• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጄኔራል ታደሰ ብሩና ኮሎኔል ሀይሉ ረጋሳ

September 16, 2014 07:44 pm by Editor 1 Comment

ይህንን ፎቶግራፍ ሰሞኑን በኢንተርኔት ላይ ሲንሸራሸር ነው ያገኘሁት፡፡ ፎቶውን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጣው በ1967 በመጋቢት ወር አጋማሽ የታተመ አንድ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅጂ ነው፡፡ ያ ጋዜጣ በደርግ ዘመን በድብቅ በከተማችን ይዘዋወር እንደነበረ ትዝ ይለኛል፡፡ በደርግ ውድቀት ማግስት ደግሞ የገለምሶ ከተማ ቀደምት ፎቶ ቤት የሆነው “ፎቶ አብደላ” የጋዜጣውን ኮፒና ይህንን ፎቶግራፍ ለየብቻቸው በማባዛት በሰፊው ሲያሰራጭ ቆይቷል (ፎቶ ቤቱ አንዱን ምስል በሶስት ብር ነው የሚሸጠው)፡፡

*****

በፎቶግራፉ ላይ የሚታዩት የሜጫና ቱለማ ማህበር አንጋፋ አባላት የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ታደሰ ብሩ እና ኮሎኔል ሀይሉ ረጋሳ ናቸው፡፡ አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሁለቱን ሰዎች ፎቶግራፍ ያተመው “ታደሰ ብሩና ግብረ አበሮቹ tadese biru abd hailu regassaተያዙ” የሚል ርዕስ ከሰጠው የዜና ዘገባ ጋር ይመስለኛል (ሙሉ ርዕሱን ዘንግቼዋለሁ)፡፡ ይሁን እንጂ በዘገባው የቀረበው “የመሬት ላራሹን አዋጅ በመቃወም ሸፍተው ሀገር ሲያተራምሱ የነበሩት እነ ጄኔራል ታደሰ ብሩ በህዝብ ትብብር ተያዙ” የሚል ከእውነታ የራቀ ሐተታ ነው፡፡ እነ ጄኔራል ታደሰ ለኦሮሞ ህዝብ መብት መከበር ሲሉ ነው በጫካ የመሸጉት እንጂ የመሬት አዋጁን በመቃወም አይደለም፡፡ ይህ የነ ጄኔራል ታደሰ ብሩ የትጥቅ አመጽ ጥንቱ የሜጫና ቱለማ እንቅስቃሴ ቀጣይ ሆኖ ነው የተለኮሰው፡፡

ጀኔራል ታደሰ ብሩ በዚያን ጊዜ በምስራቅ ኦሮሚያ የተጀመረውን የትጥቅ ትግል ሁለተኛ ግንባር በማዕከላዊው ኦሮሚያ ለመክፈት ከአስራ አምስት ያልበለጡ ሰዎችን አስከትለው በጥር ወር 1967 ወደ ምዕራብ ሸዋ ጫካዎች ገቡ፡፡ ይሁንና ብዙም ሳይራመዱ በየካቲት ወር መጨረሻ ላይ በጸጥታ ሀይሎች ተያዙ፡፡ ደርጎችም ጀኔራል ታደሰንና ኮሎኔል ሀይሉን በይስሙላ ፍርድ ቤት ካቆሟቸው በኋላ በመጋቢት ወር 1969 ረሸኗቸው (በነገራችን ላይ “መለስ ተክሌ” የሚባለው የትግራይ ቀደምት ፋኖ “በማዘጋጃ ቤት ላይ ፈንጂ አጥምዷል” የሚል ክስ ቀርቦበት ከጄኔራል ታደሰ ብሩ ጋር በአንድ ላይ ተረሽኗል፡፡ በቅርቡ የሞቱት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ “መለስ” በሚለው የትግል ስም ራሳቸውን የጠሩት መለስ ተክሌን ለማስታወስ በሚል ነው፤ የአቶ መለስ ዜናዊ የልደት ስም “ለገሠ ዜናዊ” ነው)፡፡

*****

የሜጫና ቱለማ እንቅስቃሴንና የጄኔራል ታደሰ ብሩን አመጽ ደራሲ ኦላና ዞጋ “ግዝትና ግዞት” የሚል ርዕስ በሰጠው መጽሐፍ በሰፊው ጽፎልናል፡፡ ስለዚህ ሰፊውን ታሪክ ከዚያ ማንበብ ይቻላል፡፡ እኔም ለወደፊቱ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የመጻፍ እቅድ አለኝ፡፡ ለአሁኑ ግን የሜጫና ቱለማ ማህበርን በተመለከተ አንድ አስፈላጊ መልዕክት ማስተላለፍ እፈልጋለሁ፡፡

“ሜጫና ቱለማ” ከየትኛውም የፖለቲካና የሀይማኖት ቡድን ጋር ያልወገነ አንጋፋ ማህበር ነው፡፡ መላውን የኦሮሞ ህዝብ የሚያስማማና የሚያግባባ ማህበር ቢኖር እርሱ ብቻ ናቸው፡፡ ባለቤትነቱም የመላው ህዝብ ነው፡፡ አባላቱም በፖለቲካና በሀይማኖት የተገደቡ አልነበሩም፡፡ ታዋቂው የኢትዮጵያ የውትድርና ሊቅ ሌፍትናንት ጄኔራል ጃገማ ኬሎ፣ በቅርቡ ስልጣናቸውን ያስረከቡት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ፣ የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ነጋሦ ጊዲዳ፤ የኦፌዴን አባላት የነበሩት እነ ዶ/ር ሞጋ ፍረዲሳና ኃይሥላሤ ወልዲያ፣ የኦነግ መስራች አባላት የሆኑት አባቢያ አባጆብር፣ ገላሳ ዲልቦ፣ ሌንጮ ለታ ወዘተ … የማህበሩ አባላት ነበሩ፡፡ ሟቾቹ ባሮ ቱምሳ፣ ቄስ ጉዲና ቱምሳ፣ የድሬ ዳዋው ቀኛዝማች አብዱልዓዚዝ መሐመድ፣ የአርሲው ሃጂ ሮበሌ፤ ወዘተ ከማህበሩ አንጋፋ መካከል ነበሩ፡፡

ሜጫና ቱለማ በኦሮሞዎች መካከል አንድነትንና ፍቅርን ለማጎልበት በሰፊው ሰርቷል፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ባህል፣ ታሪክና ቋንቋን ለማሳወቅም ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ ዛሬ ሁሉም የኦሮሞ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ ሲቪክ ማህበራትና የባህል ቡድኖች እንደ መለያ አርማ የሚገለገሉበትን የ“ኦዳ” (የሾላ ዛፍ) ምስል ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተዋወቀው የሜጫና ቱለማ ማክበር ነው፡፡ ይህ ማህበር በኦሮሞ ህዝብና በሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል በጠላትነት የመተያየት ክፉ አባዜ እንዳይኖርም በሰፊው አስተምሯል፡፡ በመሆኑም ከሌሎች የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች የተወለዱ በርካታ አባላት ነበሩት፡፡

ምንጭ: OPride.com
ምንጭ: OPride.com

የሜጫና ቱለማ ማህበር ታሪክ በአዎንታዊነቱ የምንጊዜም ተጠቃሽ ነው፡፡ ከኦሮሞ ህዝብ ውጪ ያሉ የፖለቲካ ቡድኖችና ግለሰቦችም በታሪኩ ይኮሩበታል፡፡ ህወሐት፣ ኢህአፓ፣ ኦነግ፣ “ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ” እና ሌሎችም የፖለቲካ ድርጅቶችና አባላቶቻቸው የጻፏቸውን ድርሳናት ብታዩ ይህንን በቀላሉ መረዳት ትችላላችሁ፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ (ሕወሐት)፣ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ (ግንቦት ሰባት)፣ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ኦፌኮ-መድረክ)፣ አቶ አባዱላ ገመዳ (ኦህዴድ)፣ አቶ አረጋዊ በርሀ (ትዴን)፣ አቶ አንዳርጋቸው አሰግድ (መኢሶን)፣ አቶ ክፍሉ ታደሰ (ኢህአፓ)፣ ዶ/ር ታደሰ ኤባ (ኦነግ) የጻፏቸውን መጻሕፍትና ያደረጓቸውን ንግግሮች ብትመለከቱ ስለሜጫና ቱለማ ማህበር ቀናውን ሲናገሩ እንጂ አንድም የነቀፋ አስተያየት ሲሰነዝሩ አታገኙም፡፡

ታዲያ በብዙዎች አንደበት እንዲህ የተደነቀው ታሪካዊ ማህበር ባለፉት 10 ዓመታት ከኦነግ ጋር ንክኪ አለው በሚል ምክንያት አላግባብ ታግዶ ነው ያለው፡፡ ማህበሩ የታገደው የዛሬ አስር ዓመት ገደማ “የኦሮሚያ ዋና ከተማ ፊንፊኔ እንጂ አዳማ አይደለችም” የሚል የተቃውሞ ሰልፍ በመዘጋጀቱ ነው፡፡ መሪዎቹና በርካታ አባላቱም “ከሽብርተኞች ጋር ንክኪ አላችሁ” ተብለው ታስረው ነበር፡፡ መሪዎቹ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ ባደረጉት ሽምግልና ተፈተዋል፡፡ ከአባላቱ መካከል ከፊሎቹ አሁንም እስር ቤት ነው ያሉት፡፡

ታዲያ የሚገርመው ነገር “የኦሮሚያ ዋና ከተማ አዳማ ናት” የሚል ውሳኔ ያሳለፉትና ውሳኔውን የተቃወመውን ሁሉ በጸረ-ሰላም ሲፈርጁ የነበሩት የኦህዴድ መሪዎች ከምርጫ-97 በኋላ ውሳኔያቸውን አጥፈው “የኦሮሚያ ዋና ከተማ ፊንፊኔ ናት” በማለት ወደ ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) መመለሳቸው ነው፡፡ ይህንን ጥያቄ በቀዳሚነት ያነሳው የሜጫና ቱለማ ማህበር ግን ከኦነግ ጋር ንክኪ አለው ተብሎ ታገደ፡፡ ያ ውሳኔ ዛሬም ድረስ እንደጸና ነው፡፡ ይህ ምን ዓይነት ፍትሕ ነው?

*****

እኛ ኦነግ አይደለንም፤ ኦህዴድም አይደለንም፤ ኦፌኮም አይደለንም፡፡ ፖለቲካው ውስጥ በጭራሽ የለንበትም፡፡ ሜጫና ቱለማ ግን የሁላችንም ነው፡፡ ኦሮሞ ነኝ የሚል ሰው በሙሉ ታሪኩን ይጋራዋል፡፡ ስለዚህ ይህ አንጋፋ ማህበር አላግባብ የተላለፈበት የእግድ ውሳኔ ተነስቶለት ታሪካዊ ሚናውን ይቀጥል ዘንድ እንዲፈቀድለት በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
——-
ግልባጭ
—-ለሚመለከተው ሁሉ …


Afendi Muteki is a researcher and author of ethnography, history and art with special focus on Eastern Ethiopia.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Engida says

    September 25, 2014 03:22 pm at 3:22 pm

    Tebarek Afendi!

    Oromo bicha sayhonu lelochm Ethiopianoch endezih ayinet netsa tekuamat endinoru yebekulachin’n astewatso enadrg.

    Silezih Mechana Tulema lai yetetalewu egid ahununu yinesa!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule