቅድ እንዳላቸው ይፋ አድርገዋል፡፡

እንደ ሙሰቪኒ አነጋገር ከሆነ ይህ የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን አምስት አገራትን የሚጠቀልልና በድምሩ አንድ ወጥ የሆነ የምስራቅ አፍሪካ ልዕለኃያል አገር መፍጠር እንደሆነ ለኡጋንዳ ሬዲዮ የተናገሩትን ጠቅሶ ኒውስዊክ ዘግቧል፡፡ በዚህ ፌዴሬሽን ውስጥ የተጠቃለሉት አገራት ቡሩንዲ፣ ኬኒያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳ ናቸው፡፡ የፌዴሬሽኑ ዋና ዓላማ አገራቱን እንደ ቻይና፣ ሕንድ እና እንግሊዝ የመሳሰሉ ልዕለኃያላን እኩይ ምኞት መከላከል እንደሆነ ኢትዮጵያን የማያካትተው ፌዴሬሽን መሐንዲስ ሙሰቪኒ አስረድተዋል፡፡eac-presidents

እነዚህ አምስት አገራት የዛሬ 50ዓመት አካባቢ የተመሠረተው የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ (East African Community – EAC) አባል አገሮች ናቸው፡፡ የዚህ ማኅበረሰብ ሃሳብ የዛሬ 15 ዓመት አካባቢ እንደገና ተነሳስቶ ቀጣናውን ለመቆጣጠር ምኞት ባላቸው አምባገነኖች ብዙ ሲባልበት የኖረ ነው፡፡ ማኅበረሰቡ በአገራት መካከል ትብብር እንዲኖር የሚጥር ሲሆን በአውሮጳውያን ዓመት 2024 በአገራቱ መካከል የሚሠራ አንድ የመገበያያ ገንዘብ ይፋ የማድረግ ዕቅድ አለው፡፡ እኤአ 2010 በአገራቱ መካከል የጋራ ንግድ የተመሠረተ ሲሆን ይህም ሠራተኞችና ዕቃ በአገራቱ ድንበር በነጻ እንዲተላለፍ የሚፈቅድ ሆኗል፡፡ በያዝነው 2016 ዓመት ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳና ኬኒያ የፖለቲካ ውህደት (ፌዴሬሽን) ለመፍጠር ዕቅድ የያዙ ሲሆን ይህ ሃሳብ ወደፊት በመግፋት በአምስቱ አገራት መካከል የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን እንዲፈጠር የሙሰቪኒ ቀጣይ አጀንዳ ይሆናል፡፡ ዕቅዱ ተሳክቶ ተግባራዊ ከሆነ ሙሰቪኒ የአገራቸው ብቻ ሳይሆን የቀጣናውም አምባገነን ይሆናሉ!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule