• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጋዛ ፍልስጥኤማውያን የደም እንባ!

July 18, 2014 04:56 pm by Editor Leave a Comment

የእስራኤል የ10 ቀናት የአየር ድብደባ ከ220 በላይ ፍልስጥኤማውያን የጋዛ ነዋሪዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በሚወሰደው ዘመቻ ነገን ላያዩ መቀጠፋቸውን እየሰማን ነው: (ከአንድ ሽህ በላይ የዘለቁ በጠና የቆሰሉትን እና ከቀያቸው የተፈናቀሉት ዜጎችን መከራ እያየንም ነው። እኒህኞቹን በራሳቸው ሀገር ስደተኛ የሆኑትንማ ፍዳ ማየቱ ከሞቱት በላይ ያማል።

ሰቆቃው በዚህ ቢያቆም መልካም ነበር ፣ ግን አልሆነም ።  በሳምንቱ መጀመሪያ የፍልስጥኤማውያን ሃማስ የጦር ክንፍ ሰው አልባ ሚጢጢ አውሮፕላን Drone …በእስራኤል ሰማይ መስፈንጠሩን አስታወቀ። ይህም የሃማስን የሚሳኤል ሮኬት ውንጨፋ ለወረራው ምክንያት ላደረጉት እስራኤሎች ከስጋት ባለፈ ጥሩ የመልሶ ማጥቂያ ምክንያት ሆነና ነገሮችን ሁሉ በፍጥነት መቀያየር ይዘዋል።

ብቻ …ዛሬ ሃሙስ ለአርብ በደረቁ ሌሊት የደረሰን ሰበር ዜና አስራኤል እግረኛ ጦር ወደ ጋዛ ማሰማራቷን ጠቁሟል። ሃማስም ከእግረኛው ጦር ጋር ፍልሚያው መጀመሩን ከዛቻ ጋር አስታውቋል። የተፈራው አደጋ  የፍጥጫ እልህ ውዝግቡ የፍጻሜ ውጤት አቅጣጫ እዚህ ላይ ደርሷል።  የቦንብ ናዳ  ያላባራባት ጋዛና የጋዛ ነዋሪ በሰማዩ ስር በሃዘን ድባብ ተውጦ ምድር ገሃነብ ሆኖበት ሰንብቷል። የሃማስ ተወንጫፊ ሚሳኤሎች ጎድተው ላይጎዱ በተለያዩ የጽዮኗ ምድር ከመዝነብ  ያቆማቸው የለም። እስካሁን ሞቶ የሰማነው እስራኤላዊ ቁጥር ግን አንድ ብቻ ነው።

እስራኤል  “ነውጠኛ አሸባሪው ሃማስን የማጽዳት ዘመቻ” በማለት በያዘችው ማጥቃት በምክንያትነት ከሚጠቀሱት  ኢላማዎች መካከል እስካሁን ተገደሉ የተባሉ ቁጥር ፣ ከተገደሉት ንጹሃን ጋር ሲወዳደር እዚህ ግባ አይባልም። በዋይታ ይህችን ፍትህ የጎደላት አለም እየተለዩ ያሉት ፍልስጥኤማውያን አቅመ የእድሜ ባለጸጋዎች፣ ህጻናትና አባወራ የቤተሰብ አባላት ናቸው። ይህ ልብን በሃዘን ቆልፎ ይሰብራል  🙁

ከሁሉም የሚዘገንነው በእስራኤል ዘመቻ የተቀጠፉት “ጦር ሰባቂ ፣ ቆስቋሽ ” የሚባሉት የሃማስ ሚሊሻዎች አለመሆናቸው ሲሆን ሚሊሽያ ታጣቂዎች እንደ ዶፍ በሚዘንበው አረር  ኢላማ የገቡ አይመስልም። “ለሃጥአን የመጣ ለጻድቃን ” እንዲሉ  በአዋጅ ነጋሪት ክተት ተብሎ የተዘመተባቸው ሃማሶች ሳይገደሉ ንጹሃን በግፍ እያለቁ ነው። ከሃማስ ሸማቂ በኩል ሞቱ የተባሉት ከቆሰሉት ጋር ቢደመሩ ከሃያ ፈቀቅ ለማለቱ መረጃ አላየሁም። ድብደባውም ሃማስን ሚሊሻዎች ሚሳኤል ከመወንጨፍ አላስቆማቸውም። ይህ ምልክት ያን ሰሞን ” የመከራ ደወል !” ያልኩትን የአደጋ ስጋት ሲያዘክር ዛሬ የስጋቱ ጊዜ አክትሞ መከራ ሰቆቃውን እያየነው ነው።  እየሆነ ያለው አሳዛኙ ውጤት ፍጻሜ ይህ ይመስላል !  ዳሩ ግን ሃማስን ለማንበርከክ የግዛት ክልሉንና የሚያስተዳድረውን ህዝብ በአየርና በምድር ጦር በትምክህት ደፍጥጦ መበቀል ከሆነ ሌላ ነገር ነው።

የሃማስ የጦር ክንፍ መክቶ  ላይመክት ፣ ጎድቶ ላይጎዳ ባስፈነጠራቸው ሮኬቶች ሌላ አደጋ በህዝቡ ላይ እያስከተለ ነው። በአጣብቂኝ ስርቻም ሆኘ በራሪ Drone  ሰራሁ ብሎ ማወጁ ለፍልስጥኤማውያን የፈየደው ወረራውን ማፋጠን ነው። ብቻ ሃማስ ከእስራኤል ጦር ጋር ተፋጦ በሚያደርገው መቆራቆስ የንጹሃን ደም ግብር የማከፈልበት መቸ ለሚመጣው፣  ማን ለሚኖርበት ትንሳኤ እንደሆነ አልገባኝ …

አረቦች ለፍልስጥኤም ግፉአን ወንድሞቻቸው መከታ እንዳይሆኑ በልዩነት ተበታትነዋል።  የአለም መንግስታት በአንጻሩ ይህ መሰሉ ግፍ በጋዛ ፍልስጥኤም ሲፈጸም ዛሬም መሸምገል ገዷቸው ደም ሲፈስ የግፍ ተመልካች ሆነዋል። በሩዋንዳው የጅምላ ጭፍጨፋ እልፍ አእላፍ አልቀው ፣ በትኩሱ ሬሳ ላይ ቆመው ያነቡት የአለም መራሔ መንግስታት  “ይህ ግፍ ፈጽሞ አይደገምም” Never Again ብለው ያፈሰሱት እንባ “የአዞ እንባ” መሆኑን ዛሬም ሆነ ትናንት በጋዛ ፍልጥኤማውያን እየሆነ ባለው “የአዛኝ እንባቸውን” እያየነው ነው: (

የእስራኤልን ዘመቻ ፣ የንጹሃንን እልቂት ፣ የሃማስን ስልት የጎደለው መከላከል በሉት ማጥቃት አልገባህ ብሎኛል። ይህንን ንጹሃን የሚቀጠፉበትን ዘመቻ ለማውገዝ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው። ይህ ሁሉ ውስብስብ ያልሆነ ግን ቅንነት ጠፍቶ የአለም  ማህበረሰብ መፍታት ባልቻሉት ውዝግብ በዚህ ዘመን ይህን ግፍ አለም ማስተናገድ ነበረባት?  ይህ ግልጽ የሃይል ሚዛን እና የተጽዕኖ መፍጠር ጫና  ለፍልስጥኤም ንጹሃን ማለቅና ለአለም ዝምታ መምረጥ ምክንያት አይደለምን ?  ይህስ በራሱ ግፍ አይደለምን ? ግልጽ የሚታየው እንቆቅልሽ መፈቻው ጊዜ መቸ ይሆን?  በሁለት ጽንፈኞች መካከል ታርቀው የሚረግፉት የፍልስጥኤማውያን እንባስ ማቆሚያው መቸ ነው?

እስኪ ቸር ያሰማን …

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule