• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሐዋሳ በእሣት ተመታች – እሣት አደጋ ነበር?

February 23, 2015 09:23 am by Editor Leave a Comment

በሐዋሳ ለጊዜው የጉዳቱ መጠን ያልታወቀ የእሣት ቃጠሎ መድረሱን በአደጋው ያዘኑ ገለጹ፡፡ ከስፍራው እንደተሰማው ለሰኞ አጥቢያ የተነሳው ቃጠሎ ምናልባትም በከተማዋ ታሪክ ከፍተኛው ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡ አደጋው ሲደርስ የእሣት አደጋ “አገልግሎት” በነዋሪዎች ላይ ቅሬታ አስነስቷል፡፡

ለሰኞ አጥቢያ ሌሊት ላይ ነፍሳት ባረፉበት ወቅት የደረሰው የእሣት አደጋ መነሻው በትክክል ባይታወቅም ማምለጥ የሚቻልበት ባለመሆኑ አሟሟቱ የከፋ እንዳደረገው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የተለያዩ ወገኖች በምስል ይፋ ያደረጉት ቃጠሎ እንደሚመለክተው የእሣቱ መጠን በቀላሉ የሚቆጣጠሩትና አደጋውን የሚቀንሱበት እንዳልነበረ ያስረዳል፡፡

በሐዋሳ ታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለው ይህ ቃጠሎ በህይወት ላይ ያደረሰው አደጋ በትክክለኛው ቁጥሩ ባይገለጽም ከሥፍራው የደረሰን አጭር መልዕክት እንደሚያስረዳው ከሰባት የማያንሱ መሞታቸውን ከ23 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቃጠሎ ደርሶባቸው የተጎዱ እንዳሉ፤ ሌሊት የተነሳ ቃጠሎ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብ ቢያስቸግርም ደረሰ የተባለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ቀውስ ከዚህ የበለጠና ምናልባትም ኅሊናን የሚጎዳ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡

በዚሁ በደረሰን አጭር መልዕክት እሣቱን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የከተማዋ የእሣት አደጋ ብርጌድ “እውን ሐዋሳ የእሣት አደጋ ብርጌድ አላት?” የሚያሰኝ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ለመባሉ ምክንያቱ በዝርዝር አልተገለጸም፡፡ ምናልባትም አደጋው ሌሊት ላይ መከሰቱ በሰው ህይወት ላይ የተመዘገበውን አኻዝ ከሚገመተው በላይ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡

የዝግጅት ክፍላችን በደረሰው የህይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት የተሰማውን ልባዊ ሐዘን በዚህ አጋጣሚ ይገልጻል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢህአዴግ በዛሬው (ሰኞ) ዕለት የሚከተለውን ዜና አሰምቶዋል:: የሞቱት ቁጥር አከራካሪ ቢሆንም በሚቀጥሉት ቀናት ሊጨምር እንደሚችል ከሁሉም አቅጣጫ እየተሰማ ነው፡፡

በሃዋሳ ከተማ ቅዳሜ ምሽት 1 ስዓት ላይ በደረሰ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

አዲሱ ገበያ ተበሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ በደረሰው አደጋ 1 አመት ከስድስት ወር የሚሆን ህፃን ህይወቱ አልፏል።

አንዲት እናት ደግሞ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

በመምሪያው የወንጀልና የትራፊክ አደጋ መከላከል ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ ዋና ኢንስፔክተር በላይ የኔው፥ የእሳት አደጋውን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር የተቻለው ከ40 ደቂቃ በኋላ ነው ብለዋል።

ህብረተሰቡና የከተማዋ አስተዳደር ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ እሳቱን መቆጣጠር መቻሉንም ነው ኢንስፔክተር በላይ የገለጹት።

በአደጋው የደረሰው የንብረት ውድመትና መንስኤውን የማጣራት ስራም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ቤቶቹ የተሰሩባቸው ቁሳቁሶችና በወቅቱ የነበረው ነፋሻማ የአየር ሁኔታ እሳቱን በቀላሉና በፍጥነት ለመቆጣጠር አዳጋች አድርጎት ነበር ነው ያሉት ዋና ኢንስፔክተሩ።

በአደጋው የተጎዱ ከ500 በላይ ሰዎችም ጊዜያዊ መጠለያ ተሰርቶላቸዋል ብለዋል።

በቀጣይ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ለማቋቋም ከክልሉ መንግስት ጋር በመሆን የተለያዩ ስራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። (በብርሃኑ በጋሻው ኤፍ.ቢ.ሲ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule